• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

በአዲስ አበባ ለተከሰተው የነዳጅ አሻጥር መፍትሔ ሊበጅለት ነው

January 18, 2019 12:39 am by Editor Leave a Comment

በአዲስ አበባ ከተማ የቤንዚን ነዳጅ እጥረት እንዲከሰት እና እንዲባባስ በሚያደርጉ ነዳጅ አቅራቢዎች እና አከፋፋዮች ላይ አስፈላጊውን ክትትል እያደረገ መሆኑን የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን አስታወቀ።

በአገር አቀፍ ደረጃ በቂ ነዳጅ እያለ ነገር ግን በአዲስ አበባ ከተማ የቤንዚን እጥረት እንዲከሰት እና እንዲባበስ በመደረጉ ያጋጠመውን ችግር ለመፍታት አዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽንን ጨምሮ ሌሎች ባለድርሻ አካላትን ያካተተ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ክቡር ኢንጂነር ታከለ ኡማ የሚመራ ግብረ ኃይል ተቋቁሞ ስራ መጀመሩ ይታወቃል።

በከተማችን ነዳጅ ለማከፋፈል 120 ገደማ የሚሆኑ የነዳጅ ማደያዎች በሕግ አግባብ ፈቃድ መውሰዳቸው እየታወቀ 106ቱ ብቻ አገልግሎት እየሰጡ መሆኑን አዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን አስታውቋል።

ጥር 8 ቀን 2011 ዓ/ም በስራ ላይ ከሚገኙ 106 የነዳጅ ማከፋፈያዎች መካከል 100 ማደያዎች ላይ በተደረገው ክትትል 54ቱ በቂ የቤንዚን እና የናፍታ፣ 5ቱ የቤንዚን ብቻ፣ 8ቱ የናፍታ ክምችት ያላቸው ሲሆን 30 ማደያዎች ደግሞ ነዳጅ ማራገፍ ሲገባቸው ያላራገፉ በመሆኑ፣ ቀሪዎቹ ሙሉ ለሙሉ ዝግ ሲሆን አንዳንዶች ለእረጅም ጊዜ አገልግሎት መስጠት በማቆማቸው ጊዚያዊ የቤንዚን እጥረት መከሰቱን ኮሚሽኑ አረጋግጧል።

እጥረቱን ለማባባስ ልዩ ልዩ ምክንያች እንዳሉ በተደረገው ክትትል ማወቅ ሲቻል አንዳንድ የማደያ ሰራተኞች ከህገ-ወጦች ጋር በመተባበር ነዳጅ በተለይ ደግሞ ቤንዚን በበርሜል በመገልበጥ፣ በሞተር ብሰክሌትና በሌሎች ተሽከርካሪዎች ከስፍራ ወደ ስፍራ በማጓጓዝ በጥቁር ገበያ በከፍተኛ ዋጋ ሲሸጡ እንደተደረሰባቸው፣ እንዲሁም ሌሎች ሆን ብለው ነዳጅ በመደበቅ፣ ነዳጅ እያላቸው ለምሳና ለእራት ወጥተናል በሚል ሰበብ በመፍጠር፣ የተወሰኑ ደግሞ 24 ሰዓት አገልግሎት መስጠት ሲገባቸው ያለበቂ ምክንያት በመዘጋታቸው የማደል ስራው እንዲስተጓጎል እያደረጉ መሆኑን ፖሊስ ገልፆ እጥረቱን ምክንያት በማድረግ በትራንስፖርት አገልግሎት ላይ ህገ-ወጥ የሆነ የዋጋ ጭማሪ መደረጉን ደርሶበታል።

ህጋዊ ፈቃድ ወስደው ያለበቂ ምክንያት አገልግሎት የማይሰጡ ማደያዎች በአስቸኳይ ሥራቸውን እንዲጀምሩ እንዲሁም በጥቁር ገበያ ነዳጅ በህገ-ወጥ መንገድ በመሸጥ ላይ ያሉ ከህገ-ወጥ ድርጊታቸው እንዲቆጠቡ ኮሚሽኑ አሳስቦ ነገር ግን ማሳሰቢያውን ተግባራዊ በማያደርጉ ተቋማትና ግለሰቦች ላይ ከከተማ አስተዳደሩ ጋር በመሆን በቁጥጥር ስር አውሎ ምርመራ እያጣራ መሆኑን ኮሚሽኑ ከላከው ዘገባ ለመረዳት ተችሏል። በተጨማሪም ነዋሪዎች ሕገወጥ ተግባራትን በነፃ የስልክ መስመር 991 ወይም 01-11-11-01-11 መጠቀም ለፖሊስ ጥቆማ እንዲያደርጉ ኮሚሽን አስታውቋል።

በሌላ በኩል ሪፖርተር ባወጣው ዘገባ ባለፉት ቀናት በፀጥታ ችግር ምክንያት በመዲናዋ አዲስ አበባና በክልል ከተሞች የተስተጓጎለው የነዳጅ አቅርቦት በጥቂት ቀናት ውስጥ እንደሚፈታ ገልጾዋል።

በአፋር ክልል በተቀሰቀሰ ተቃውሞ ከእሑድ ጥር 5 ቀን 2011 ዓ.ም. ጀምሮ የጂቡቲ መስመር ለሁለት ቀናት ያህል በመዘጋቱ፣ 1,000 የሚሆኑ የነዳጅ ማመላለሻ ተሽከርካሪዎች ወደ መሀል አገር የሚያደርጉት ጉዞ ተስተጓጉሏል። ከጂቡቲ የሚመጡ ብቻ ሳይሆን ወደ ጂቡቲም የሚጓዙ ተሽከርካሪዎች ለመቆም ተገደው ነበር። በአጠቃላይ የጭነት ተሽከርካሪዎች የአፋር ክልልን ለማቋረጥ ተቸግረው ቆይተዋል።

በድሬዳዋ በኩል የገቡትም የተወሰኑ ነዳጅ አመላላሽ ተሽከርካሪዎች ሰኞ ጥር 6 ቀን 2011 ዓ.ም. አዋሽ ላይ መንገድ ስተለዘጋባቸው መሻገር አልቻሉም። በዚህ ምክንያት ቤንዚን፣ ናፍጣና የአውሮፕላን ነዳጅ የጫኑ 1,000 ያህል ተሽከርካሪዎች በተለያዩ ቦታዎች ቆመው እንደነበር ለማወቅ ተችሏል።

የኢትዮጵያ ነዳጅ አቅራቢ ድርጅት ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ታደሰ ኃይለ ማርያም ለሪፖርተር እንደተናገሩት፣ በአፋር ክልል የተዘጉት ዋና ዋና መንገዶች ሰኞ ጥር 6 ቀን 2011 ዓ.ም. በመከፈታቸው የነዳጅ ማመላለሻ ተሽከርካሪዎች ጉዟቸውን ቀጥለዋል። “የቆሙት የነዳጅ ማመላለሻ ተሽከርካሪዎች ብቻ ሳይሆኑ የደረቅ ጭነት ማመላለሻ ተሽከርካሪዎች ጭምር በመሆናቸው፣ መንገድ ላይ የትራፊክ መጨናነቅ ስለሚኖር አዲስ አበባ ለመድረስ አንድ ሁለት ቀን ይፈጅባቸዋል። ከማክሰኞ ጥር 7 ቀን 2011 ዓ.ም. ጀምሮ አዲስ አበባ መግባት ስለሚጀምሩ የተፈጠረው የነዳጅ እጥረት ይቀረፋል። ወደ ክልል ከተሞች እስኪደርሱ ሁለትና ሦስት ቀናት ሊፈጅ ይችላል። በክልል ከተሞች የተፈጠረው የነዳጅ እጥረት በሳምንቱ መጨረሻ ይፈታል። በአዲስ አበባ ግን ከረቡዕ ጥር 8 ቀን 2011 ዓ.ም. ጀምሮ ይረጋጋል፤” ብለዋል።

ባለፈው ሳምንት በአማራ ክልል በምዕራብ ጎንደር ዞን በተፈጠረ ግጭት ሳቢያ ከሱዳን ወደ ኢትዮጵያ ነዳጅ የሚያመላልሱ የነዳጅ ማመላለሻ ተሽከርካሪዎች መተማ ከተማ ለመቆም መገደዳቸው ይታወሳል። በምዕራብ ጎንደር ዞን በተፈጠረው የፀጥታ ሥጋት 70 ያህል ቤንዚን የጫኑ የነዳጅ ማመላለሻ ተሽከርካሪዎች መተማ ከተማ እንደቆሙ ታውቋል። ቤንዚን ለማምጣት ወደ ሱዳን የሚጓዙ ተሽከርካሪዎች በተመሳሳይ ችግር መጓዝ ባለመቻላቸው፣ ከሱዳን የሚገባው የቤንዚን ምርት ሙሉ በሙሉ ተቋርጧል።

የኢትዮጵያ ነዳጅ ማመላለሻ ተሽከርካሪዎች ቤንዚን የሚቀዱት ከካርቱም 60 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ ከሚገኘው ጌሊ የነዳጅ ማጣሪያ ነው። የሱዳን ፔትሮሊየም ኮርፖሬሽን በኢትዮጵያ ተሽከርካሪዎች እስከ ጥር 6 ቀን 2001 ዓ.ም. ሲጭን የነበረ ቢሆንም፣ ከጥር 7 ቀን 2011 ዓ.ም. ጀምሮ ተሽከርካሪ ማግኘት አልቻለም።

የተዘጋው የመተማ መንገድ ከረቡዕ ጥር 8 ቀን 2011 ዓ.ም. ጀምሮ የሚከፈት በመሆኑ፣ የተከሰተው የቤንዚን እጥረት በጥቂት ቀናት ውስጥ እንደሚፈታ አቶ ታደሰ ተናግረዋል። “ከሱዳን በአሁኑ ወቅት የምናስገባው ቤንዚን የፍጆታችንን 20 በመቶ በመሆኑ ያን ያህል የጎላ ተፅዕኖ አይኖረውም። ዋናው ነገር 80 በመቶ የቤንዚን ፍጆታችን የሚገባው ከጂቡቲ ወደብ በመሆኑ የአፋር ክልል መንገዶች መከፈታቸው ነው፤” ያሉት አቶ ታደሰ፣ የነዳጅ እጥረቱ በጥቂት ቀናት ውስጥ እንደሚፈታ ያላቸውን እምነት ገልጸዋል።

“ችግሩ ሊከሰት የቻለው በጊዜያዊ የፀጥታ ችግር ነው። የነዳጅ ምርት አቅርቦት ወይም የግዥ ችግር የለም። የተዘጉት መንገዶች በመከፈት ላይ በመሆናቸው የቆሙት ተሽከርካሪዎች እስኪደርሱ ለሁለትና ለሦስት ቀናት ችግር ሊኖር ይችላል። ነገር ግን ኅብረተሰቡ በጥቂት ቀናት ውስጥ የሚፈታ ጊዜያዊ ችግር መሆኑን ተረድቶ መረጋጋት ይኖርበታል። በእርግጠኝነት ችግሩ እስከ ሐሙስና ዓርብ እንደሚፈታ መናገር ይቻላል፤” ብለዋል።

ከሱዳን የሚገባው ቤንዚን በአብዛኛው የሚከፋፈለው በአማራ ክልል ውስጥ በመሆኑ፣ በአዲስ አበባ ከተማ ላይ የጎላ ተፅዕኖ እንደማይኖረው ምንጮች ለሪፖርተር ተናግረዋል።

አዲስ አበባ ውስጥ ሪፖርተር ያነጋገራቸው የነዳጅ ማደያ ባለቤቶች የአፋር ክልል መንገድ በመከፈቱ፣ ነዳጅ የጫኑ ተሽከርካሪዎች ይገባሉ ተብለው በመጠባበቅ ላይ እንደሆኑ ገልጸዋል።

(ፎቶ፤ ከኦይል ሊቢያ የነዳጅ ማደያዎች በአንደኛው ቤንዚን እንደሌለ በጽሑፍና በነዳጅ ቀጂ ሠራተኛ ጭምር ሲገለጽ)

ጎልጉል፤ የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ከፍተኛ የፋኖ አመራሮች መገደላቸው ተነገረ May 6, 2025 10:40 pm
  • ሃይማኖትን ለተራ የፖለቲካ ሸቀጥ ማዋል ውርደት ነው April 24, 2025 12:43 am
  •  የኬሪያ ኢብራሒም ኑዛዜ “ብትንትናችን ወጥቷል” April 22, 2025 12:08 am
  • ለወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን አመራሮች ወታደራዊ ሥልጠና ተሰጠ April 16, 2025 11:44 pm
  • ዓቅም እንደሌለው የገመገመው ሻዕቢያ ፊቱን ከጦርነት ወደ ዲፕሎማሲ እያዞረ ነው   April 15, 2025 12:32 am
  • “አንድ የፋኖ ተቋም (የእስክንድር) ተመሥርቷል፤ ሌሎቹ ደግሞ እንዲሁ አንድ ተቋም መሥርተው ወደዚህ ይመጡ” አበበ ጢሞ April 11, 2025 12:07 am
  • መለስ (ለገሰ) ዜናዊ – ተዋርዶ ያዋረደን! April 9, 2025 10:28 pm
  • የተከዜ ዘብ: የሉዓላዊነት መጠበቂያ April 8, 2025 11:49 pm
  • አዲስ አበባ አስተዳደር የሪፖርተርን የተዛባ መረጃ ኮነነ፤ ሕጋዊ እርምጃ እወስዳለሁ አለ April 8, 2025 10:06 pm
  • ሀሰተኛውን የሪፖርተር ዘገባ ንግድ ባንክ በጽኑ ተቃወመ፤ እርማትም ጠየቀ April 8, 2025 09:48 pm
  • “ኦሮሚያ ላይ ወይም ሌላ ቦታ ላይ ስታደርገው ከነበረ ትግራይ ወስጥም የማታደርግበት ምንም ምክንያት አይኖርህም” ነው ጌታቸው ረዳ April 7, 2025 10:22 pm
  • “TPLF’s belief in a strong federal government was always tied to its own dominance in Addis Ababa” April 7, 2025 10:15 pm
  • Counter-Video by EBC Challenges EBS Broadcast, Sparks Public Outcry Over Alleged Misinformation March 31, 2025 02:36 am
  • የኤሊያስ መሠረትን ፌክ መረጃ ማን ያጋልጥ? February 19, 2025 06:00 pm
  • አዘርባጃን፡ የሻዕቢያን ሸምቀቆ ማጥበቂያ?! February 19, 2025 12:29 am
  • የአሜሪካ ድምፅ/ቪኦኤ ይዘጋ ተባለ  February 12, 2025 03:37 am
  • የብልፅግና ፓርቲ ሹመኛ ካድሬዎች February 3, 2025 11:07 am
  • ትግሉን የጎዳው የእስክንድር ነጋ አካሄድ February 3, 2025 10:29 am
  • ኤሊያስ መሠረት “ጭምብሉ ዛሬ ወለቀ”፤ ተከፋይ ነው! February 2, 2025 05:32 pm
  • የፋሲል ግንብ እድሳት እንዴት ተካሄደ? የመንጣቱ ምክንያት? January 23, 2025 03:41 pm
  • ታሪካዊዉ የፋሲል ቤተመንግሥት ለምን ነጣ? January 23, 2025 03:04 pm
  • የኢትዮጵያ አየር መንገድ በተወልደ አስተዳደር ዘመን ለተሠራ ስህተት 425ሺ ዶላር ተቀጣ December 14, 2024 01:44 am
  • በትግራይ ከሞትና ከአካላዊ ጉዳት የተረፉት ለስደት ተዳርገዋል November 27, 2024 12:09 pm
  • የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት አሠራሩን እንዲያርም ጥብቅ መመሪያ ተሰጠው November 27, 2024 11:31 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule