• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

በአዲስ አበባ ለተከሰተው የነዳጅ አሻጥር መፍትሔ ሊበጅለት ነው

January 18, 2019 12:39 am by Editor Leave a Comment

በአዲስ አበባ ከተማ የቤንዚን ነዳጅ እጥረት እንዲከሰት እና እንዲባባስ በሚያደርጉ ነዳጅ አቅራቢዎች እና አከፋፋዮች ላይ አስፈላጊውን ክትትል እያደረገ መሆኑን የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን አስታወቀ።

በአገር አቀፍ ደረጃ በቂ ነዳጅ እያለ ነገር ግን በአዲስ አበባ ከተማ የቤንዚን እጥረት እንዲከሰት እና እንዲባበስ በመደረጉ ያጋጠመውን ችግር ለመፍታት አዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽንን ጨምሮ ሌሎች ባለድርሻ አካላትን ያካተተ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ክቡር ኢንጂነር ታከለ ኡማ የሚመራ ግብረ ኃይል ተቋቁሞ ስራ መጀመሩ ይታወቃል።

በከተማችን ነዳጅ ለማከፋፈል 120 ገደማ የሚሆኑ የነዳጅ ማደያዎች በሕግ አግባብ ፈቃድ መውሰዳቸው እየታወቀ 106ቱ ብቻ አገልግሎት እየሰጡ መሆኑን አዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን አስታውቋል።

ጥር 8 ቀን 2011 ዓ/ም በስራ ላይ ከሚገኙ 106 የነዳጅ ማከፋፈያዎች መካከል 100 ማደያዎች ላይ በተደረገው ክትትል 54ቱ በቂ የቤንዚን እና የናፍታ፣ 5ቱ የቤንዚን ብቻ፣ 8ቱ የናፍታ ክምችት ያላቸው ሲሆን 30 ማደያዎች ደግሞ ነዳጅ ማራገፍ ሲገባቸው ያላራገፉ በመሆኑ፣ ቀሪዎቹ ሙሉ ለሙሉ ዝግ ሲሆን አንዳንዶች ለእረጅም ጊዜ አገልግሎት መስጠት በማቆማቸው ጊዚያዊ የቤንዚን እጥረት መከሰቱን ኮሚሽኑ አረጋግጧል።

እጥረቱን ለማባባስ ልዩ ልዩ ምክንያች እንዳሉ በተደረገው ክትትል ማወቅ ሲቻል አንዳንድ የማደያ ሰራተኞች ከህገ-ወጦች ጋር በመተባበር ነዳጅ በተለይ ደግሞ ቤንዚን በበርሜል በመገልበጥ፣ በሞተር ብሰክሌትና በሌሎች ተሽከርካሪዎች ከስፍራ ወደ ስፍራ በማጓጓዝ በጥቁር ገበያ በከፍተኛ ዋጋ ሲሸጡ እንደተደረሰባቸው፣ እንዲሁም ሌሎች ሆን ብለው ነዳጅ በመደበቅ፣ ነዳጅ እያላቸው ለምሳና ለእራት ወጥተናል በሚል ሰበብ በመፍጠር፣ የተወሰኑ ደግሞ 24 ሰዓት አገልግሎት መስጠት ሲገባቸው ያለበቂ ምክንያት በመዘጋታቸው የማደል ስራው እንዲስተጓጎል እያደረጉ መሆኑን ፖሊስ ገልፆ እጥረቱን ምክንያት በማድረግ በትራንስፖርት አገልግሎት ላይ ህገ-ወጥ የሆነ የዋጋ ጭማሪ መደረጉን ደርሶበታል።

ህጋዊ ፈቃድ ወስደው ያለበቂ ምክንያት አገልግሎት የማይሰጡ ማደያዎች በአስቸኳይ ሥራቸውን እንዲጀምሩ እንዲሁም በጥቁር ገበያ ነዳጅ በህገ-ወጥ መንገድ በመሸጥ ላይ ያሉ ከህገ-ወጥ ድርጊታቸው እንዲቆጠቡ ኮሚሽኑ አሳስቦ ነገር ግን ማሳሰቢያውን ተግባራዊ በማያደርጉ ተቋማትና ግለሰቦች ላይ ከከተማ አስተዳደሩ ጋር በመሆን በቁጥጥር ስር አውሎ ምርመራ እያጣራ መሆኑን ኮሚሽኑ ከላከው ዘገባ ለመረዳት ተችሏል። በተጨማሪም ነዋሪዎች ሕገወጥ ተግባራትን በነፃ የስልክ መስመር 991 ወይም 01-11-11-01-11 መጠቀም ለፖሊስ ጥቆማ እንዲያደርጉ ኮሚሽን አስታውቋል።

በሌላ በኩል ሪፖርተር ባወጣው ዘገባ ባለፉት ቀናት በፀጥታ ችግር ምክንያት በመዲናዋ አዲስ አበባና በክልል ከተሞች የተስተጓጎለው የነዳጅ አቅርቦት በጥቂት ቀናት ውስጥ እንደሚፈታ ገልጾዋል።

በአፋር ክልል በተቀሰቀሰ ተቃውሞ ከእሑድ ጥር 5 ቀን 2011 ዓ.ም. ጀምሮ የጂቡቲ መስመር ለሁለት ቀናት ያህል በመዘጋቱ፣ 1,000 የሚሆኑ የነዳጅ ማመላለሻ ተሽከርካሪዎች ወደ መሀል አገር የሚያደርጉት ጉዞ ተስተጓጉሏል። ከጂቡቲ የሚመጡ ብቻ ሳይሆን ወደ ጂቡቲም የሚጓዙ ተሽከርካሪዎች ለመቆም ተገደው ነበር። በአጠቃላይ የጭነት ተሽከርካሪዎች የአፋር ክልልን ለማቋረጥ ተቸግረው ቆይተዋል።

በድሬዳዋ በኩል የገቡትም የተወሰኑ ነዳጅ አመላላሽ ተሽከርካሪዎች ሰኞ ጥር 6 ቀን 2011 ዓ.ም. አዋሽ ላይ መንገድ ስተለዘጋባቸው መሻገር አልቻሉም። በዚህ ምክንያት ቤንዚን፣ ናፍጣና የአውሮፕላን ነዳጅ የጫኑ 1,000 ያህል ተሽከርካሪዎች በተለያዩ ቦታዎች ቆመው እንደነበር ለማወቅ ተችሏል።

የኢትዮጵያ ነዳጅ አቅራቢ ድርጅት ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ታደሰ ኃይለ ማርያም ለሪፖርተር እንደተናገሩት፣ በአፋር ክልል የተዘጉት ዋና ዋና መንገዶች ሰኞ ጥር 6 ቀን 2011 ዓ.ም. በመከፈታቸው የነዳጅ ማመላለሻ ተሽከርካሪዎች ጉዟቸውን ቀጥለዋል። “የቆሙት የነዳጅ ማመላለሻ ተሽከርካሪዎች ብቻ ሳይሆኑ የደረቅ ጭነት ማመላለሻ ተሽከርካሪዎች ጭምር በመሆናቸው፣ መንገድ ላይ የትራፊክ መጨናነቅ ስለሚኖር አዲስ አበባ ለመድረስ አንድ ሁለት ቀን ይፈጅባቸዋል። ከማክሰኞ ጥር 7 ቀን 2011 ዓ.ም. ጀምሮ አዲስ አበባ መግባት ስለሚጀምሩ የተፈጠረው የነዳጅ እጥረት ይቀረፋል። ወደ ክልል ከተሞች እስኪደርሱ ሁለትና ሦስት ቀናት ሊፈጅ ይችላል። በክልል ከተሞች የተፈጠረው የነዳጅ እጥረት በሳምንቱ መጨረሻ ይፈታል። በአዲስ አበባ ግን ከረቡዕ ጥር 8 ቀን 2011 ዓ.ም. ጀምሮ ይረጋጋል፤” ብለዋል።

ባለፈው ሳምንት በአማራ ክልል በምዕራብ ጎንደር ዞን በተፈጠረ ግጭት ሳቢያ ከሱዳን ወደ ኢትዮጵያ ነዳጅ የሚያመላልሱ የነዳጅ ማመላለሻ ተሽከርካሪዎች መተማ ከተማ ለመቆም መገደዳቸው ይታወሳል። በምዕራብ ጎንደር ዞን በተፈጠረው የፀጥታ ሥጋት 70 ያህል ቤንዚን የጫኑ የነዳጅ ማመላለሻ ተሽከርካሪዎች መተማ ከተማ እንደቆሙ ታውቋል። ቤንዚን ለማምጣት ወደ ሱዳን የሚጓዙ ተሽከርካሪዎች በተመሳሳይ ችግር መጓዝ ባለመቻላቸው፣ ከሱዳን የሚገባው የቤንዚን ምርት ሙሉ በሙሉ ተቋርጧል።

የኢትዮጵያ ነዳጅ ማመላለሻ ተሽከርካሪዎች ቤንዚን የሚቀዱት ከካርቱም 60 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ ከሚገኘው ጌሊ የነዳጅ ማጣሪያ ነው። የሱዳን ፔትሮሊየም ኮርፖሬሽን በኢትዮጵያ ተሽከርካሪዎች እስከ ጥር 6 ቀን 2001 ዓ.ም. ሲጭን የነበረ ቢሆንም፣ ከጥር 7 ቀን 2011 ዓ.ም. ጀምሮ ተሽከርካሪ ማግኘት አልቻለም።

የተዘጋው የመተማ መንገድ ከረቡዕ ጥር 8 ቀን 2011 ዓ.ም. ጀምሮ የሚከፈት በመሆኑ፣ የተከሰተው የቤንዚን እጥረት በጥቂት ቀናት ውስጥ እንደሚፈታ አቶ ታደሰ ተናግረዋል። “ከሱዳን በአሁኑ ወቅት የምናስገባው ቤንዚን የፍጆታችንን 20 በመቶ በመሆኑ ያን ያህል የጎላ ተፅዕኖ አይኖረውም። ዋናው ነገር 80 በመቶ የቤንዚን ፍጆታችን የሚገባው ከጂቡቲ ወደብ በመሆኑ የአፋር ክልል መንገዶች መከፈታቸው ነው፤” ያሉት አቶ ታደሰ፣ የነዳጅ እጥረቱ በጥቂት ቀናት ውስጥ እንደሚፈታ ያላቸውን እምነት ገልጸዋል።

“ችግሩ ሊከሰት የቻለው በጊዜያዊ የፀጥታ ችግር ነው። የነዳጅ ምርት አቅርቦት ወይም የግዥ ችግር የለም። የተዘጉት መንገዶች በመከፈት ላይ በመሆናቸው የቆሙት ተሽከርካሪዎች እስኪደርሱ ለሁለትና ለሦስት ቀናት ችግር ሊኖር ይችላል። ነገር ግን ኅብረተሰቡ በጥቂት ቀናት ውስጥ የሚፈታ ጊዜያዊ ችግር መሆኑን ተረድቶ መረጋጋት ይኖርበታል። በእርግጠኝነት ችግሩ እስከ ሐሙስና ዓርብ እንደሚፈታ መናገር ይቻላል፤” ብለዋል።

ከሱዳን የሚገባው ቤንዚን በአብዛኛው የሚከፋፈለው በአማራ ክልል ውስጥ በመሆኑ፣ በአዲስ አበባ ከተማ ላይ የጎላ ተፅዕኖ እንደማይኖረው ምንጮች ለሪፖርተር ተናግረዋል።

አዲስ አበባ ውስጥ ሪፖርተር ያነጋገራቸው የነዳጅ ማደያ ባለቤቶች የአፋር ክልል መንገድ በመከፈቱ፣ ነዳጅ የጫኑ ተሽከርካሪዎች ይገባሉ ተብለው በመጠባበቅ ላይ እንደሆኑ ገልጸዋል።

(ፎቶ፤ ከኦይል ሊቢያ የነዳጅ ማደያዎች በአንደኛው ቤንዚን እንደሌለ በጽሑፍና በነዳጅ ቀጂ ሠራተኛ ጭምር ሲገለጽ)

ጎልጉል፤ የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • “ሚካኤል ችግኝ ነው። … ችግኝ ይተክላል” ቴዲ አፍሮ June 29, 2022 03:30 am
  • “የእኔን ልጆችና የልጅ ልጆች (22ቱንም) የቀበርኩት እኔ ነኝ” አቶ መሀመድ የሱፍ ከምዕራብ ወለጋ June 28, 2022 01:07 pm
  • የገዳ ሥርዓት እና የኦሮሞ ገዢ መደብ June 20, 2022 11:34 pm
  • “የወልቃይትን ጉዳይ ለድርድር የማናቀርበው ቀይ መስመራችን ነው” ርዕሰ መስተዳድር ይልቃል June 12, 2022 07:09 pm
  • የሰሜን ምዕራብ ዕዝና የአማራ ልዩ ኃይል ተከዜ ክፍለ ጦር ዕውቅናና ሽልማት ተሰጣቸው June 12, 2022 06:21 pm
  • ሀገር በቀል ባህላዊ የግጭት አፈታቶችን በተገቢው በመጠቀም ዘላቂ እርቅና ሰላምን ማምጣት ይቻላል June 12, 2022 05:40 pm
  • የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን በገረጂና በቀበና ያስገነባቸውን የመኖሪያ አፓርትመንቶች አስመረቀ June 12, 2022 05:35 pm
  • በኦነግ ሸኔ ፈርሶ የነበረውና ወታደራዊ ጠቀሜታ ያለው ድልድይ ተጠግኖ አገልግሎት መስጠት ጀመረ June 10, 2022 09:13 am
  • ጃዋር በዳውድ ኢብሣ ቀይ መስመር ተሰመረለት June 8, 2022 12:59 pm
  • ወልቃይት: ቢመረንም ለመዋጥና ራሳችንን ለመመልከት እንሞክር June 8, 2022 11:53 am
  • እብድ ይሻለዋል እንጂ አይድንም፤ ሐጂ ጃዋር አሁን ለምን ብቅ አለ? June 8, 2022 05:59 am
  • ሕዝብ ድምፅ የነፈጋቸው “ፓርቲዎች” የሽግግር መንግሥት ይቋቋም አሉ June 7, 2022 01:11 am
  • “አድጌ እንደናንተ መሆን እፈልጋለሁ” June 5, 2022 06:58 pm
  • በሳምንት ለ100 ያህል ሕሙማን አገልግሎት የሚሰጥ የኩላሊት ዕጥበት ማዕከል ሥራ ጀመረ May 30, 2022 02:20 am
  • የጥቁር አንበሳ ዕጩ መኮንኖች (ካዴቶች) ተመረቁ May 29, 2022 04:01 pm
  • “ኢትዮጵያን መንካት አይቻልም!!” በሚል ቁጭት ነው እየሠራን ያለነው May 29, 2022 01:04 pm
  • “ከሞፈርና ቀንበር ወደ ትራክተር” በሚል መርህ ለአማራ ገበሬዎች የግብርና ሜካናይዜሽን ተሰጠ May 29, 2022 02:02 am
  • ኢትዮ 360 “የወያኔ፣ የጁንታ ሚዲያ ነው” – ባለከዘራው ጄኔራል May 27, 2022 02:51 am
  • “እኛ የምናውቀው ነገር የለም፤ የሚያጣሉን ፖለቲከኞች ናቸው” የአማራ ወዳጃቸውን አደራ ቤት የመለሱ የቅማንት ተወላጅ May 27, 2022 01:40 am
  • ትግራይን አገር እናደርጋለን፤ “በውይይት እና በጦርነት” ሁሉንም ጉዳይ እንቋጫለን – የወንበዴው መሪ ደብረጽዮን May 26, 2022 09:18 am
  • “ሁለቱ የምዕራብ ዕዝ ተዋጊ ዶክተሮች” May 26, 2022 08:19 am
  • ወደ ትህነግ ሊተላለፍ የነበረ አምስት ሚሊዮን ብር ከ20 ተጠርጣሪዎች ጋር ተያዘ May 25, 2022 01:57 am
  • የጦርነቱ ስትራቴጂያዊ እውነታዎች May 19, 2022 09:37 am
  • በጦርነቱ የተጎዱ አካባቢዎችን ለማቋቋም የሚውል የ15 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር ድጋፍ የዓለም ባንክ May 16, 2022 10:22 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2022 · Goolgule