• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

በኢትዮጵያ 36 ሚሊዮን የሚጠጉ ህጻናት በድህነት ደረጃ ላይ ናቸው

January 22, 2019 02:30 am by Editor Leave a Comment

በድርብ አኻዝ በከፍተኛ ፍጥነት ዕድገት ላይ ነች እየተባለ ሲደሰኮርባት በነበረችው አገር በቅርቡ ይፋ የተደረገ ጥናት እንደጠቆመው ሰላሣ ስድስት ሚሊየን የሚጠጉ ህፃናቶቿ ዘርፈብዙ በሆነ መልኩ ድሃ መሆናቸው ተነገረ። ይህም ማለት ህፃናቱ ለመኖር የሚያስፈልጓቸው መሠረታዊ አገልግሎቶችን እንኳን ማግኘት ብርቅ ሆኖባቸዋል ነው ጥናቱ ያለው።

በኢትዮጵያ ከ18 አመት በታች ከሆኑት ከ41 ሚሊየን ውስጥ 36 ሚሊዮኑ በድህነት ውስጥ እንዳሉ የስታቲስቲክ ኤጀንሲ እና ዩኒሴፍ ጥናት አስረድቷል።

ጥናቱ በተለያዩ ዘጠኝ ክፍሎች ተለይቷል። ድህነቱ በዕድገት፣ በምግብ፣ በጤና፣ በውሃ፣ በንፅህና እና በመጠለያ ሲሆን ሌሎቹ የድህነት መለኪያ መስፈርቶች ደግሞ ትምህርት፣ ከጤና ጋር በተያያዘ በቂ ዕውቀት፣ መረጃና ተሳትፎን የሚጨምር ነው ተብሏል።

በጥናቱ እንደተገለጸው 88 በመቶ የሚሆኑት ዕድሜያቸው ከ18ዓመት በታች የሆኑት (36 ሚሊዮን) ልጆች ከዘጠኙ መለኪያዎች በተለይ በመጠለያና በንጽህና ጉዳይ ከፍተኛ ዕጥረት ያለባቸው እንደሆነ ነው። ከዚህ በተጨማሪም ከኢትዮጵያ የጂኦግራፊያዊ አቀማመጥ አንጻር በገጠር የሚኖሩት በከፍተኛ ሁኔታ የችግሩ ሰለባ መሆናቸውን ነው ጥናቱ የጠቆመው። ይህም ማለት በገጠር ከሚኖሩት 94 በመቶ የሚሆኑት ዘርፈብዙ በሆነው ድህነት የተጠቁ ሲሆን በከተሞች ግን ቁጥሩ 42 በመቶ ነው ተብሏል።

በክልል ደረጃ ከታየ በአዲስ አበባ ያለው የህጻናት ድህንት መጠን 18 በመቶ ሲሆን በአፋር፣ በአማራና በደቡብ ሕዝብ 91 በመቶ፣ በኦሮሚያና በሶማሊ 90 በመቶ ሲሆን በቤንሻንጉል ጉሙዝ ደግሞ 89 በመቶ በዘገባው ተጠቅሷል።

በአጠቃላይ ኢትዮጵያ ሁሉም መሠረታዊ መሥፈርቶች የተሟሉላቸው ህጻናት ቁጥር 1 በመቶ መሆኑን ዘገባው አትቷል።

ይህንኑ የከፋ የህፃናቱን ድህነት ለመቀነስና መላ ለማለትም መንግስት የበጎ አድራጎት ድርጅቶችና የሚመለከታቸውም በሙሉ ጉዳዩ በጣም ትኩረት የሚያስፈልገው እንደሆነ አውቀው በርትተው መሥራት እንዳለባቸው ጥናቱን ያወጣው ድርጅት አስረድቷል።

ጎልጉል፤ የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ጎርጎራ – የመጻዒው ዘመን ሙሽራ! የዉበት ፈርጥ! January 17, 2023 04:18 pm
  • ሁለተኛው መስቀል አደባባይ January 17, 2023 04:13 pm
  • በአቡዳቢ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን January 17, 2023 04:08 pm
  • በንፋስ ስልክ ላፍቶ ስምንት የመሬት ሌቦች ተያዙ January 16, 2023 11:36 am
  • ሺሻ ሲያስጨሱ በተገኙ ሆቴሎችና የምሽት ጭፈራ ቤቶች ላይ እርምጃ ተወሰደ January 16, 2023 08:50 am
  • በሐሰተኛ መታወቂያ የደኅንነት አባል ነን ብለው ሲያጭበረብሩ የነበሩ ተያዙ January 13, 2023 02:03 pm
  • ተሽከርካሪ ወንበር ለትግራይ – “ናይ ኣካል ጉዱኣት ተሽከርካሪ ዘለዎ ወንበር” January 12, 2023 07:17 pm
  • የአማራው ኩራት፣ የኢትዮጵያ ዘብ፣ የትህነግን ቅስም ሰባሪ! January 12, 2023 04:00 pm
  • በኢትዮጵያ ላይ የተጣሉ ማዕቀብ እና ሌሎች አስገዳጅ ሕጎች ሙሉ ለሙሉ ተሰረዙ January 12, 2023 01:52 pm
  • የቻይና ዕዳ ስረዛ “Payday Loan Diplomacy” ወይስ ኢትዮጵያን ያዳነ ተግባር? January 12, 2023 11:00 am
  • የአዲስ አበባ አስተዳደር ከቋንቋ ጋር በተያያዘ ውሳኔ አስተላለፈ January 12, 2023 10:46 am
  • “አምባሳደሩ” የቀድሞ ጌቶቻቸውን እንዲያቋቁሙ ተሾሙ January 11, 2023 03:47 pm
  • መከላከያ ሸኔን የሚዋጉ ሚሊሻዎችን አሠልጥኖ አስመረቀ January 10, 2023 05:37 pm
  • በሰባት ተጠርጣሪዎች ላይ ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመሰረተ January 10, 2023 03:36 pm
  • የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ አቅጣጫ January 6, 2023 03:26 pm
  • “ከዕብሪቱ አስተንፍሰነዋል” – ኢሳያስ January 2, 2023 07:29 pm
  • [ኢትዮጵያን] “አስታክኮ ኤርትራን መውጋት ለሚፈልግ ኃይል አንተባበርም” January 2, 2023 07:11 pm
  • የ፰ ወር ሕጻንና ጨቅላ ወንዶች የሚደፈሩባት ትግራይ December 14, 2022 02:49 pm
  • “ሰውን ለመርዳት ሰው መሆን ብቻ በቂ ነው” የደጎች አውራ የመቄዶኒያው ቢንያም በለጠ December 14, 2022 09:59 am
  • “የሀብት ምዝገባ መረጃው ለሕዝብ ክፍት ይደረግ “ December 13, 2022 10:30 am
  • የኢትዮጵያ ዓለምአቀፋዊ የሌብነት ደረጃ December 13, 2022 09:42 am
  • ለብረት አቅላጮች ለመሸጥ በኤሌክትሪክ የብረት ማማዎች ስርቆት የ100 ሚሊዮን ብር ኪሳራ December 13, 2022 09:26 am
  • በትግራይ የሰላም ስምምነቱን መሠረት ያደረገ የሽግግር ፍትሕ እንደሚፈጸም ተገለጸ December 13, 2022 09:20 am
  • ከ30 ሚሊየን ብር በላይ በሚሆን ሌብነት የተከሰሱት የደኅንነት መ/ቤት ሠራተኞች ክስ ተመሰረተ December 13, 2022 09:06 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule