• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

በኢትዮጵያ 36 ሚሊዮን የሚጠጉ ህጻናት በድህነት ደረጃ ላይ ናቸው

January 22, 2019 02:30 am by Editor Leave a Comment

በድርብ አኻዝ በከፍተኛ ፍጥነት ዕድገት ላይ ነች እየተባለ ሲደሰኮርባት በነበረችው አገር በቅርቡ ይፋ የተደረገ ጥናት እንደጠቆመው ሰላሣ ስድስት ሚሊየን የሚጠጉ ህፃናቶቿ ዘርፈብዙ በሆነ መልኩ ድሃ መሆናቸው ተነገረ። ይህም ማለት ህፃናቱ ለመኖር የሚያስፈልጓቸው መሠረታዊ አገልግሎቶችን እንኳን ማግኘት ብርቅ ሆኖባቸዋል ነው ጥናቱ ያለው።

በኢትዮጵያ ከ18 አመት በታች ከሆኑት ከ41 ሚሊየን ውስጥ 36 ሚሊዮኑ በድህነት ውስጥ እንዳሉ የስታቲስቲክ ኤጀንሲ እና ዩኒሴፍ ጥናት አስረድቷል።

ጥናቱ በተለያዩ ዘጠኝ ክፍሎች ተለይቷል። ድህነቱ በዕድገት፣ በምግብ፣ በጤና፣ በውሃ፣ በንፅህና እና በመጠለያ ሲሆን ሌሎቹ የድህነት መለኪያ መስፈርቶች ደግሞ ትምህርት፣ ከጤና ጋር በተያያዘ በቂ ዕውቀት፣ መረጃና ተሳትፎን የሚጨምር ነው ተብሏል።

በጥናቱ እንደተገለጸው 88 በመቶ የሚሆኑት ዕድሜያቸው ከ18ዓመት በታች የሆኑት (36 ሚሊዮን) ልጆች ከዘጠኙ መለኪያዎች በተለይ በመጠለያና በንጽህና ጉዳይ ከፍተኛ ዕጥረት ያለባቸው እንደሆነ ነው። ከዚህ በተጨማሪም ከኢትዮጵያ የጂኦግራፊያዊ አቀማመጥ አንጻር በገጠር የሚኖሩት በከፍተኛ ሁኔታ የችግሩ ሰለባ መሆናቸውን ነው ጥናቱ የጠቆመው። ይህም ማለት በገጠር ከሚኖሩት 94 በመቶ የሚሆኑት ዘርፈብዙ በሆነው ድህነት የተጠቁ ሲሆን በከተሞች ግን ቁጥሩ 42 በመቶ ነው ተብሏል።

በክልል ደረጃ ከታየ በአዲስ አበባ ያለው የህጻናት ድህንት መጠን 18 በመቶ ሲሆን በአፋር፣ በአማራና በደቡብ ሕዝብ 91 በመቶ፣ በኦሮሚያና በሶማሊ 90 በመቶ ሲሆን በቤንሻንጉል ጉሙዝ ደግሞ 89 በመቶ በዘገባው ተጠቅሷል።

በአጠቃላይ ኢትዮጵያ ሁሉም መሠረታዊ መሥፈርቶች የተሟሉላቸው ህጻናት ቁጥር 1 በመቶ መሆኑን ዘገባው አትቷል።

ይህንኑ የከፋ የህፃናቱን ድህነት ለመቀነስና መላ ለማለትም መንግስት የበጎ አድራጎት ድርጅቶችና የሚመለከታቸውም በሙሉ ጉዳዩ በጣም ትኩረት የሚያስፈልገው እንደሆነ አውቀው በርትተው መሥራት እንዳለባቸው ጥናቱን ያወጣው ድርጅት አስረድቷል።

ጎልጉል፤ የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am
  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule