• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“እንጨርሳቸው፤ አንድም አኙዋክ መትረፍ የለበትም” የሚለውን የህወሓት ትዕዛዝ ተፈጻሚ ያደረገው ኦሞት ኦባንግ ሞቷል

November 24, 2018 10:07 am by Editor Leave a Comment

በወንበዴው የህወሓት ቡድን ትዕዛዝ 424 አኙዋኮችን የጨፈጨፈው ኦሞት ኡባንግ ኡሎም ያለፈው ሳምንት መጨረሻ አካባቢ መሞቱ ታውቋል።

ከመለስ ዜናዊ ትዕዛዝ በመቀበል ለ424 የአኙዋክ ተወላጆች የግፍ ዕልቂት ተጠያቂ የነበረው ኦሞት ኦባንግ በስደት በሚገኝበት ፊሊፒንስ ሞቷል። የሞቱ ምክንያት ኤችአይቪ ኤድስ ሊሆን ይችላል የሚል ግምት አለ።

ኦሞት ኦባንግ የዛሬ 15 ዓመት አካባቢ በታኅሳስ ወር ከህወሓት ሹሞች ቀጥተኛ ትዕዛዝ በመቀበል ጭፍጨፋውን በፈጸመበት ወቅት የክልሉ የፀጥታና ደኅንነት ኃላፊ ነበር። ለዚህም ኢሰብዓዊ ድርጊቱ ሽልማት ይሆን ዘንድ የወንበዴው ህወሓት መሪዎች የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አድርገው ሾመውታል።

ጋምቤላን እንደፈለገ ሲፈነጭባት የኖረው ኦሞት ከታህሳስ 23 ቀን 2004 ዓም ጀምሮ ሞት እንደ ቡሽ ክዳን ያስፈነጠረው መለስ ዜናዊ በላከው አስገምጋሚዎች ለሳምንት በጋምቤላ በተካሄደ አውጫጪኝ “የአኙዋክ ተወላጆችን አስጨፍጭፈሃል” የሚል መነሻውና ዓላማው ግልጽ ያልሆነ ጥያቄ ቀርቦለት ነበር። በወቅቱ ግምገማው ላይ የነበሩ እንዳሉት ለዚህ ጥያቄ ኦሞት “እኔ በዚህ ጉዳይ ተጠያቂ ከሆንኩ መሳሪያና ወታደር የሰጠኝ መለስም ይታሰራል” በማለት መልስ ሰጥቶ ነበር።

ከዚህ ቁርሾ በኋላ ወደ ፌዴራል መንግሥት ሥራ እንዲዛወር ተደርጎ አዲስ አበባ ከመጣ በኋላ በፌዴራል ጉዳዮች ውስጥ ኃላፊነት ተሰጥቶት ነበር።

በቀጣይም ህወሓቶች ለእስር ሲፈልጉት አምልጦ ከኮበለለ በኋላ እስከ ዕለተ ሞቱ ድረስ በፊሊፒንስ ተደብቆ ኖሯል። በዚያም እያለ ህወሓትን አጋልጣለሁ በሚል ሰበብ፤ ወደ ተቃዋሚው ጎራ ለመግባት በመከጀል ወደ ሚዲያ ብቅ ማለቱ ይታወሳል። የአኙዋክ የፍትሕ ምክር ቤት ይህንን ተቃውሞ መግለጫ መስጠቱ ይታወቃል።

ያለፈው ሳምንት ውስጥ ለኅልፈተ ሞት የበቃው ኦሞት አስከሬኑን ወደ ኢትዮጵያ በመላክ እዚህ እንዲቀበር ለማድረግ ለውጭ ጉዳይ ሚ/ር ጥያቄ የቀረበ ሲሆን እስካሁን ምላሽ አለመገኘቱን ጎልጉል ለመረዳት ችሏል። ከኢትዮጵያ መንግሥት በኩል ምላሽ ካልተሰጠ የፊሊፒንስ መንግሥት የኦሞትን አስከሬን ከዚህ በላይ ማቆየት ስለማይችል እንደሚያቃጥለው የተገኘው መረጃ ይጠቁማል።

ከዚሁ ጋር በተያያዘ ለጎልጉል የደረሰው የኦሞት አስከሬን ፎቶ ለሕዝብ መቅረብ የሌለበት ስለሆነ ሳናትመው ትተነዋል። ሆኖም ግን ግለሰቡ ከመሞቱ በፊት ማንነቱ እስከሚቀየር ድረስ በከፍተኛ ሁኔታ የተበለሻ (ዲፎርምድ የሆነ) መሆኑን ለመረዳት ችለናል።

ኦሞት ከዚህ ዓለም ቢያልፍም ለአኙዋኮች ጭፈጨፋ ትዕዛዝ በመስጠቱ ውስጥ ቀትተኛ ተሳትፎ የነበራቸው እስካሁን በቁጥጥር ሥር አልዋሉም። በዚህ ጉዳይ ላይ ጎልጉል ከሠራቸው በርካታ የዜና ዘገባዎች መካከል “እንጨርሳቸው፤ አንድም አኙዋክ መትረፍ የለበትም” በሚል ርዕስ የዛሬ አንድ ዓመት አካባቢ (December 13, 2017) የዘገብነውን በድጋሚ ከዚህ በታች አትመነዋል።

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

“እንጨርሳቸው፤ አንድም አኙዋክ መትረፍ የለበትም”

• እነዚህም የህወሓት ነፍሰበላዎች ይፈለጋሉ!

የሰላም ሰዎች የሆኑት አኙዋኮች ከህወሓት ጋር መቃቃር ውስጥ የገቡት ገና ከጅምሩ ነበር። የቀድሞው የአኙዋክ ምክርቤት ኃላፊ የነበሩት አቶ ኦባንግ ሜቶ እንደሚሉት ችግሩ የተያያዘው ህወሓት የጋምቤላን ለም ምድር የራሱ ለማድረግ ከመፈለጉ ጋር ነው። ህወሓት ሥልጣን ላይ እንደተቆናጠጠ የጋምቤላን ብቸኛ ጄኔሬተር በመንቀል ከመውሰድ አልፎ በአሎሮ ግድብ ላይ የነበሩትን ወደ 400 የሚሆኑ ማሽነሪዎች እና የእርሻ መሣሪዎች በምሽት ወደ ትግራይ ነቅሎ ወስዷል ይላሉ አቶ ኦባንግ። በመቀጠልም ተዝቆ የማያልቀውን የጋምቤላን ድንቅ ሃብት በረኸኞቹ ህወሃቶች ለመዝረፍ ውሳኔያቸው አደረጉ።

“መሬቴን አላስነካም” በሚለው አኙዋክና ህወሓት መካከል ያለውን መቃቃር አንድ “ዕልባት” ላይ ለማድረስ በሚል አኙዋክን ማጥፋት የህወሓት ቀዳሚ ሃሳብ ሆነ እንደ አቶ ኦባንግ ሜቶ ገለጻ። ጉዳዩን አቅጣጫ ለማስቀየርም ከዚህ በፊት ተነስተው የማያውቁ የጎሣ ግጭቶችን ህወሃት መቆስቆስ ጀመረ። ሸመጋይ መስሎም የመከላከያ ሠራዊት በቦታው ማስፈር ተግባሩ አደረገ። በመጨረሻም “እንጨርሳቸው፤ አንድም አኙዋክ መትረፍ የለበትም” የሚለው ትዕዛዝ ወጣ። “Let us kill them all! From today forward there will be no Anuak! There will be no more Anuak land! No one will arrest us! Erase the trouble makers!”

መለስ በመራው ስብሰባ ላይ፤

አዲሱ ለገሰ፣

ስብሃት ነጋ፣

በረከት ስምዖን፣

ኦሞት ኡባንግ ኡሎም (ያኔ የጋምቤላ ደኅንነት ኃላፊ)፣

አባይ ጸሃዬ፣

ሳሞራ ዩኑስ፣

ዮሐንስ ገብረመስቀል (ያኔ የወታደራዊ ስለላ ኃላፊ)፣

አባዱላ ገመዳ ተገኝተዋል።

የዕቅዱ አፈጻጸም ላይ አኙዋኮች እንዲጨፈጨፉ ቀጥተኛ ትዕዛዝ የሰጠው ጸጋይ በየነ (በጋምቤላ የሠራዊቱ ኃላፊ) ሲሆን ፈቃዱ ያገኘው ያኔ የፌዴራል ጉዳይ ኃላፊ ከነበረው ገብረአብ በርናባስ ነበር። የፖሊስ ኃላፊው ታደሰ ኃይለሥላሴም አኙዋኮችን የማስገደል ትዕዛዝ በመስጠቱ ውስጥ ነበረበት። ይህ ሁሉ በማስረጃ የተረጋገጠ መሆኑን አቶ ኦባንግ ያስረዳሉ።

“እንግዲህ ይህ ዘር የማጽዳት ዘመቻ በ1996 ከተካሄደ በኋላ የጋምቤላ መሬት እንደ ካሩቱሪና ሳውዲ ስታር ላሉ ባለሃብቶች በአንድ ዶላር ሒሳብ የተቸበቸበው። ብዙ ጊዜ ለውጭ ባለሃብት ተሰጠ ይባላል እንጂ ከጋምቤላ መሬት 78 በመቶውን የተቀራመቱት ትግሬዎች ሲሆኑ 12 በመቶው ብቻ ነው ለውጭ ባለሃብቶች የተሰጠው። ከዚህ ሌላ ይህ ሁሉ መሬትና ብድር ለትግራይ ተወላጆች ተሰጥቶ የእርሻ ልማት ባለቤቶች ሲሆኑ አንድም አኙዋክ ይህንን ዕድል አላገኘም፤ ይልቁንም ለውሃ ቅርብ የነበሩና በአባቶቻቸው መሬት ላይ የሚገኙትን አኙዋኮች በልማት ሰበብ በህወሃት ተፈናቅለው ወደ ሌላ ቦታ ሰፍረዋል” በማለት ኦባንግ ይናገራሉ።

ኦሞት ኦባንግ ኡሎም ከአገር ኮብልሎ ከመውጣቱ በፊት ከሙስና ጋር በተያያዘ ወንጀለኛ እንደሆነ ሲነገረው “እኔ ከተወነጀልኩና ከታሰርኩ ከእኔ ጋር አዜብ መስፍን አብራ መታሠር አለባት” ማለቱ ይታወሳል።

ከታህሳስ 23 ቀን 2004 ዓ ም ጀምሮ ሟቹ መለስ ዜናዊ በላከው አስገምጋሚዎች ለሳምንት በጋምቤላ በተካሄደ አውጫጪኝ ኦሞት ኦባንግ ኡሎም “የአኙዋክ ተወላጆችን አስጨፍጭፈሃል” የሚል መነሻውና ዓላማው ግልጽ ያልሆነ ጥያቄ ቀርቦለት ነበር። በወቅቱ ግምገማው ላይ የነበሩ እንዳሉት ለዚህ ጥያቄ ኦሞት “እኔ በዚህ ጉዳይ ተጠያቂ ከሆንኩ መሳሪያና ወታደር የሰጠኝ መለስም ይታሰራል” በማለት መልስ ሰጥቶ ነበር።

አስራ አራት ዓመት ቢያልፍም፤ መለስም ወደ ከርሰ መቃብር እንደ ቡሽ ክዳን ተስፈንጥሮ ቢወርድም፤ ኦሞትም ሆነ የህወሓት ነፍሰበላዎች አሁንም ይፈለጋሉ! (ቀን ጠብቆ ኦሞትም ወደማይመለስበት ከነወንጀሉ አሸልቧ)


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ ንብረት ናቸው። ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን።

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News Tagged With: Anuak Massacre, Full Width Top, meles zenawi, Middle Column, omot obang, tplf

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule