• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የኢትዮጵያ ህዝብ ፍርድህ ምንድነው?

September 15, 2014 01:20 am by Editor 2 Comments

ከአኝዋክ ጀስቲስ ካውንስል የተሰጠ መግለጫ  

Anuak-Justice-Councilየህወሃት ፍጹም ታማኝ ነበር። በተለያዩ ሃላፊነቶች በህጻናት፣ በወንድሞቹ፣ በእህቶቹ፣ በእናቶቹ፣ በአባቶቹ አጠቃላይ በኢትዮጵያ ህዝብ ላይ በሰራው ወንጀል በህግ ይፈለጋል፣ በህግ የሚፈልጉት ኢትዮጵያዊያን ብቻ ሳይሆኑ ዓለም አቀፍ የፍትህና የመብት ተሟጋቾች ናቸው። ህወሃትን ክዶ በስደት ከሚገኝበት አገር እጁን እንዲሰጥ ጥሪ ቀርቦለታል። ይህ “ሰው” በጋምቤላ ክልል የፖሊስና የጸጥታ ሃላፊ የነበረ። የደህንነት አመራር ነበረ። ክልሉን በፕሬዚዳንትነት ለዓመታት የመራ፣ በጅምላ ለተጨፈጨፉት የአኝዋክ ንጹሃን ደም ቀዳሚ ተጠያቂ ነው – ኦሞት ኦባንግ !!

ኦሞት በዴሰምበር 13/2003 በጅምላ ጄኖሳይድ ለተፈጸመባቸው ከ424 በላይ የአኝዋክ ንጹሃን ዜጎች፣ በአስር ሺህ የሚቆጠሩ ዜጎች ስደት፣ መሬታቸው በግፍ ለተነጠቁና በጠመንጃ ለተፈናቀሉ ዜጎች ግንባር ቀደም ተጠያቂ መሆኑን ከአገራችን የቀበሌ ነዋሪ ጀምሮ እስከ ዓለም አቀፍ ደረጃ በማስረጃ የሚታወቅ ነው። ኦሞት በጋምቤላ ለፈሰሰው የንጹሃን ደም “ነጻ” ሊሆን የሚችልበት አንድም አግባብ የለም። ድርጅታችን አኙዋክ ጀስቲስ ኦሞትን ፍትህ አደባባይ እንደሚያቆመው ቅንጣት ያክል የማይጠራጠረውም ለዚህ ነው። ከተሰወረበት ፊሊፒንስ አድኖ ለመያዝ አስፈላጊው ስራ እየተሰራ ነው።

ጄኖሳይድ ዎች፣ የሂውማን ራይትስ ዎችና ከአኝዋክ ጀስቲስ ጋር አብረው ሲሰሩ የነበሩት የአይሲሲ /የዓለም አቀፉ የወንጀለኞች ፍርድ ቤት ጠበቆች/ በጋራ ኦሞት ኦባንግን ህግ ፊት ለማቅረብ እየሰሩ ነው። ኦሞት ከተሸሸገበት ፊሊፒንስ ወጥቶ ህግ ፊት እንዲቀርብ የሚደረገው ግፊት ባየለበት በአሁኑ ሰዓት የኦሞት አደባባይ ወጥቶ “ታግሎ አታጋይ” ለመሆን መወሰኑ ዜና የሆነበት ምክንያት አልገባንም።

omot wanted“የኢትዮጵያ ህዝብ ፍረድ፣ ፍርድህ ምንድን ነው?” ብለን ስንጠይቅ በህዝብ ዘንድ ያለውን የፍትህ ጥማት ዘንግተን አይደለም። እንደ ኦሞት አይነት በደምና በሙስና የተጨማለቀ ሰው ራሱን ነጻ ለማድረግ የሚናዘዘውን ኑዛዜ በጥንቃቄ እንድትመለከቱት ስለምንፈልግ ነው። ኦሞት ለኢሳት ከሰጠው መግለጫ ላይ ተቀንጭቦ “በሰበር ዜና” በተላለፈው መልዕክት “ኦሞት ወያኔን ለመታገል መወሰኑንና፣ በአኝዋክ ንጹሃን ዜጎች ላይ የተፈጸመውን ጭፍጨፋ አስመልከቶ ወንጀሉን የፈጸሙትን ክፍሎች ዝርዝር ሰጥተዋል” መባሉን ሰምተናል።

ኦሞት ኦባንግ ከክልል ፕሬዚዳንትነቱ ተነስቶ ወደ ፌዴራል ጉዳዮች ሚኒስትር ደዔታነት ከተዛወረ በኋላ አገር ጥሎ እንደኮበለለ አስቀድሞ ሊያነጋግረን ሞክሮ ነበር። ወያኔንን ለመታገል መወሰኑን ገልጾልን ነበር። አስፈላጊውን መረጃ ለመስጠት ተማጽኖንን ነበር። በዓለም ዓቀፍ ደረጃ የተመሰረተበትን ክስ እንድናጠራለት/ነጻ እንድናደርገው ሊማጸነን ሞክሮ ነበር። እኛ ግን እሱን ህግ ፊት ከማቅረብ የዘለለ ሃሳብና ፍላጎት ስላልነበረን “እጅህን ለፍትህ ስጥ” የሚል መልስ ነበር የመለስንለት። “የዓለም ዓቀፉ የወንጀለኞች ፍርድ ቤት ቀርበህ ተናዘዝ” ነበር ያልነው።

ትናንት በወገኖቹ ደም አጥንት ላይ ቆሞ ሲደንስ፣ በኢህአዴግ መገናኛዎች ላይ የወገኖቹን ነፍስ ሲረግም የነበረ ወንጀለኛ በየትኛውም መስፈርት ለወገኖቹ ነጻ መሆን ይታገላል ብለን አናምንም። መታገልም ከፈለገ ራሱን ቅድሚያ ህግ ፊት አቅርቦ ነጻ ሊያደርግ ይገባል የሚል አቋም አለን። ትግል የሚመራው ስብዕና ባላቸውና በህዝብ ዘንድ ከበሬታ ባላቸው ወገኖች በመሆኑ አቶ ኦሞት ዲያስፖራውን ለመቀላቀል ያቀረበውን ምልጃ አበክረን እንቃወማለን። ዳግም ጄኖሳይድ አንለዋለን። በዚሁ መነሻ ጥንቃቄ ሊወሰድ እንደሚገባም እናሳስባለን። በቅርቡ ይፋ በሚሆነው የህግ አካሄድ ሁሉም ነገር ስለሚገለጥ ከሁሉም ወገን ማስተዋል ሊኖር እንደሚገባ ደግመን ደጋግመን ለመግለጽ እንወዳለን። እውነታው እየታወቀ እንደ ኦሞት ኦባንግ ካለ ወንጀለኛ ጋር ተባብሮ መሥራት የወንጀሉ ሰላባ የሆኑትን ንጹሃን የመካድ ያህል ሆኖ ይሰማናል። እንደ ኦሞት አይነት ወንጀለኞችን ወደ ትግል ማግበስበስ ኪሳራ ከመሆን እንደማያልፍ እናስገነዝባለን። ሳይውል ሳያድር እናየዋለን።

ኦሞት ኦባንግ በአኝዋክ ጭፍጨፋ ላይ እጃቸው አለበት የተባሉትን ሰዎች ሰም ዝርዝር መስጠቱ ተጠቁሟል። ድሮ ህግ ላይ ቀርቦ በማስረጃነት ሚዛን ደፍቶ መለስ ዜናዊ እንዲከሰስ ያስፈረደው ሰነድ ከመዘጋጀቱ በፊት ይህንን መሰሉ ትብብር ቢኖር በመጠኑም ቢሆን ባደነቅን ነበር። ዛሬ ሁሉም መረጃዎች ህዝብና ህግ ዘንድ ቀርበው ፍትህ በሚጠበቅበት ወቅት ላይ ጩኸትህ ከቶውንም አይገባንምና ኦሞት ኦባንግ መጀመሪያ ራስህን ነጻ እንድታደርግ እንመክርሃለን። ራስህን ሳትገደድ ለህግ አስረክብ!! ከዚህ ውጪ አሁን ማስተባበያ ማቅረቡ ጊዜው አይደለም። ለሂውማን ራይትስ ዎች የሰጠሃቸውን የጽሁፍ መልስ አንተነትህን ሊሸሽግ አይችልምና ካለህበት ታድነህ ህግ ፊት ከመቅረብህ በፊት ጊዜውን ተጠቀምበት።

ከአኙዋክ ጀስቲስ ካውንስል ጋር

መስከረም 13 ቀን 2014

For information, please contact Ato Ochala Abula, Chairman of the Anuak Justice Council (AJC)  E-mail:ochala@anuakjustice.org

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Comments

  1. Jemal M. says

    September 15, 2014 11:49 am at 11:49 am

    No one couldnot be above z law !

    Reply
  2. Aychew says

    October 10, 2014 08:46 pm at 8:46 pm

    law never justify z case with in this existing state

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የእምዬ ምኒልክ አዳራሽ October 30, 2023 10:27 am
  • የኢትዮጵያ መከላከያ መሥራች አጼ ምኒልክ መሆናቸውን ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ተናገሩ October 26, 2023 01:30 pm
  • ጥቅምት 15 ለምን? October 26, 2023 01:29 am
  • “በተፈተነ ጊዜ ሁሉ የሚፀና የድል ሠራዊት” October 26, 2023 12:57 am
  • “ውትድርና ሕይወቴ ነው” October 26, 2023 12:13 am
  • መከላከያ በሁሉም መስክ ኢትዮጵያን የሚመጥን ኃይል እየገነባ ነው October 20, 2023 05:07 pm
  • “ሁሉም ኢትዮጵያዊ ትምህርት ቤት እኩል ነው በችሎታው ነው እንጂ የሚመዘነው” ፕ/ር ብርሃኑ October 20, 2023 04:47 pm
  • 42 የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት አመራሮች እና ሠራተኞች ታሰሩ October 18, 2023 04:29 pm
  • በተማሪዎች ፈተና ውጤት ለታየው ውድቀት ትምህርት ሚ/ር ኃላፊ መሆን አለበት ተባለ October 18, 2023 04:00 pm
  • ቀይ ባሕር እና ዓባይ “የኅልውና ጉዳይ ናቸው”፤ “መተንፈሻ ወደብ ያስፈልገናል” October 13, 2023 10:04 pm
  • ከ3,106 ትምህርት ቤቶች 1,328ቱ (44%) አንድም ተማሪ አላሳለፉም October 10, 2023 01:51 pm
  • “አቋጥሬ” በአማራ ክልል እያጫረሰ ነው፤ ” ኑሮውን መቋቋም አልቻልንም ” ነዋሪዎች October 10, 2023 09:07 am
  • እሸቴ አሸባሪ፤ ቲዲኤፍ/ትሕነግ “ሰማዕት” – የዘመናችን ጉድ! October 7, 2023 06:47 am
  • በወልቃይት 1.1ሚሊዮን ኩንታል ሰሊጥ ለመሰብሰብ ከ1 ሚሊዮን በላይ ሠራተኛ ይፈለጋል September 27, 2023 10:42 am
  • በአማራ ክልል ሰላም ዕጦት ከ90.5 ቢሊዮን ብር በላይ ፕሮጀክቶች ቆመዋል September 27, 2023 08:41 am
  • ወርቁ አይተነው የሸሹት ከዝርፊያ፣ ውንብድናና ዕዳ ጋር በተያያዘ ነው September 21, 2023 02:38 pm
  • ወደ አማራ ክልል ሊተላለፍ የነበረ መሣሪያና ሰነድ ተያዘ September 19, 2023 04:35 pm
  • በትግራይ መርዶ በይፋ ሊታወጅ ነው September 19, 2023 04:22 pm
  • ጃርቶች ለምን ይጮኻሉ? September 19, 2023 04:37 am
  • “ዐቢይ ግድቡን ሸጦታል” ጌታቸው ረዳ September 11, 2023 10:18 am
  • አቶ አገኘሁ መረጃ አሳልፎ በመስጠት ዋጋ እንደሚከፍሉ ተሰማ September 10, 2023 06:52 pm
  • ለዋዜማ ሬዲዮ “ኢትዮጵያን ቋሚ የውሀ ባለ እዳ” ያደርጋል ያላችሁት ረቂቅ ሰነድ የታለ? September 10, 2023 01:58 am
  • ወደር የሌለው የኅብረተሰባዊት ኢትዮጵያ ጀግና! ብርጋዴር ጄኔራል ተስፋዬ ኃብተማርያም September 8, 2023 02:31 pm
  • የትግራይ መፍረስ በርዕሰ መስተዳደሩ አንደበት September 8, 2023 02:49 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule