• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የኢትዮጵያ ህዝብ ፍርድህ ምንድነው?

September 15, 2014 01:20 am by Editor 2 Comments

ከአኝዋክ ጀስቲስ ካውንስል የተሰጠ መግለጫ  

Anuak-Justice-Councilየህወሃት ፍጹም ታማኝ ነበር። በተለያዩ ሃላፊነቶች በህጻናት፣ በወንድሞቹ፣ በእህቶቹ፣ በእናቶቹ፣ በአባቶቹ አጠቃላይ በኢትዮጵያ ህዝብ ላይ በሰራው ወንጀል በህግ ይፈለጋል፣ በህግ የሚፈልጉት ኢትዮጵያዊያን ብቻ ሳይሆኑ ዓለም አቀፍ የፍትህና የመብት ተሟጋቾች ናቸው። ህወሃትን ክዶ በስደት ከሚገኝበት አገር እጁን እንዲሰጥ ጥሪ ቀርቦለታል። ይህ “ሰው” በጋምቤላ ክልል የፖሊስና የጸጥታ ሃላፊ የነበረ። የደህንነት አመራር ነበረ። ክልሉን በፕሬዚዳንትነት ለዓመታት የመራ፣ በጅምላ ለተጨፈጨፉት የአኝዋክ ንጹሃን ደም ቀዳሚ ተጠያቂ ነው – ኦሞት ኦባንግ !!

ኦሞት በዴሰምበር 13/2003 በጅምላ ጄኖሳይድ ለተፈጸመባቸው ከ424 በላይ የአኝዋክ ንጹሃን ዜጎች፣ በአስር ሺህ የሚቆጠሩ ዜጎች ስደት፣ መሬታቸው በግፍ ለተነጠቁና በጠመንጃ ለተፈናቀሉ ዜጎች ግንባር ቀደም ተጠያቂ መሆኑን ከአገራችን የቀበሌ ነዋሪ ጀምሮ እስከ ዓለም አቀፍ ደረጃ በማስረጃ የሚታወቅ ነው። ኦሞት በጋምቤላ ለፈሰሰው የንጹሃን ደም “ነጻ” ሊሆን የሚችልበት አንድም አግባብ የለም። ድርጅታችን አኙዋክ ጀስቲስ ኦሞትን ፍትህ አደባባይ እንደሚያቆመው ቅንጣት ያክል የማይጠራጠረውም ለዚህ ነው። ከተሰወረበት ፊሊፒንስ አድኖ ለመያዝ አስፈላጊው ስራ እየተሰራ ነው።

ጄኖሳይድ ዎች፣ የሂውማን ራይትስ ዎችና ከአኝዋክ ጀስቲስ ጋር አብረው ሲሰሩ የነበሩት የአይሲሲ /የዓለም አቀፉ የወንጀለኞች ፍርድ ቤት ጠበቆች/ በጋራ ኦሞት ኦባንግን ህግ ፊት ለማቅረብ እየሰሩ ነው። ኦሞት ከተሸሸገበት ፊሊፒንስ ወጥቶ ህግ ፊት እንዲቀርብ የሚደረገው ግፊት ባየለበት በአሁኑ ሰዓት የኦሞት አደባባይ ወጥቶ “ታግሎ አታጋይ” ለመሆን መወሰኑ ዜና የሆነበት ምክንያት አልገባንም።

omot wanted“የኢትዮጵያ ህዝብ ፍረድ፣ ፍርድህ ምንድን ነው?” ብለን ስንጠይቅ በህዝብ ዘንድ ያለውን የፍትህ ጥማት ዘንግተን አይደለም። እንደ ኦሞት አይነት በደምና በሙስና የተጨማለቀ ሰው ራሱን ነጻ ለማድረግ የሚናዘዘውን ኑዛዜ በጥንቃቄ እንድትመለከቱት ስለምንፈልግ ነው። ኦሞት ለኢሳት ከሰጠው መግለጫ ላይ ተቀንጭቦ “በሰበር ዜና” በተላለፈው መልዕክት “ኦሞት ወያኔን ለመታገል መወሰኑንና፣ በአኝዋክ ንጹሃን ዜጎች ላይ የተፈጸመውን ጭፍጨፋ አስመልከቶ ወንጀሉን የፈጸሙትን ክፍሎች ዝርዝር ሰጥተዋል” መባሉን ሰምተናል።

ኦሞት ኦባንግ ከክልል ፕሬዚዳንትነቱ ተነስቶ ወደ ፌዴራል ጉዳዮች ሚኒስትር ደዔታነት ከተዛወረ በኋላ አገር ጥሎ እንደኮበለለ አስቀድሞ ሊያነጋግረን ሞክሮ ነበር። ወያኔንን ለመታገል መወሰኑን ገልጾልን ነበር። አስፈላጊውን መረጃ ለመስጠት ተማጽኖንን ነበር። በዓለም ዓቀፍ ደረጃ የተመሰረተበትን ክስ እንድናጠራለት/ነጻ እንድናደርገው ሊማጸነን ሞክሮ ነበር። እኛ ግን እሱን ህግ ፊት ከማቅረብ የዘለለ ሃሳብና ፍላጎት ስላልነበረን “እጅህን ለፍትህ ስጥ” የሚል መልስ ነበር የመለስንለት። “የዓለም ዓቀፉ የወንጀለኞች ፍርድ ቤት ቀርበህ ተናዘዝ” ነበር ያልነው።

ትናንት በወገኖቹ ደም አጥንት ላይ ቆሞ ሲደንስ፣ በኢህአዴግ መገናኛዎች ላይ የወገኖቹን ነፍስ ሲረግም የነበረ ወንጀለኛ በየትኛውም መስፈርት ለወገኖቹ ነጻ መሆን ይታገላል ብለን አናምንም። መታገልም ከፈለገ ራሱን ቅድሚያ ህግ ፊት አቅርቦ ነጻ ሊያደርግ ይገባል የሚል አቋም አለን። ትግል የሚመራው ስብዕና ባላቸውና በህዝብ ዘንድ ከበሬታ ባላቸው ወገኖች በመሆኑ አቶ ኦሞት ዲያስፖራውን ለመቀላቀል ያቀረበውን ምልጃ አበክረን እንቃወማለን። ዳግም ጄኖሳይድ አንለዋለን። በዚሁ መነሻ ጥንቃቄ ሊወሰድ እንደሚገባም እናሳስባለን። በቅርቡ ይፋ በሚሆነው የህግ አካሄድ ሁሉም ነገር ስለሚገለጥ ከሁሉም ወገን ማስተዋል ሊኖር እንደሚገባ ደግመን ደጋግመን ለመግለጽ እንወዳለን። እውነታው እየታወቀ እንደ ኦሞት ኦባንግ ካለ ወንጀለኛ ጋር ተባብሮ መሥራት የወንጀሉ ሰላባ የሆኑትን ንጹሃን የመካድ ያህል ሆኖ ይሰማናል። እንደ ኦሞት አይነት ወንጀለኞችን ወደ ትግል ማግበስበስ ኪሳራ ከመሆን እንደማያልፍ እናስገነዝባለን። ሳይውል ሳያድር እናየዋለን።

ኦሞት ኦባንግ በአኝዋክ ጭፍጨፋ ላይ እጃቸው አለበት የተባሉትን ሰዎች ሰም ዝርዝር መስጠቱ ተጠቁሟል። ድሮ ህግ ላይ ቀርቦ በማስረጃነት ሚዛን ደፍቶ መለስ ዜናዊ እንዲከሰስ ያስፈረደው ሰነድ ከመዘጋጀቱ በፊት ይህንን መሰሉ ትብብር ቢኖር በመጠኑም ቢሆን ባደነቅን ነበር። ዛሬ ሁሉም መረጃዎች ህዝብና ህግ ዘንድ ቀርበው ፍትህ በሚጠበቅበት ወቅት ላይ ጩኸትህ ከቶውንም አይገባንምና ኦሞት ኦባንግ መጀመሪያ ራስህን ነጻ እንድታደርግ እንመክርሃለን። ራስህን ሳትገደድ ለህግ አስረክብ!! ከዚህ ውጪ አሁን ማስተባበያ ማቅረቡ ጊዜው አይደለም። ለሂውማን ራይትስ ዎች የሰጠሃቸውን የጽሁፍ መልስ አንተነትህን ሊሸሽግ አይችልምና ካለህበት ታድነህ ህግ ፊት ከመቅረብህ በፊት ጊዜውን ተጠቀምበት።

ከአኙዋክ ጀስቲስ ካውንስል ጋር

መስከረም 13 ቀን 2014

For information, please contact Ato Ochala Abula, Chairman of the Anuak Justice Council (AJC)  E-mail:ochala@anuakjustice.org

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Opinions Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Comments

  1. Jemal M. says

    September 15, 2014 11:49 am at 11:49 am

    No one couldnot be above z law !

    Reply
  2. Aychew says

    October 10, 2014 08:46 pm at 8:46 pm

    law never justify z case with in this existing state

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • በጦርነቱ የተጎዱ አካባቢዎችን ለማቋቋም የሚውል የ15 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር ድጋፍ የዓለም ባንክ May 16, 2022 10:22 am
  • በአዲስ አበባ 1 ሺህ 98 የብሬን እና 2 ሺህ 162 የክላሽ ጥይት ተያዘ May 16, 2022 10:10 am
  • በአዲስ አበባ ከተማ በግለሰብ መኖሪያ ቤት ከ5 ሺህ በላይ የአሜሪካ ዶላርና የተለያዩ አገራት ገንዘቦች ተያዙ May 16, 2022 09:53 am
  • አገር አፍራሹ ትህነግ ለቀለብ፣ መድኃኒትና ሥራ ማስኬጃ 76 ቢሊዮን ብር ቀርጥፏል May 16, 2022 08:30 am
  • እየተባባሰ ከመጣው የማህበራዊ ሚዲያ አጭበርባሪዎች ዜጎች ራሳቸውን እንዲጠብቁ ተጠየቀ May 15, 2022 09:38 am
  • የትህነግና ሸኔ መሠልጠኛ የምትባለው ዩጋንዳ መከላከያ ሚ/ር ከኤታማዦር ሹሙ ጋር ተወያዩ May 13, 2022 09:55 am
  • በትግራይ የውጊያ ምልመላው ጉዳይ May 11, 2022 02:37 am
  • መከላከያ በተጨማሪ ድሮን፣ በሥልጠና፣ በዝግጅት ራሱን አብቅቷል May 11, 2022 01:35 am
  • ትህነግ ለሌላ ውጊያ እየተዘጋጀ ነው ተባለ May 10, 2022 01:04 pm
  • ኤርትራ 8 ሩስያ ሠራሽ ድሮኖችን ተረክባለች May 10, 2022 12:37 am
  • ሙስሊምና ክርስቲያን በአንድነት የሚያከብረው የአኾላሌ ባሕላዊ ጭፈራ May 9, 2022 01:46 pm
  • በወልዲያ ፋኖዎች ተመረቁ May 9, 2022 12:51 pm
  • “ሠራዊታችን ድልን በአስተማማኝ መልኩ ማምጣት በሚችል ቁመና ላይ” ጀኔራል ጌታቸው May 9, 2022 11:57 am
  • ዋጋው 64 ሚሊዮን ብር የሚሆን (16 ኪሎ) ሕገወጥ ወርቅ ተያዘ May 9, 2022 11:51 am
  • አብን ክርስቲያን ታደለን ለመጨረሻ ጊዜ አስጠነቀቀ፤ 10 አባላቱን አገደ May 9, 2022 08:58 am
  • ራሱ አቡክቶ፣ ራሱ አሟሽሾ፣ ራሱ ጋግሮ በሰዓት 460 እንጀራ የሚያወጣ ፈጠራ May 9, 2022 08:17 am
  • በህገ ወጥ መንገድ 19 ህጻናትን ሲያዘዋወሩ የነበሩ 6 ሴቶች ተያዙ May 8, 2022 12:39 am
  • በአርሲ ሙስሊሞች ለቤ/ክ ማሠሪያ 3 ሚሊዮን ብርና 20 የቀንድ ከብት ሰጡ May 6, 2022 09:35 am
  • በአዲስ አበባ የሚኖረው የትህነግ ደጋፊ ማንነት በማስረጃ May 4, 2022 11:04 pm
  • ሙስሊም ወንድማማች የቤ/ክ ዘራፊዎችን በቁጥጥር ሥር አዋሉ May 4, 2022 09:04 am
  • ከ6 ሺህ የዓሳ ጫጩት ወደ 80 ሺህ May 4, 2022 08:57 am
  • ተስፋቢሱ ቴድሮስ May 3, 2022 12:16 pm
  • ከሽፏል! April 6, 2022 11:58 am
  • “ሩሲያ ዩክሬይንን ወረረች” እየተባለ ስለሚነዛው ወሬ ጥቂት እውነታዎች March 8, 2022 11:30 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2022 · Goolgule