• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ባለፉት ዘጠኝ ዓመታት ኢትዮጵያ 20 ቢሊዮን ዶላር ተዘርፋለች!

February 13, 2019 10:39 am by Editor 3 Comments

ህወሓት/ኢህአዴግ በግፍ ሲገዛት በነበረችው ኢትዮጵያ፣ አንድ ዓመት ያልሞላው የለውጥ ሒደት ተግባራዊ ከመሆኑ በፊት ባሉት ዘጠኝ ዓመታት (እኤአ 2003 – 2012) ባሉት ዓመታት ውስጥ 20ቢሊዮን ዶላር የሚጠጋ ገንዘብ በሕገወጥ መንገድ ከአገር ወጥቷል፤ ተዘርፏል። የሪፖርተሩ ብርሃኑ ፈቃደ ያቀናበረው እንዲህ ይነበባል፤

በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት  (ተመድ) ሥር የሚገኘው የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን ይፋ ያደረገው የአፍሪካ የጤና ክብካቤና የኢኮኖሚ ዕድገት ሪፖርት፣ ኢትዮጵያ ባለፉት ዘጠኝ ዓመታት ውስጥ 20 ቢሊዮን ዶላር የሚጠጋ ገንዘብ ወደ ውጭ በሕገወጥ መንገድ እንደሸሸባት አስታውቆ፣ ይህ ገንዘብ ለጤናው ዘርፍ የምታውለውን 87 በመቶ በጀት እንደሚሸፍን አመለከተ።

ማክሰኞ የካቲት 5 ቀን 2011 ዓ.ም. በአዲስ አበባ ይፋ የተደረገው የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን ሪፖርት፣ ኢትዮጵያ እ.ኤ.አ. ከ2003 እስከ 2012 ባሉት ዘጠኝ ዓመታት በየዓመቱ ከ2.2 ቢሊዮን ዶላር በላይ በሕገወጥ ገንዘብ በሚያሸሹ አካላት ሳቢያ ተጎጂ ሆናለች ብሏል። በዚህ ሳቢያም ለጤናው ዘርፍ የምትመድበው ዝቅተኛ በጀትም  በሚሸሸው ገንዘብ ምክንያት ከባድ ተፅዕኖ ውስጥ እንደቆየ አመላክቷል።

ኢትዮጵያ ከጠቅላላ ኢኮኖሚዋ (ከአገር ውስጥ አጠቃላይ ምርት አኳያ) አንድ በመቶ ለጤናው ዘርፍ ትመድባለች ያለው ሪፖርቱ፣ በአንፃሩ በየዓመቱ ከ2.2 ቢሊዮን ዶላር በላይ እየሸሸባት በመሆኑ 87 በመቶውን የጤናውን ዘርፍ በጀት ወደ ውጭ የሚሸሸው ገንዘብ እንደሚሸፍነው ሪፖርቱ አሥፍሯል።

ከዚህም በተጓዳኝ መንግሥት ለጤናው ዘርፍ ከሚያወጣው ወጪና ለዕዳ ክፍያ ከሚያውለው ገንዘብ ተቀናንሶ ሲሰላም፣ አገሪቱ በየዓመቱ የ2.5 ቢሊዮን ዶላር የበጀት ክፍተት እንደሚገጥማት ታውቋል።

እ.ኤ.አ. ከ2015 እስከ 2017 ባለው ጊዜ ውስጥ የኢትዮጵያ መንግሥት አማካይ ጠቅላላ የዕዳ ክምችት መጠን 55 ቢሊዮን ዶላር እንደደረሰ ተመድ አውስቶ፣ ከሕገወጥ ገንዘብ የማሸሽ ተግባር ባሻገር ለዕዳ ክፍያ የሚውለው ከፍተኛ ገንዘብም እንደ ጤናው መስክ ባሉት መሠረታዊ ዘርፎች ላይ ጫና ማሳደሩን አስታውቋል።

እንዲህ ያሉትን እውነታዎች ያጎላው የተመድ ሪፖርት፣ እ.ኤ.አ. ከ2003 እስከ 2012 ባለው ጊዜ ውስጥ አፍሪካ በጠቅላላው ከ300 እስከ 600 ቢሊዮን ዶላር  በሕገወጦች ገንዘብ የማሸሽ ድርጊት ሳቢያ ማጣቷትን አመልክቷል። ከጤናው መስክ አኳያም አገሮች ከዓመታዊ በጀታቸው አምስት በመቶ ለጤና ዘርፍ ይመድባሉ ተብሎ ቢገመት፣ በአፍሪካ ለጤናው መስክ ከሚያስፈልገው ገንዘብ ውስጥ የ66 ቢሊዮን ዶላር ክፍት እንደሚታይ ይፋ አድርጓል።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ አህመድ (ዶ/ር) የተገኙበትና የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን ከዳንጎቴ ፋውንዴሽን ጋር በመተባበር ባሰናዳው የ“አፍሪካ ቢዝነስ ሔልዝ ፎረም 2019” በተሰኘው መድረክ ላይ የናይጄሪያ ቢሊየነር ሐጂ አሊኮ ዳንጎቴ ልጅ ሐሊማ ዳንጎቴ ይፋ እንዳደረገችው፣ የዳንጎቴ ግሩፕ ኩባንያዎች ከታክስ ተቀናሽ በኋላ ከሚያስገቡት ትርፍ ውስጥ በአፍሪካ ጤናው ዘርፍ እንዲውል የአንድ በመቶ ገቢያቸውን ያውላሉ።

 እ.ኤ.አ. በ1994 የተመሠረተው የዳንጎቴ ፋውንዴሽን ከምሥረታው ጀምሮ፣ ለጤናና መሰል የበጎ ተግባራት የሚውል የ1.5 ቢሊዮን ዶላር በጀት በመመደብ ድጋፍ ሲያደረግ መቆየቱን የፋውንዴሽኑ መረጃዎች ይጠቁማሉ።

የአፍሪካ መንግሥታት ብቻቸውን ከፍተኛ የጤና ክብካቤ ችግሮች በሚስተዋሉባት አፍሪካ መሠረታዊ አገልግሎቶችን ማቅረብ እንደማይችሉ በማመን፣ ድጋፍ ለማድረግ በዳንጎቴ ፋውንዴሽን አማካይነት መሰባሰብ የጀመሩት የአፍሪካ ባለሀብቶች፣ ለጤናው ዘርፍ የአፍሪካ የቢዝነስ ጥምረት የተሰኘ መድረክም በአዲስ አበባው ፎረም ይፋ አድርገዋል።

የዓለም እግር ኳስ ኮከቡ ኮትዲቯራዊ ዲዲዬር ድሮግባ፣ በጤናና በትምህርት መስክ ለአፍሪካውያን ድጋፍ የሚያደርግበትን የዲዲዬር ድሮግባ ፋውንዴሽንን እንቅስቃሴዎች በማስመልከት ማብራሪያ ሰጥቷል።

በዚሁ መድረክ ጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይን ጨምሮ የጂቡቲ ፕሬዚዳንት ኢስማኤል ኦማር ጊሌህ፣ የቦትስዋና ፕሬዚዳንት ሞክዊትሲ ማሲሲአ፣ እንዲሁም የኬንያ፣ የግብፅና የሌሎች አገሮች የጤና ሚኒስትሮች ስለአገሮቻቸው የጤና ዘርፍ እንቅስቃሴዎች ገለጻ አቅርበዋል። (ምንጭ፤ ሪፖርተር)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Comments

  1. Tesfa says

    February 24, 2019 07:39 am at 7:39 am

    ፓለቲካ ነፍስና ሥጋን ያጠወልጋል። ስልጣንም ከራስ ላይ ከወጣ በህዋላ እንደ ስካር ቶሎ አይለቅም። ለዛ ነው በአለም ዙሪያ ዘልዛላ የሃገር መሪዎችን የምናየው። መዝረፉ፤ መግደሉ፤ ታጅቦ መሄድ ከውሃ ጥም የበለጠ ስለሆነባቸው ውረድ ለሃገርና ለህዝብ አልበጃቹሁም ሲባሉ በጊዜአዊ አዋጅ እጅ እና እግርን አፍን ጠፍሮና ለጎሞ በሚይዝ ህግ ሰውን የሚተበትቡት። ጊዜአዊ መረጃ የሱዳኑን መሪ መውሰድ ይቻላል። ሰው እንዴት ከጃፋር ኒሜሪ አወዳደቅ አይማርም። እንዴት ከጎረቤቱ የኡጋንዳው ኢዲአሚን እድል ፈንታ ዛሬን አይቶ በቃኝ ማለት አይችልም?
    የአፍሪቃ መሪዎች ጨካኞችና ዘረኞች ናቸው። የሚያስቡትም ለዛሬ ብቻ ነው። በዘጠኝ ዓመታት 9 ቢሊዮን ዶላር የተዘረፈችው መከረኛዋ ሃገራችን በወያኔ ዘመን የደረሰባት ገመና ጣሊያን ካደረሰባት ይከፋል። በ27 አመቱ አስከፊ ድርጊት በሃገሪቱ አንጡራ ሃብት ሲፈነጩ የኖሩት ጠባብ ብሄርተኞቹ ዛሬም እያስፈራሩ እንደሆነ ከዶ/ር ደብረጽዮን ንግግር መረዳት ይቻላል። አልፈው ከመጡ “እንጠራርጋቸዋለን” የሚጠረገው ታልፎስ የሚመጣው ማን ነው? ባህር ተሻግሮ የሃገሪቱን ድንበር አቋርጦ ለወረራ ሊመጣ የተዘጋጀ የውጭ ሃይል ካለ ይፋ ማድረግና በህብረት መፋለም ነው። ውጊያው ከወገን ሰው ጋር ከሆነ የወያኔ የመኖሪያ ብልሃት እንጂ ወራሪም ተወራሪም የለም። የሚያሳዝነው ግን ለዘብ ያለ አቋም አላቸው የተባሉት እነ ገብሩ አሥራትም ንግግራቸው ሁሉ በእሳት ላይ ነዳጅ ማርከፍከፍ መሆኑ ያሳዝናል። አይበቃም መገዳደል? ሌላውን ወደ እሳት እየገፋችሁ እስከ መቼ ነው እናንተ የምትኖሩት? ዘልዛሎች። በቃኝን የማታውቁ። የፓለቲከኛ ጡረታ የለውም እንዴ? ከ44 ዓመት በፊት የገመዳችሁት የመከፋፈልና የብሄርተኛ ገመድ ዛሬ ሃገሪቱን ከፍተኛ ቀውስ ላይ እንደጣላት ማየት እንዴት ይከብዳል? ህገ – መንግሥቱ ይከበር ማለትስ ምን ማለት ነው። እናነተን እስካላገለገለ ድረስ ህገ-መንግሥቱ ፈረስ ማለት ነው? ስታፍኑ፤ ስትገሉ፤ በወንድ ላይ እሴት ሽንቷን እንድትሸና ስታረጉ፤ ወንድ ወንድን እንዲደፍር ሲደረግ፤ ጥፍር በፒንሳ ሲነቀል ወዘተ… ህገ መንግሥቱን ተደግፋችሁ ነበር እንዴ የፈጸማችሁት?
    አንድ የወያኔን ግፍ ለበልና ሃሳቤን ልግታ። ጊዜው ወያኔ የከተማ አለቃ እንደሆነ ነው። ከሻቢያም ጋር እንደሙጫ ተጣብቀዋል። በዚህ መካከል የወረቀት ገንዘብና ሽርፍራፊ ሳንቲም ኤርትራ ውስጥ የለምና በአስቸኳይ ይላክልን ይላል በቅርቡ የኤርትራ አለቃ የሆነው ሻቢያ። ጉዳዮም በአቶ መለስ ታይቶ ይሰጥ ይባላል። ጉዳዮ ከባንኩ ሃላፊ ሲደርስ ጭራሽ አይሆንም በማለት ይቃወማል። ማታ የወያኔ የግድያ ኮማንዶ ተልኮ አፍነው ከገደሉት በህዋላ ራሱን ሰቀለ ለማለት ያንጠለጥሉታል። በምትኩም ለወያኔ ዝርፊያ የሚስማማ ሰው ለባንኩ ይሾማል። የተባለውም ገንዘብ በኢትዮጵያ አየር መንገድ ተጭኖ ለሻቢያ ይሰጣል። ይህ ከሚያልፍ ውሃ የተቀዳ ታሪክ አይደለም። እውነት እንጂ! በ44 አመቱ የወያኔ ዘመን ያልተሰራ ግፍ የለም። የትግራይ ህዝብ ለትግራይ ህዝብ የሚባለው ሰውን ለማደንቆር ነው። ለዘመናት በስሙ ሲነግዱበት፤ ተርቦ የዓለም ህዝብ ያዋጣውን ገንዘብ ተከፋፍለው ይገዛ በተባለው ስንዴ ምትክ አሽዋ በጆኒያ ከምረው ስንዴ ነው በማለት እርዳታ አቅራቢዎችን የሚያታልሉ ጉዶች ናቸው። በመሰረቱ የትግራይ ህዝብ ሁለት ክፉ ሃይሎች እንደ ሥጋ ቅርጫ ሲቀራመቱት ነው የኖረው። ወያኔና ደርግ!
    ወያኔ በውጊያ ወደ ነበርንበት ስልጣን እንመለሳለን ብሎ ማሰቡ ክትዕቢት የመነጨ እንጂ ከእውነት ጋር አይገናኝም። ሃገሪቱን ያፈርሷታል እንጂ ዳግም በእነርሱ እጅ የሚገዛ ማንም አይኖርም። የትግራይም ህዝብ ጊዜውን ጠብቆ እንደ ሞሶሎኒ ዘቅዝቆ እንደ ሚሰቅላቸው አልጠራጠርም። የታፈነ ህዝብ ሲነሳ የሚያቆመው ሃይል አይኖርምና! አቦይ ስብሃት ይኖሩ ይሆን ከሚሰቅሉት መካከል ወይስ ቀድመው የተፈጥሮ ሞትን ይሞቱ! የቆየ ሰው ያያል!!

    Reply
  2. Yabdeta says

    March 17, 2019 12:15 pm at 12:15 pm

    Is golgool frozen in time since February? Is it your sources have dried up or there are not topics worth googol’s editorial policies to write about. Or could it be googol losing the neutral ground in the current old-odp-jawarian led ethnographies politics? We wonder as we see many showing their true colours. – is golgool also a chameleon?

    Reply
  3. Golguayoo says

    March 19, 2019 05:10 pm at 5:10 pm

    Stuck in time Golgool? Nothing to report since this article? Nothing happened since or you don’t want to report it? Shut down your web then.

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule