• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ባለፉት ዘጠኝ ዓመታት ኢትዮጵያ 20 ቢሊዮን ዶላር ተዘርፋለች!

February 13, 2019 10:39 am by Editor 3 Comments

ህወሓት/ኢህአዴግ በግፍ ሲገዛት በነበረችው ኢትዮጵያ፣ አንድ ዓመት ያልሞላው የለውጥ ሒደት ተግባራዊ ከመሆኑ በፊት ባሉት ዘጠኝ ዓመታት (እኤአ 2003 – 2012) ባሉት ዓመታት ውስጥ 20ቢሊዮን ዶላር የሚጠጋ ገንዘብ በሕገወጥ መንገድ ከአገር ወጥቷል፤ ተዘርፏል። የሪፖርተሩ ብርሃኑ ፈቃደ ያቀናበረው እንዲህ ይነበባል፤

በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት  (ተመድ) ሥር የሚገኘው የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን ይፋ ያደረገው የአፍሪካ የጤና ክብካቤና የኢኮኖሚ ዕድገት ሪፖርት፣ ኢትዮጵያ ባለፉት ዘጠኝ ዓመታት ውስጥ 20 ቢሊዮን ዶላር የሚጠጋ ገንዘብ ወደ ውጭ በሕገወጥ መንገድ እንደሸሸባት አስታውቆ፣ ይህ ገንዘብ ለጤናው ዘርፍ የምታውለውን 87 በመቶ በጀት እንደሚሸፍን አመለከተ።

ማክሰኞ የካቲት 5 ቀን 2011 ዓ.ም. በአዲስ አበባ ይፋ የተደረገው የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን ሪፖርት፣ ኢትዮጵያ እ.ኤ.አ. ከ2003 እስከ 2012 ባሉት ዘጠኝ ዓመታት በየዓመቱ ከ2.2 ቢሊዮን ዶላር በላይ በሕገወጥ ገንዘብ በሚያሸሹ አካላት ሳቢያ ተጎጂ ሆናለች ብሏል። በዚህ ሳቢያም ለጤናው ዘርፍ የምትመድበው ዝቅተኛ በጀትም  በሚሸሸው ገንዘብ ምክንያት ከባድ ተፅዕኖ ውስጥ እንደቆየ አመላክቷል።

ኢትዮጵያ ከጠቅላላ ኢኮኖሚዋ (ከአገር ውስጥ አጠቃላይ ምርት አኳያ) አንድ በመቶ ለጤናው ዘርፍ ትመድባለች ያለው ሪፖርቱ፣ በአንፃሩ በየዓመቱ ከ2.2 ቢሊዮን ዶላር በላይ እየሸሸባት በመሆኑ 87 በመቶውን የጤናውን ዘርፍ በጀት ወደ ውጭ የሚሸሸው ገንዘብ እንደሚሸፍነው ሪፖርቱ አሥፍሯል።

ከዚህም በተጓዳኝ መንግሥት ለጤናው ዘርፍ ከሚያወጣው ወጪና ለዕዳ ክፍያ ከሚያውለው ገንዘብ ተቀናንሶ ሲሰላም፣ አገሪቱ በየዓመቱ የ2.5 ቢሊዮን ዶላር የበጀት ክፍተት እንደሚገጥማት ታውቋል።

እ.ኤ.አ. ከ2015 እስከ 2017 ባለው ጊዜ ውስጥ የኢትዮጵያ መንግሥት አማካይ ጠቅላላ የዕዳ ክምችት መጠን 55 ቢሊዮን ዶላር እንደደረሰ ተመድ አውስቶ፣ ከሕገወጥ ገንዘብ የማሸሽ ተግባር ባሻገር ለዕዳ ክፍያ የሚውለው ከፍተኛ ገንዘብም እንደ ጤናው መስክ ባሉት መሠረታዊ ዘርፎች ላይ ጫና ማሳደሩን አስታውቋል።

እንዲህ ያሉትን እውነታዎች ያጎላው የተመድ ሪፖርት፣ እ.ኤ.አ. ከ2003 እስከ 2012 ባለው ጊዜ ውስጥ አፍሪካ በጠቅላላው ከ300 እስከ 600 ቢሊዮን ዶላር  በሕገወጦች ገንዘብ የማሸሽ ድርጊት ሳቢያ ማጣቷትን አመልክቷል። ከጤናው መስክ አኳያም አገሮች ከዓመታዊ በጀታቸው አምስት በመቶ ለጤና ዘርፍ ይመድባሉ ተብሎ ቢገመት፣ በአፍሪካ ለጤናው መስክ ከሚያስፈልገው ገንዘብ ውስጥ የ66 ቢሊዮን ዶላር ክፍት እንደሚታይ ይፋ አድርጓል።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ አህመድ (ዶ/ር) የተገኙበትና የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን ከዳንጎቴ ፋውንዴሽን ጋር በመተባበር ባሰናዳው የ“አፍሪካ ቢዝነስ ሔልዝ ፎረም 2019” በተሰኘው መድረክ ላይ የናይጄሪያ ቢሊየነር ሐጂ አሊኮ ዳንጎቴ ልጅ ሐሊማ ዳንጎቴ ይፋ እንዳደረገችው፣ የዳንጎቴ ግሩፕ ኩባንያዎች ከታክስ ተቀናሽ በኋላ ከሚያስገቡት ትርፍ ውስጥ በአፍሪካ ጤናው ዘርፍ እንዲውል የአንድ በመቶ ገቢያቸውን ያውላሉ።

 እ.ኤ.አ. በ1994 የተመሠረተው የዳንጎቴ ፋውንዴሽን ከምሥረታው ጀምሮ፣ ለጤናና መሰል የበጎ ተግባራት የሚውል የ1.5 ቢሊዮን ዶላር በጀት በመመደብ ድጋፍ ሲያደረግ መቆየቱን የፋውንዴሽኑ መረጃዎች ይጠቁማሉ።

የአፍሪካ መንግሥታት ብቻቸውን ከፍተኛ የጤና ክብካቤ ችግሮች በሚስተዋሉባት አፍሪካ መሠረታዊ አገልግሎቶችን ማቅረብ እንደማይችሉ በማመን፣ ድጋፍ ለማድረግ በዳንጎቴ ፋውንዴሽን አማካይነት መሰባሰብ የጀመሩት የአፍሪካ ባለሀብቶች፣ ለጤናው ዘርፍ የአፍሪካ የቢዝነስ ጥምረት የተሰኘ መድረክም በአዲስ አበባው ፎረም ይፋ አድርገዋል።

የዓለም እግር ኳስ ኮከቡ ኮትዲቯራዊ ዲዲዬር ድሮግባ፣ በጤናና በትምህርት መስክ ለአፍሪካውያን ድጋፍ የሚያደርግበትን የዲዲዬር ድሮግባ ፋውንዴሽንን እንቅስቃሴዎች በማስመልከት ማብራሪያ ሰጥቷል።

በዚሁ መድረክ ጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይን ጨምሮ የጂቡቲ ፕሬዚዳንት ኢስማኤል ኦማር ጊሌህ፣ የቦትስዋና ፕሬዚዳንት ሞክዊትሲ ማሲሲአ፣ እንዲሁም የኬንያ፣ የግብፅና የሌሎች አገሮች የጤና ሚኒስትሮች ስለአገሮቻቸው የጤና ዘርፍ እንቅስቃሴዎች ገለጻ አቅርበዋል። (ምንጭ፤ ሪፖርተር)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Comments

  1. Tesfa says

    February 24, 2019 07:39 am at 7:39 am

    ፓለቲካ ነፍስና ሥጋን ያጠወልጋል። ስልጣንም ከራስ ላይ ከወጣ በህዋላ እንደ ስካር ቶሎ አይለቅም። ለዛ ነው በአለም ዙሪያ ዘልዛላ የሃገር መሪዎችን የምናየው። መዝረፉ፤ መግደሉ፤ ታጅቦ መሄድ ከውሃ ጥም የበለጠ ስለሆነባቸው ውረድ ለሃገርና ለህዝብ አልበጃቹሁም ሲባሉ በጊዜአዊ አዋጅ እጅ እና እግርን አፍን ጠፍሮና ለጎሞ በሚይዝ ህግ ሰውን የሚተበትቡት። ጊዜአዊ መረጃ የሱዳኑን መሪ መውሰድ ይቻላል። ሰው እንዴት ከጃፋር ኒሜሪ አወዳደቅ አይማርም። እንዴት ከጎረቤቱ የኡጋንዳው ኢዲአሚን እድል ፈንታ ዛሬን አይቶ በቃኝ ማለት አይችልም?
    የአፍሪቃ መሪዎች ጨካኞችና ዘረኞች ናቸው። የሚያስቡትም ለዛሬ ብቻ ነው። በዘጠኝ ዓመታት 9 ቢሊዮን ዶላር የተዘረፈችው መከረኛዋ ሃገራችን በወያኔ ዘመን የደረሰባት ገመና ጣሊያን ካደረሰባት ይከፋል። በ27 አመቱ አስከፊ ድርጊት በሃገሪቱ አንጡራ ሃብት ሲፈነጩ የኖሩት ጠባብ ብሄርተኞቹ ዛሬም እያስፈራሩ እንደሆነ ከዶ/ር ደብረጽዮን ንግግር መረዳት ይቻላል። አልፈው ከመጡ “እንጠራርጋቸዋለን” የሚጠረገው ታልፎስ የሚመጣው ማን ነው? ባህር ተሻግሮ የሃገሪቱን ድንበር አቋርጦ ለወረራ ሊመጣ የተዘጋጀ የውጭ ሃይል ካለ ይፋ ማድረግና በህብረት መፋለም ነው። ውጊያው ከወገን ሰው ጋር ከሆነ የወያኔ የመኖሪያ ብልሃት እንጂ ወራሪም ተወራሪም የለም። የሚያሳዝነው ግን ለዘብ ያለ አቋም አላቸው የተባሉት እነ ገብሩ አሥራትም ንግግራቸው ሁሉ በእሳት ላይ ነዳጅ ማርከፍከፍ መሆኑ ያሳዝናል። አይበቃም መገዳደል? ሌላውን ወደ እሳት እየገፋችሁ እስከ መቼ ነው እናንተ የምትኖሩት? ዘልዛሎች። በቃኝን የማታውቁ። የፓለቲከኛ ጡረታ የለውም እንዴ? ከ44 ዓመት በፊት የገመዳችሁት የመከፋፈልና የብሄርተኛ ገመድ ዛሬ ሃገሪቱን ከፍተኛ ቀውስ ላይ እንደጣላት ማየት እንዴት ይከብዳል? ህገ – መንግሥቱ ይከበር ማለትስ ምን ማለት ነው። እናነተን እስካላገለገለ ድረስ ህገ-መንግሥቱ ፈረስ ማለት ነው? ስታፍኑ፤ ስትገሉ፤ በወንድ ላይ እሴት ሽንቷን እንድትሸና ስታረጉ፤ ወንድ ወንድን እንዲደፍር ሲደረግ፤ ጥፍር በፒንሳ ሲነቀል ወዘተ… ህገ መንግሥቱን ተደግፋችሁ ነበር እንዴ የፈጸማችሁት?
    አንድ የወያኔን ግፍ ለበልና ሃሳቤን ልግታ። ጊዜው ወያኔ የከተማ አለቃ እንደሆነ ነው። ከሻቢያም ጋር እንደሙጫ ተጣብቀዋል። በዚህ መካከል የወረቀት ገንዘብና ሽርፍራፊ ሳንቲም ኤርትራ ውስጥ የለምና በአስቸኳይ ይላክልን ይላል በቅርቡ የኤርትራ አለቃ የሆነው ሻቢያ። ጉዳዮም በአቶ መለስ ታይቶ ይሰጥ ይባላል። ጉዳዮ ከባንኩ ሃላፊ ሲደርስ ጭራሽ አይሆንም በማለት ይቃወማል። ማታ የወያኔ የግድያ ኮማንዶ ተልኮ አፍነው ከገደሉት በህዋላ ራሱን ሰቀለ ለማለት ያንጠለጥሉታል። በምትኩም ለወያኔ ዝርፊያ የሚስማማ ሰው ለባንኩ ይሾማል። የተባለውም ገንዘብ በኢትዮጵያ አየር መንገድ ተጭኖ ለሻቢያ ይሰጣል። ይህ ከሚያልፍ ውሃ የተቀዳ ታሪክ አይደለም። እውነት እንጂ! በ44 አመቱ የወያኔ ዘመን ያልተሰራ ግፍ የለም። የትግራይ ህዝብ ለትግራይ ህዝብ የሚባለው ሰውን ለማደንቆር ነው። ለዘመናት በስሙ ሲነግዱበት፤ ተርቦ የዓለም ህዝብ ያዋጣውን ገንዘብ ተከፋፍለው ይገዛ በተባለው ስንዴ ምትክ አሽዋ በጆኒያ ከምረው ስንዴ ነው በማለት እርዳታ አቅራቢዎችን የሚያታልሉ ጉዶች ናቸው። በመሰረቱ የትግራይ ህዝብ ሁለት ክፉ ሃይሎች እንደ ሥጋ ቅርጫ ሲቀራመቱት ነው የኖረው። ወያኔና ደርግ!
    ወያኔ በውጊያ ወደ ነበርንበት ስልጣን እንመለሳለን ብሎ ማሰቡ ክትዕቢት የመነጨ እንጂ ከእውነት ጋር አይገናኝም። ሃገሪቱን ያፈርሷታል እንጂ ዳግም በእነርሱ እጅ የሚገዛ ማንም አይኖርም። የትግራይም ህዝብ ጊዜውን ጠብቆ እንደ ሞሶሎኒ ዘቅዝቆ እንደ ሚሰቅላቸው አልጠራጠርም። የታፈነ ህዝብ ሲነሳ የሚያቆመው ሃይል አይኖርምና! አቦይ ስብሃት ይኖሩ ይሆን ከሚሰቅሉት መካከል ወይስ ቀድመው የተፈጥሮ ሞትን ይሞቱ! የቆየ ሰው ያያል!!

    Reply
  2. Yabdeta says

    March 17, 2019 12:15 pm at 12:15 pm

    Is golgool frozen in time since February? Is it your sources have dried up or there are not topics worth googol’s editorial policies to write about. Or could it be googol losing the neutral ground in the current old-odp-jawarian led ethnographies politics? We wonder as we see many showing their true colours. – is golgool also a chameleon?

    Reply
  3. Golguayoo says

    March 19, 2019 05:10 pm at 5:10 pm

    Stuck in time Golgool? Nothing to report since this article? Nothing happened since or you don’t want to report it? Shut down your web then.

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ጎርጎራ – የመጻዒው ዘመን ሙሽራ! የዉበት ፈርጥ! January 17, 2023 04:18 pm
  • ሁለተኛው መስቀል አደባባይ January 17, 2023 04:13 pm
  • በአቡዳቢ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን January 17, 2023 04:08 pm
  • በንፋስ ስልክ ላፍቶ ስምንት የመሬት ሌቦች ተያዙ January 16, 2023 11:36 am
  • ሺሻ ሲያስጨሱ በተገኙ ሆቴሎችና የምሽት ጭፈራ ቤቶች ላይ እርምጃ ተወሰደ January 16, 2023 08:50 am
  • በሐሰተኛ መታወቂያ የደኅንነት አባል ነን ብለው ሲያጭበረብሩ የነበሩ ተያዙ January 13, 2023 02:03 pm
  • ተሽከርካሪ ወንበር ለትግራይ – “ናይ ኣካል ጉዱኣት ተሽከርካሪ ዘለዎ ወንበር” January 12, 2023 07:17 pm
  • የአማራው ኩራት፣ የኢትዮጵያ ዘብ፣ የትህነግን ቅስም ሰባሪ! January 12, 2023 04:00 pm
  • በኢትዮጵያ ላይ የተጣሉ ማዕቀብ እና ሌሎች አስገዳጅ ሕጎች ሙሉ ለሙሉ ተሰረዙ January 12, 2023 01:52 pm
  • የቻይና ዕዳ ስረዛ “Payday Loan Diplomacy” ወይስ ኢትዮጵያን ያዳነ ተግባር? January 12, 2023 11:00 am
  • የአዲስ አበባ አስተዳደር ከቋንቋ ጋር በተያያዘ ውሳኔ አስተላለፈ January 12, 2023 10:46 am
  • “አምባሳደሩ” የቀድሞ ጌቶቻቸውን እንዲያቋቁሙ ተሾሙ January 11, 2023 03:47 pm
  • መከላከያ ሸኔን የሚዋጉ ሚሊሻዎችን አሠልጥኖ አስመረቀ January 10, 2023 05:37 pm
  • በሰባት ተጠርጣሪዎች ላይ ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመሰረተ January 10, 2023 03:36 pm
  • የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ አቅጣጫ January 6, 2023 03:26 pm
  • “ከዕብሪቱ አስተንፍሰነዋል” – ኢሳያስ January 2, 2023 07:29 pm
  • [ኢትዮጵያን] “አስታክኮ ኤርትራን መውጋት ለሚፈልግ ኃይል አንተባበርም” January 2, 2023 07:11 pm
  • የ፰ ወር ሕጻንና ጨቅላ ወንዶች የሚደፈሩባት ትግራይ December 14, 2022 02:49 pm
  • “ሰውን ለመርዳት ሰው መሆን ብቻ በቂ ነው” የደጎች አውራ የመቄዶኒያው ቢንያም በለጠ December 14, 2022 09:59 am
  • “የሀብት ምዝገባ መረጃው ለሕዝብ ክፍት ይደረግ “ December 13, 2022 10:30 am
  • የኢትዮጵያ ዓለምአቀፋዊ የሌብነት ደረጃ December 13, 2022 09:42 am
  • ለብረት አቅላጮች ለመሸጥ በኤሌክትሪክ የብረት ማማዎች ስርቆት የ100 ሚሊዮን ብር ኪሳራ December 13, 2022 09:26 am
  • በትግራይ የሰላም ስምምነቱን መሠረት ያደረገ የሽግግር ፍትሕ እንደሚፈጸም ተገለጸ December 13, 2022 09:20 am
  • ከ30 ሚሊየን ብር በላይ በሚሆን ሌብነት የተከሰሱት የደኅንነት መ/ቤት ሠራተኞች ክስ ተመሰረተ December 13, 2022 09:06 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule