1) ያልተረጋገጠ መረጃ እያኘክ ትኩረትክን አትጣ። አሁንም ተወርረሃል! በርካታ ወገንህ በጨካኝ ኃይል ስር ነው። እየተዘረፈ፣ እየተጨፈጨፈ ነው። አቋም ያዝ። ጠላት ወርሮኛል ብለህ ተቆጣ! በሰበር ዜና ስሜትህን አታላላ! ሰበር ዜና አንተ እንድትታለን የሚለቀቅ አይደለም። ከሜዳ እንድትዘናጋ የሚሰራ አይደለም። ጠላት ይደንግጥበት፣ አንተ ተጨማሪ የማሸነፍ ወኔ ሰንቀህ ገስገስበት! 2) መጥፎ ነገር ሲኖር ከዚህም ከዛም ላይ አትበሳጭ፣ ተስፋ አትቁረጥ። መፅናት ብቻ ነው የሚያዋጣው። መቼም ቢሆን እናሸንፋለን ብለህ አቋም ያዝ። 3) ሕዝብ በረንዳህ አይደለም። በረንዳህን ብርድ ሲሆን ጥለኸው ትገባለህ። ፀሐይ ሲሆን ወጥተህ ትዘረጋበታለህ አይደል? ሕዝብ እንደዛ አይደለም። በክፉውም በበጎውም አብረኸው ሁን። ሲጠቃ ተስፋ ቆርጠህ፣ ተስፋ እያስቆረጥክ፣ ለጠላት የሚጠቅም ፕሮፖጋንዳ ስታሰራጭ … [Read more...] about ምን ታደርጋለህ መሰለህ?
Middle Column
ዳዊት ወልደጊዮርጊስ – የጸረ ኢትዮጵያዊነት መገለጫ
ዳዊት ወልደጊዮርጊስ እሱን የመሰሉትን ከየዓይነቱ ሰብስቦ በጀመረው ዘመቻ የሽግግር መንግሥት ሰነድ ነድፎ የሞተውን ትህነግን አዝሎ እየሮጠ እንደሆነ አስቀድሞ የተገለጸ ቢሆንም ዛሬ ላይ ግን እሱና ራሱን በሚከረፉ ቃላት አደባባይ መላው ኢትዮጵያ ህዝብ ፊት ካዋረደው ታምራት ላይኔ የሚደግፏቸው ሚዲያዎች አማካይነት ይህንኑ የሽግግር መንግሥት አዋጅ ልክ ነገ እንደሚተገበር አድርጎ እያሳወጃቸው ነው። በኢትዮጵያ ውስጥ ተሞክረው ከከሸፉ በርካታ መልካም አጋጣሚዎች ጀርባ ስሙ የሚነሳው ሰላዩ ዳዊት ወልደጊዮርጊስ ደጋፊ ለማሰባሰብ ሲል እሱና ታምራት ላይኔ፣ እንዲሁም በመረጃ ቲቪ ባለቤቶች ስፖንሰር አድራጊነት የአሜሪካ መንግሥት ዕውቅና እንዳለው አድርጎ የሚዲያ ማስታወቂያ ያሰራበት ዕቅድ ሰነድ ለአሜሪካ መንግሥት ከመድረሱ በፊት ሙሉ ዶሴው መንግሥት እጅ መግባቱን የጎልጉል ተባባሪ ዘጋቢያችን … [Read more...] about ዳዊት ወልደጊዮርጊስ – የጸረ ኢትዮጵያዊነት መገለጫ
“የተባረኩ እጆች” – በአራት ዓመት 326 ገደማ የልብ ቀዶ ጥገና ያደረጉ ሐኪም
ከቶንሲልና ተያያዥ ህመሞች ጋር በተያያዘ የሚመጡ በተለይም ቦርቀው ባልጠገቡ ህጻናት ላይ የሚያጋጥሙ የልብ ህመሞችን በማከም ይታወቃሉ። መሳቅ፤ መጫወትም ሆነ መቦረቅ አቅቷቸው ነጋቸው የጨለመባቸውን በርካታ ህጻናት ለመታደግ በመቻላቸውም ስማቸው በብዙዎች ይጠቀሳል፤ ኢትዮጵያው ልብ ቀዶ ጠጋኝ ሃኪም ዶ/ር ፈቀደ አግዋር። ከባልደረቦቻቸው ጋር በመሆን በኢትዮጵያ የልብ ቀዶ ጥገና ህክምና ታሪክ አዲስ ምዕራፍን ከፍተዋል የሚባልላቸው ዶ/ር ፈቀደ በግላቸው 326 ገደማ ቀዶ ጥገናዎችን ማድረጋቸውን ከአል ዐይን አማርኛ ጋር በነበራቸው ቆይታ ተናግረዋል። በገንዘብም ሆነ በአገልግሎት ለመገመት ሊያዳግት በሚችል ደረጃ በርካቶችን ረድተናል የሚሉት ዶ/ር ፈቀደ እነዚህን የብዙዎችን ህይወት የታደጉ ቀዶ ጥገናዎች በ4 ዓመታት ውስጥ ነው ያደረጉት። ከ326ቱ ውስጥ 290 ገደማዎቹ ቀዶ … [Read more...] about “የተባረኩ እጆች” – በአራት ዓመት 326 ገደማ የልብ ቀዶ ጥገና ያደረጉ ሐኪም
“ብቃት የለኝም፤ የሥነምግባር ችግር አለብኝ” ታምራት ላይኔ
https://youtu.be/fWtD-akMhSU?t=400 ታምራት ስለ ራሱ የሥነምግባር ጉድለት በአደባባይ የተናገረውን ቪዲዮውን በመጫን ይመልከቱ የወንበዴው ቡድን አምበል በሆነው መለስ ዜናዊ በያኔው “ፓርላማ” ፊት ሌብነቱ ተዘርዝሮ እና የሥነምግባር ብልሹነቱን አምኖ ከፓርላማው የተባረረው ታምራት ላይኔ ሰሞኑን የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ለመሆን እየተመኘ ነው። ከበረኻ ወዳጆቹ እነ ሰዬ አብርሃ ጋር በመሆን ነው በዚህ ሥራ የተጠመደው። ታምራት በመለስ ትዕዛዝ በፓርላማው ፊት ሌብነቱን፣ ሥነ ምግባሩ የጎደፈና መሪ መሆን የማይችል መሆኑን አምኖ መባረሩ ትክክል ነው በማለት ተቀብሎ የላሰውን ስኳር ሳያጣጥም ወዲያውኑ ወደ እስር ቤት ነበር የተወረወረው። ጥያቄያችን ያኔ በዚህ መልኩ ብቃት የለኝም፣ ሥነ ምግባሬ ለተቀመጥኩበት የምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የመከላከያ ሚኒስትር … [Read more...] about “ብቃት የለኝም፤ የሥነምግባር ችግር አለብኝ” ታምራት ላይኔ
በአዲስ አበባ 325 የትህነግ አሸባሪዎች ከነመሣሪያቸው ተይዘዋል
የአዲስ አበባ ፖሊስ ከሌሎች የፀጥታ አካላት ጋር በመቀናጀት በጥናት ላይ በመመስረት እና ከህዝብ የደረሰውን መረጃ መሰረት በማድረግ በከተማችን በስጋትነት በተለዩ የተለያዩ ንግድ ቤቶች እና ድርጅቶች ላይ ባደረገው ብርበራ እና ፍተሻ ልዩ ልዩ የጦር መሳሪዎችን፣ ሰነዶችን እና የፀጥታ አካላት የደንብ አልባሳትን በቁጥጥር ስር ማዋሉን ገለፀ። መንግስት የህግ የበላይነትን ለማስከበር በህወሃት ጁንታ ቡድን ላይ እርምጃ መውሰዱን ተከትሎ ህግ የማስከበር ዘመቻው በድል ተጠናቆ የሀገር መከላከያ ሰራዊት መቀሌን ጨምሮ መላው ትግራይን መቆጣጠሩ ይታወቃል። የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽነር ጌቱ አርጋው ሐምሌ 11 ቀን 2013 ዓ/ም በሰጡት መግለጫ እንዳብራሩት በዚህ ሀገርን የማዳን እና ትግራይን የመታደግ ዘመቻ አብዛኞቹ የጁንታው አመራሮች ሲማረኩ፣ የተወሰኑት ደግሞ ተደምስሰዋል። ወቅቱ … [Read more...] about በአዲስ አበባ 325 የትህነግ አሸባሪዎች ከነመሣሪያቸው ተይዘዋል
ከ 170 በላይ ሴት የጁንታው አባላት በራሱ የጁንታው ታጣቂዎች ተደፍረዋል
በማይካድራ ንጹሃንን ጨፍጭፎ የሸሸው የአሸባሪው የህወሓት ወንጀለኛ ታጣቂ ቡድን በሱዳን መጠለያ ጣቢያዎች የሚገኙ ሴቶችን መድፈሩን በመከላከያ ሰራዊት የተማረኩት የህክምና ባለሙያና ወታደራዊ አመራር የሆኑት ሻምበል ተክለወይኒ ታረቀ ማጋለጣቸውን የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት ዘግቧል። በሱዳን የስደተኛ ጣቢያ ውስጥ ከሚገኙ ከ170 በላይ የሚሆኑት የጁንታው አባላት ሴቶች ላልተፈለገ እርግዝናና ለአባላዘር በሽታዎች መጋለጣቸውንም ምረኮኛው ገልጸዋል። ወንጀል ፈፅመው ወደ ሱዳን የሸሹ የትህነግ ታጣቂዎች በስደተኞቹ ላይ ወሲባዊ ጥቃት እንደሚፈፀሙና በዚህም ያልተፈለገ እርግዝናና የአባላዘር በሽታዎች መስፋፋታቸውን ሲታዘቡ መቆየታቸውን ገልፀዋል። ተክለወይኒ ታረቀ ሻምበል ተክለወይኒ ታረቀ ትውልዳቸውና ዕድገታቸው በሰሜን ምስራቅ ትግራይ ታህታይ አዲያቦ በባድመ አካባቢ ሲሆን ከሰራዊቱ … [Read more...] about ከ 170 በላይ ሴት የጁንታው አባላት በራሱ የጁንታው ታጣቂዎች ተደፍረዋል
ዳግማዊ ዓድዋ – የዓባይ ግድብ በጸጥታው ምክርቤት
የታላቁ የኢትዮጵያ ዓባይ ግድብ ውዝግብ ለመፍታት ጥረት ሲያደርግ የነበረውን የአፍሪካ ኅብረት ሚና አጣጥለው ከተባበሩት መንግሥታት ድርጅት (ተመድ) የፀጥታው ምክር ቤት መፍትሔ ለመሻት የሄዱት የታችኞቹ የዓባይ ተፋሰስ አገሮች ግብፅና ሱዳን፣ የጠበቁትን ሳያገኙ በዓለም አደባባይ ሚናውን ወዳረከሱት የአፍሪካ ኅብረት እንዲመለሱ ተመክረው ተሸኝተዋል። በታላቁ የኢትዮጵያ ዓባይ ግድብ ላይ ሥጋት አለን ከማለት አልፈው የብሔራዊ ደኅንነት ጉዳያቸው እንደሆነ ሲገልጹ የከረሙት ግብፅና ሱዳን፣ እንደ አዲስ በፈጠሩት ጥምረት በሰኔ ወር 2012 ዓ.ም. ጉዳዩን ወደ ተመድ የፀጥታው ምክር ቤት ወስደውት የነበረ ቢሆንም፣ ምክር ቤቱ ቅድሚያ ለአኅጉራዊ የመፍትሔ አማራጭ ቅድሚያ በመስጠት በግድቡ ላይ ያለው ልዩነት በአፍሪካ ኅብረት አደራዳሪነት መፍትሔ እንዲያገኝ በመወሰኑ፣ ላለፈው አንድ ዓመት በዚሁ … [Read more...] about ዳግማዊ ዓድዋ – የዓባይ ግድብ በጸጥታው ምክርቤት
“ለዶሮ በሽታ በሬ ማረድ ትክክል አይደለም” ጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ አህመድ
አንዳንዶች ከሁለት አሥርት ዓመታት በላይ በቆዩበት የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባልነት የመጨረሻ ዘመንና የመጨረሻው ሳምንት ከጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ አህመድ (ዶ/ር) ጋር ሰኔ 28 ቀን 2013. ዓ.ም. በነበራቸው ጥያቄና መልስ፣ በአገሪቱ ታሪክ ከፍተኛ የተባለውን 561 ቢሊዮን ብር የ2014 ዓመታዊ በጀት እንዲሆን የቀረበውን የውሳኔ ሐሳብ በሙሉ ድምፅ በማፅደቅ የመጨረሻ የውሳኔ አሻራቸውን አሳርፈዋል፡፡ በዕለቱ ከፍተኛ የአገሪቱ የመንግሥት ኃላፊዎች፣ ዲፕሎማቶች፣ የተፎካካሪ ፓርቲ መሪዎች፣ የግሉ ዘርፍ ተወካዮችና ሌሎችም አካላት በተገኙበት በዚሁ የፓርላማው ስድስተኛ ዓመት አራተኛ ልዩ ስብሰባ በወቅታዊ ፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ማኅበራዊ ጉዳዮች ላይ ያመዘኑ በርከት ያሉ ጥያቄዎች ከ15 የምክር ቤት አባላት ለጠቅላይ ሚኒስትሩ ቀርበውላቸው ነበር፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ምክር ቤቱን … [Read more...] about “ለዶሮ በሽታ በሬ ማረድ ትክክል አይደለም” ጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ አህመድ
ብቃት ዓልባው ቴድሮስ ዳግም መመረጥ የለበትም-ለተባበሩት መንግሥታት ጥሪ ቀረበ
በአለም ጤና ድርጅት ውስጥ እየጨመረ በመጣው የሥነ ምግባር ጉድለት፤ ማጭበርበርና ጾታዊ ጥቃት የድርጅቱ ዳይሬክተር ዶክተር ቴድሮስ አድሃኖም ከሃላፊነታቸው እንዲነሱ ተጠይቋል። አለም አቀፉ ኢንዲፔንደንት ፋይናንሽያል ኦዲት ባቀረበው የኦዲት ሪፖርት በአለም ጤና ድርጅት ውስጥ የሥነ ምግባር ጉድለት፣ ማጭበርበር፣ ጾታዊ ጥቃትና የሙያ ደረጃዎችን ያልጠበቁ አሰራሮች በከፍተኛ ሁኔታ ጨምረዋል። የአለም ጤና ድርጅት እ.ኤ.አ የ2020 አመታዊ አፈጻጸምን በተመለከተ የኦዲት ሪፖርት ቀርቧል። በዚህም በተቋሙ እየጨመረ የመጣውን የሥነ ምግባር ጉድለት ማጭበርበርና ጾታዊ ጥቃት ተከትሎ የድርጅቱ ዳይሬክተር ለሁለተኛ ጊዜ እንዳይመረጡ የአለም ኤች አይቪ ኤድስ ሄልዚኬር ፋውንዴሽን ጠይቋል። ሪፖርቱ በ2020 የበጀት አመት የአለም ጤና ድርጅት ከ332 ሚሊዮን ዶላር በላይ ከአሰራር ውጪ ከአማካሪ … [Read more...] about ብቃት ዓልባው ቴድሮስ ዳግም መመረጥ የለበትም-ለተባበሩት መንግሥታት ጥሪ ቀረበ
የቴድሮስ “ሥልጣን” – የመጨረሻው መጀመሪያ!?
ከመግቢያው በፊት ይህንን ዘገባ በቴድሮስ አድሃኖም ላይ የሠራነው ከዓመት በፊት April 12, 2020 ነው። ትህነጉ ቴድሮስ አገራችንን ወክሎ የዓለም ጤና ጥበቃ ሃላፊ መሆን እንደሌለበት ገና ለምርጫ ሲወዳደር ጀምሮ አጥብቀን ተቃውመናል። አሁን ወቅቱ የደረሰ ይመስላል። ጥያቄው እየቀረበ ነው። ቴድሮስ አሸባሪውን ህወሃት እስካሁን እየደገፈ ያለ በመሆኑ ብቻ ከሥልጣኑ መወገድ ብቻ ሳይሆን ለፍርድም መቅረብ ያለበት ነው። ዘገባውን በድጋሚ አትመነዋል። እንደ መግቢያ ሰሞኑንን ከኮቪድ - 19 ጋር ተያይዞ የዓለም ጤና ድርጅት ዳይሬክተር ቴድሮስ አድሓኖም አጣብቂኝ ውስጥ መግባቱ ይታወሳል። ኢትዮጵያንና ኢትዮጵያዊነትን ካወደመው፣ የዘር ፖለቲካን ከሚያራምደው ፍጹም ጽንፈኛና ዘረኛ፣ እንዲሁም በከፍተኛ ደረጃ ኢትዮጵያውያንን በዘራቸው፣ በፖለቲካ እምነታቸው ካኮላሸ፣ ከጨፈጨፈ፣ ቶርቸር … [Read more...] about የቴድሮስ “ሥልጣን” – የመጨረሻው መጀመሪያ!?