• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“ምኒልክ ዛሬም ንጉሥ ነው!”

March 2, 2022 12:53 pm by Editor 1 Comment

የዓለም ህዝብ ሁሉ ለመጀመሪያ ጊዜ ነጭን ድል ያደረገውን የጥቁር ጦር መሪ አጤ ምኒልክን ለማወቅ እጅግ ጓጓ፡፡

ምስላቸውን ለማየት ተቁነጠነጠ፡፡

ሙሉ ታሪካቸውን ለመስማት ተንሰፈሰፈ፡፡

ይህንኑ ተከትሎም፤ “እንኳንም ደስ አለዎት” ለማለት ከቁጥር የበዙ ደብዳቤዎች ይጎርፉላቸው ነበር፡፡ ከነዚህ ውስጥ አንዳንዶቹ በፖስታ ቤት በኩል የኢትዮጵያ ቴምብር የተለጠፈበት መልስ እንዲላክላቸው ይጠይቁ ነበር፡፡

ለምን… ?

ቴምብሩ ላይ ያለውን የምኒልክን መልክ ለማየት፡፡

ባለ ብዙ ዝናና ክብር ባለቤት የሆኑትን የምኒልክን ጥቁር ፊት ለማየት፡፡

የሰው ሀገር ሰው ሁሉ፤ “ዝናውን እንደሰማሁ መቼ ሄጄ ባየሁት”፣ “በጀግንነቱ እንደ ተማረኩ መች ተጉዤ ባገኘሁት”፣ “ካሁን ካሁን ፈቅዶልኝ ወታደር ሆኜ ባገለገልኩት” ያለላቸው አጤ ምኒልክ የኛ ናቸው፡፡

በዓለም ታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ ነጭን ያንበረከከ የጥቁር ጦርን የመሩት ንጉስ የኛ ናቸው፡፡

መወድስ የማይበዛበት የአድዋ ድልም የኛ ነውና፣

እንኳን ትላንትም፣ ዛሬም፣ ነገም ለምንኮራበት በዓላችን በጤንነት አደረሰን! (ምንጭ: ነቆራ እና ሌሎችም ወጎች ከሕይወት እምሻው ጋር – Hiwot Emishaw)

በድጋሚ የተለጠፈ

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Middle Column, Politics, Slider

Reader Interactions

Comments

  1. Tesfa says

    March 3, 2022 12:15 pm at 12:15 pm

    ጉልበተኛ ዓለምን እንደሚገዛና እንደሚያስገዛ ቀደም ብለን የምናውቀው ጉዳይ ቢሆንም አሁን የራሽያ ወደ ዪክሬን መግባት በጉዳዪ ላይ ላመነታ ማሳመኛ መድሃኒት ነው። ረጅም በትር ባይመቱበት ያስፈራሩበት ያሉት አበው ሲፈለግ እንደሚመታበትም አውቀው ነው። ይገርማል አሁን በ 140 ሃገሮች የተኮነነችው ሩሲያ ያው ውጊያውን አፋፍማዋለች። የአህያ ባል ከጅብ አያድንም እንዲሉ በፊት ከሩቅና ከቅርብ ሆነው ሲለፈልፉ የነበሩ ሃያላን መንግስታትም ሆነ ተለጣፊ መንግስታት ምንም ማድረግ አልቻሉም። ያው ለዘመናት ሲያረጉ እንደነበሩት በርቀት እሳት ያቀብላሉ።
    ወደ አድዋው ድልና አሁን በሃበሻዋ ምድር የሚታየውን የፓለቲካ አተካራና የመገዳደል ዘዬ ተራምደን ከዘመናት በፊት ማንበብና መጻፍ እምብዛም የማይችሉት ለሃገራቸው አንድነት ከጠላት ጋር ተዋድቀው ያቆዪልንን ሃገር እድሜ ለትግራይ ተገንጣይ ቡድን በዘርና በቋንቋ ተሸንሽና አሁን ያለችበት የሰዶ ማሳደድ የዘር ፓለቲካ ላይ ደርሰናል። የአሁኑ ትውልድ ካለፈው የሚልቅበት ኢምንት ነገር የለም። አለ ከተባለም ትቢያ ነው። ያኔ ሰው ሰው ሆኖ ሲያድር ምንም የሃገሪቱ ተወላጅ የትም ሂዶ ሰርቶ የመኖር መብት ነበረው። አሁን ደግሞ ሁሉም በየጓዳህ ስለተባለ ነገሩ ሁሉ ለሚመለከተው አይነ ሸውራራ ያረጋል። እስቲ እንበልና የዳግማዊ አጼ ሚኒሊክ ድል ሽንፈት ሆኖ ቢሆን ኑሮ ዛሬ በቋንቋ፤ በሃይማኖት፤ ወይም በሌላው ሃበሻው ይዣለጥ ነበርን? ጭራሽ። የጣሊያን ቋንቋ ተናጋሪና ካቶሊክ ነበር የሚሆነው። ይህን ለመረዳት ደቡብ አሜርካን ከብራዚል በስተቀር የስፔን ወራሪዎች እንዴት እንደለወጧቸው ማየት በቂ ነው። ብራዚልም ቢሆን ከአፍሪቃ እልፍ ጥቁሮችን በባርነት ታጓጉዝ የነበረችው ፓርቹጋል የፓርቹጊዝ ተናጋሪ ብራዚልን አርጓታል። ዛሬ በቺሌ፤ በአርጀንቲና በሌሎችም የዚህ ክፍለ ሃጉር የናጠጡ ኗሪዎች መጤዎች ናቸው። ይበልጦቹ ከሁለቱም የዓለም ጦርነቶች በህዋላ የተሰደድ ናቸው። ግን አሁን ሃገራቸው ነው። ይኖሩበታል። ተዋልደውል። የሃበሻው የገማ ፓለቲካ የዛሬ መቶ ዓመት እንዲህ አይነት በደል ደርሶብኛልና ልበቀል የሚል ጥላቻን የተላበሰ የድንበር ገተር ህልፈተ ቢስ የፓለቲካ እይታ እየቆየን እንድንቀጭጭና በረሃብና በቸንፈር እንድንጠቃ አርጎናል። ዛሬ እኔ አማራ ነኝ፤ እኔ ኦሮሞ ነኝ፤ ያ ደግሞ ከደቡብ ነው፤ ይህ ደግሞ ከትግራይ ነው የምንለው ሁሉ የአድዋ ድል በድል ባይጠናቀቅ ኑሮ አይኖርም። ያ ድል የሁለተኛውን የጣሊያን የብቀላ ወረራ ሁሉ ሃገሬው እንዲመክት ያስቻለው የማይነቃነቅ የነጻነት ምሰሶ ነበር፤ ነውም። የሃበሻን አልገዛም ማለት ያዪ የአፍሪቃ ሃገሮችም ነቅተው፤ ታጥቀው በመታገላቸው ዛሬ ግማሾቹ ለህዝባቸው በሚያቀርቧቸው አገልግሎቶች ቀድመውን ሂደዋል። እኛ ግን ከጨካኝ ወደ ሌላ ጨካኝ ስንሸጋገር ባለንበት እንኳን ለመኖር ተስኖን አዲስ ፈሊጥና የመጨቆኛ ዘዴ እያወጣን የቆመን በማፍረስ ላይ እንገኛለን።
    ባጭሩ ዛሬ ኢትዮጵያ አትፈርስም የሚሉን አፍራሽ ሥራ እየሰሩ ነው። ደግሞም በዚህ አያያዝ ኢትዮጵያ የማትፍረከረክበት ምንም ምክንያት የለም። ፈክሮ ከማፋከር ይልቅ በመሬቷ ላይ የሚወርደውን የመከራ ዝናብ ለመግታት በአንድነት መነሳት ተገቢ ነው። ሶሪያ፤ ኢራቅ፤ ሊቢያ፤ የመን ወዘተ የተንኮታኮቱት አንፈርስም እያሉ ነው። አሁን ባለው የፓለቲካ አሰላለፍ (ራሺያና ቀሪው ዓለም) ነገ ምን ይዞ እንደሚመጣ የሚገምት አለ? ጭራሽ። ስለሆነም ከዘመናት በፊት በህብረ ተጋድሎ ያስረከቡንን ሃገር ህልውና ለማስቀጠል የአድዋን ድል በየአመቱ ከማክበር ባሻገር እኔ ለሃገሬ ለወገኔ ዘርና ቋንቋን ወይም ሃይማኖትን መሰረት ስላደርግ ምን ሰራሁ በማለት ራሳችን ጠይቀን የምንችለውን ሁሉ ማድረግ ይኖርብናል። በቃኝ!

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • በጦርነቱ የተጎዱ አካባቢዎችን ለማቋቋም የሚውል የ15 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር ድጋፍ የዓለም ባንክ May 16, 2022 10:22 am
  • በአዲስ አበባ 1 ሺህ 98 የብሬን እና 2 ሺህ 162 የክላሽ ጥይት ተያዘ May 16, 2022 10:10 am
  • በአዲስ አበባ ከተማ በግለሰብ መኖሪያ ቤት ከ5 ሺህ በላይ የአሜሪካ ዶላርና የተለያዩ አገራት ገንዘቦች ተያዙ May 16, 2022 09:53 am
  • አገር አፍራሹ ትህነግ ለቀለብ፣ መድኃኒትና ሥራ ማስኬጃ 76 ቢሊዮን ብር ቀርጥፏል May 16, 2022 08:30 am
  • እየተባባሰ ከመጣው የማህበራዊ ሚዲያ አጭበርባሪዎች ዜጎች ራሳቸውን እንዲጠብቁ ተጠየቀ May 15, 2022 09:38 am
  • የትህነግና ሸኔ መሠልጠኛ የምትባለው ዩጋንዳ መከላከያ ሚ/ር ከኤታማዦር ሹሙ ጋር ተወያዩ May 13, 2022 09:55 am
  • በትግራይ የውጊያ ምልመላው ጉዳይ May 11, 2022 02:37 am
  • መከላከያ በተጨማሪ ድሮን፣ በሥልጠና፣ በዝግጅት ራሱን አብቅቷል May 11, 2022 01:35 am
  • ትህነግ ለሌላ ውጊያ እየተዘጋጀ ነው ተባለ May 10, 2022 01:04 pm
  • ኤርትራ 8 ሩስያ ሠራሽ ድሮኖችን ተረክባለች May 10, 2022 12:37 am
  • ሙስሊምና ክርስቲያን በአንድነት የሚያከብረው የአኾላሌ ባሕላዊ ጭፈራ May 9, 2022 01:46 pm
  • በወልዲያ ፋኖዎች ተመረቁ May 9, 2022 12:51 pm
  • “ሠራዊታችን ድልን በአስተማማኝ መልኩ ማምጣት በሚችል ቁመና ላይ” ጀኔራል ጌታቸው May 9, 2022 11:57 am
  • ዋጋው 64 ሚሊዮን ብር የሚሆን (16 ኪሎ) ሕገወጥ ወርቅ ተያዘ May 9, 2022 11:51 am
  • አብን ክርስቲያን ታደለን ለመጨረሻ ጊዜ አስጠነቀቀ፤ 10 አባላቱን አገደ May 9, 2022 08:58 am
  • ራሱ አቡክቶ፣ ራሱ አሟሽሾ፣ ራሱ ጋግሮ በሰዓት 460 እንጀራ የሚያወጣ ፈጠራ May 9, 2022 08:17 am
  • በህገ ወጥ መንገድ 19 ህጻናትን ሲያዘዋወሩ የነበሩ 6 ሴቶች ተያዙ May 8, 2022 12:39 am
  • በአርሲ ሙስሊሞች ለቤ/ክ ማሠሪያ 3 ሚሊዮን ብርና 20 የቀንድ ከብት ሰጡ May 6, 2022 09:35 am
  • በአዲስ አበባ የሚኖረው የትህነግ ደጋፊ ማንነት በማስረጃ May 4, 2022 11:04 pm
  • ሙስሊም ወንድማማች የቤ/ክ ዘራፊዎችን በቁጥጥር ሥር አዋሉ May 4, 2022 09:04 am
  • ከ6 ሺህ የዓሳ ጫጩት ወደ 80 ሺህ May 4, 2022 08:57 am
  • ተስፋቢሱ ቴድሮስ May 3, 2022 12:16 pm
  • ከሽፏል! April 6, 2022 11:58 am
  • “ሩሲያ ዩክሬይንን ወረረች” እየተባለ ስለሚነዛው ወሬ ጥቂት እውነታዎች March 8, 2022 11:30 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2022 · Goolgule