• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“ምኒልክ ዛሬም ንጉሥ ነው!”

March 2, 2022 12:53 pm by Editor 1 Comment

የዓለም ህዝብ ሁሉ ለመጀመሪያ ጊዜ ነጭን ድል ያደረገውን የጥቁር ጦር መሪ አጤ ምኒልክን ለማወቅ እጅግ ጓጓ፡፡

ምስላቸውን ለማየት ተቁነጠነጠ፡፡

ሙሉ ታሪካቸውን ለመስማት ተንሰፈሰፈ፡፡

ይህንኑ ተከትሎም፤ “እንኳንም ደስ አለዎት” ለማለት ከቁጥር የበዙ ደብዳቤዎች ይጎርፉላቸው ነበር፡፡ ከነዚህ ውስጥ አንዳንዶቹ በፖስታ ቤት በኩል የኢትዮጵያ ቴምብር የተለጠፈበት መልስ እንዲላክላቸው ይጠይቁ ነበር፡፡

ለምን… ?

ቴምብሩ ላይ ያለውን የምኒልክን መልክ ለማየት፡፡

ባለ ብዙ ዝናና ክብር ባለቤት የሆኑትን የምኒልክን ጥቁር ፊት ለማየት፡፡

የሰው ሀገር ሰው ሁሉ፤ “ዝናውን እንደሰማሁ መቼ ሄጄ ባየሁት”፣ “በጀግንነቱ እንደ ተማረኩ መች ተጉዤ ባገኘሁት”፣ “ካሁን ካሁን ፈቅዶልኝ ወታደር ሆኜ ባገለገልኩት” ያለላቸው አጤ ምኒልክ የኛ ናቸው፡፡

በዓለም ታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ ነጭን ያንበረከከ የጥቁር ጦርን የመሩት ንጉስ የኛ ናቸው፡፡

መወድስ የማይበዛበት የአድዋ ድልም የኛ ነውና፣

እንኳን ትላንትም፣ ዛሬም፣ ነገም ለምንኮራበት በዓላችን በጤንነት አደረሰን! (ምንጭ: ነቆራ እና ሌሎችም ወጎች ከሕይወት እምሻው ጋር – Hiwot Emishaw)

በድጋሚ የተለጠፈ

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Middle Column, Politics, Slider

Reader Interactions

Comments

  1. Tesfa says

    March 3, 2022 12:15 pm at 12:15 pm

    ጉልበተኛ ዓለምን እንደሚገዛና እንደሚያስገዛ ቀደም ብለን የምናውቀው ጉዳይ ቢሆንም አሁን የራሽያ ወደ ዪክሬን መግባት በጉዳዪ ላይ ላመነታ ማሳመኛ መድሃኒት ነው። ረጅም በትር ባይመቱበት ያስፈራሩበት ያሉት አበው ሲፈለግ እንደሚመታበትም አውቀው ነው። ይገርማል አሁን በ 140 ሃገሮች የተኮነነችው ሩሲያ ያው ውጊያውን አፋፍማዋለች። የአህያ ባል ከጅብ አያድንም እንዲሉ በፊት ከሩቅና ከቅርብ ሆነው ሲለፈልፉ የነበሩ ሃያላን መንግስታትም ሆነ ተለጣፊ መንግስታት ምንም ማድረግ አልቻሉም። ያው ለዘመናት ሲያረጉ እንደነበሩት በርቀት እሳት ያቀብላሉ።
    ወደ አድዋው ድልና አሁን በሃበሻዋ ምድር የሚታየውን የፓለቲካ አተካራና የመገዳደል ዘዬ ተራምደን ከዘመናት በፊት ማንበብና መጻፍ እምብዛም የማይችሉት ለሃገራቸው አንድነት ከጠላት ጋር ተዋድቀው ያቆዪልንን ሃገር እድሜ ለትግራይ ተገንጣይ ቡድን በዘርና በቋንቋ ተሸንሽና አሁን ያለችበት የሰዶ ማሳደድ የዘር ፓለቲካ ላይ ደርሰናል። የአሁኑ ትውልድ ካለፈው የሚልቅበት ኢምንት ነገር የለም። አለ ከተባለም ትቢያ ነው። ያኔ ሰው ሰው ሆኖ ሲያድር ምንም የሃገሪቱ ተወላጅ የትም ሂዶ ሰርቶ የመኖር መብት ነበረው። አሁን ደግሞ ሁሉም በየጓዳህ ስለተባለ ነገሩ ሁሉ ለሚመለከተው አይነ ሸውራራ ያረጋል። እስቲ እንበልና የዳግማዊ አጼ ሚኒሊክ ድል ሽንፈት ሆኖ ቢሆን ኑሮ ዛሬ በቋንቋ፤ በሃይማኖት፤ ወይም በሌላው ሃበሻው ይዣለጥ ነበርን? ጭራሽ። የጣሊያን ቋንቋ ተናጋሪና ካቶሊክ ነበር የሚሆነው። ይህን ለመረዳት ደቡብ አሜርካን ከብራዚል በስተቀር የስፔን ወራሪዎች እንዴት እንደለወጧቸው ማየት በቂ ነው። ብራዚልም ቢሆን ከአፍሪቃ እልፍ ጥቁሮችን በባርነት ታጓጉዝ የነበረችው ፓርቹጋል የፓርቹጊዝ ተናጋሪ ብራዚልን አርጓታል። ዛሬ በቺሌ፤ በአርጀንቲና በሌሎችም የዚህ ክፍለ ሃጉር የናጠጡ ኗሪዎች መጤዎች ናቸው። ይበልጦቹ ከሁለቱም የዓለም ጦርነቶች በህዋላ የተሰደድ ናቸው። ግን አሁን ሃገራቸው ነው። ይኖሩበታል። ተዋልደውል። የሃበሻው የገማ ፓለቲካ የዛሬ መቶ ዓመት እንዲህ አይነት በደል ደርሶብኛልና ልበቀል የሚል ጥላቻን የተላበሰ የድንበር ገተር ህልፈተ ቢስ የፓለቲካ እይታ እየቆየን እንድንቀጭጭና በረሃብና በቸንፈር እንድንጠቃ አርጎናል። ዛሬ እኔ አማራ ነኝ፤ እኔ ኦሮሞ ነኝ፤ ያ ደግሞ ከደቡብ ነው፤ ይህ ደግሞ ከትግራይ ነው የምንለው ሁሉ የአድዋ ድል በድል ባይጠናቀቅ ኑሮ አይኖርም። ያ ድል የሁለተኛውን የጣሊያን የብቀላ ወረራ ሁሉ ሃገሬው እንዲመክት ያስቻለው የማይነቃነቅ የነጻነት ምሰሶ ነበር፤ ነውም። የሃበሻን አልገዛም ማለት ያዪ የአፍሪቃ ሃገሮችም ነቅተው፤ ታጥቀው በመታገላቸው ዛሬ ግማሾቹ ለህዝባቸው በሚያቀርቧቸው አገልግሎቶች ቀድመውን ሂደዋል። እኛ ግን ከጨካኝ ወደ ሌላ ጨካኝ ስንሸጋገር ባለንበት እንኳን ለመኖር ተስኖን አዲስ ፈሊጥና የመጨቆኛ ዘዴ እያወጣን የቆመን በማፍረስ ላይ እንገኛለን።
    ባጭሩ ዛሬ ኢትዮጵያ አትፈርስም የሚሉን አፍራሽ ሥራ እየሰሩ ነው። ደግሞም በዚህ አያያዝ ኢትዮጵያ የማትፍረከረክበት ምንም ምክንያት የለም። ፈክሮ ከማፋከር ይልቅ በመሬቷ ላይ የሚወርደውን የመከራ ዝናብ ለመግታት በአንድነት መነሳት ተገቢ ነው። ሶሪያ፤ ኢራቅ፤ ሊቢያ፤ የመን ወዘተ የተንኮታኮቱት አንፈርስም እያሉ ነው። አሁን ባለው የፓለቲካ አሰላለፍ (ራሺያና ቀሪው ዓለም) ነገ ምን ይዞ እንደሚመጣ የሚገምት አለ? ጭራሽ። ስለሆነም ከዘመናት በፊት በህብረ ተጋድሎ ያስረከቡንን ሃገር ህልውና ለማስቀጠል የአድዋን ድል በየአመቱ ከማክበር ባሻገር እኔ ለሃገሬ ለወገኔ ዘርና ቋንቋን ወይም ሃይማኖትን መሰረት ስላደርግ ምን ሰራሁ በማለት ራሳችን ጠይቀን የምንችለውን ሁሉ ማድረግ ይኖርብናል። በቃኝ!

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule