• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የትህነግ የጦር መሳሪያ ዝውውር ኮሪደሮቹ

February 17, 2022 02:51 am by Editor Leave a Comment

ራሱን የትግራይ ሕዝብ ነጻ አውጪ ግምባር (ህወሓት/ትህነግ) በማለት የሚጠራውና በኢትዮጵያ እጅግ አስከፊ የሚባልና ትውልድን ያወደመ ርዕዮት በመከተል አገር ያፈረሰው የወንበዴዎች ጥርቅም፤ እስካሁንም በዓለምአቀፍ የአሸባሪዎች የመረጃ ቋት በአሸባሪነት ተመዝግቦ የሚገኝ ድርጅት መሆኑ ይታወቃል። አባላቱና ደጋፊዎችም በዚሁ ሁኔታ የሚታዩ መሆናቸውን ብዙዎች የሚስማሙበት ነው።

በአገራችን ባለፉት ሁለት ዓመታት ያህል በእጅጉ ተንሰራፍቶ ከሚገኙት ሦስት ሕገወጥ ሥራዎች መካከል አንዱ ሕገወጥ የጦር መሣሪያ ዝውውር ነው። ሌሎቹ ሁለቱ ደግሞ ሕገወጥ የገንዘብ ዝውውርና ሐሰተኛ የዜና ዘገባዎች ናቸው። በሦስቱም ውስጥ አሸባሪው ህወሓት እጁ እንዳለበት በርካታ ጠቋሚ መረጃዎች አሉ።

ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ድብቅ ምሥጢራትን በማውጣት የሚታወቀው ethio wiki leaks “ህወሓት እና የጦር መሳሪያ ዝውውር ኮሪደሮቹ” በሚል ርዕስ ባወጣው አጭር የመረጃ ዘገባ ላይ ህወሓት ህገወጥ የጦር መሣሪያ የሚያዘዋውርበት መስመሮችን አቅርቧል፤ ለዚህም ድርጊቱ ለኢትዮጵ ብቻ ሳይሆን ለአፍሪካ ቀንድም ስጋት በመሆኑ በኢጋድ እንዲሁም በዓለምአቀፉ ፍርድቤት በኃላፊነት እንዲጠየቅ ይገባል ብሏል።

የፌዴራሉ መንግሥት በዚህ ጉዳይ ላይ ከባለሞያዎች ጋር በመነጋገር ተግባራዊ ቢያደርግ ብዙዎች የሚደግፉት ሃሳብ እንደሆነ ይገመታል።  

“ህወሓት እና የጦር መሳሪያ ዝውውር ኮሪደሮቹ”

ባለፉት ሃያ ወራት በፖለቲካና የሽብር ተግባሮቹ ተግቶ ሲንቀሳቀስ የነበረው ህወሓት የጦር መሳሪያ ክምችትን ጨምሮ በዝውውር ላይ ተሳትፎ እያደረገ ይገኛል።

የጦር መሳሪያዎቹ የነፍስ ወከፍና የቡድን ተብለው በሁለት ሊከፈሉ ይችላል። ጦር መሳሪያዎቹ በሱዳን በኩል ባለው መስመር እንዲገቡ የሚያደርግ ሲሆን÷ የጦር መሳሪያዎቹ መነሻ ከቱርክና ከሰሜን አፍሪቃ ሀገራት እንደሆነ መረጃዎች ያመለክታሉ ።

የጦር መሳሪያ መተላለፊያ ኮሪደሮቹ፤

ከሱዳን ሱፍ ውሃና ወዲ ኢሎ አድርጎ ሉግዲ ሁመራ የሚያስገባው መስመር የጦር መሳሪያ ዝውውር የሚካሄድበት ዋና ኮሪደር ነው።

የወልቃይት ምድር የሆነችው ሉግዲ በምዕራባዊ የትግራይ ዞን ስር የምትገኝ የድንበር ከተማ ናት።

ከሱዳን የድንበር አካባቢዎች (በዋናነት ወዲ ኢሎ እና ሱፍ ውሃ) በኩል ተሻግሮ የሚገባ በርካታ የጦር መሳሪያ የሚከማችባትና የሚሰራጭባት ማዕከል ነች።

በምስሉ ላይ በቀይ የተመለከተችው ቦታ ‘ሉግዲ’ ትሰኛች

ሉግዲ ይህ ነው የሚባል የፌዴራሉ የፀጥታና ደህንነት (መከላከያ፣ ፌዴራል ፖሊስ) መዋቅር የሌለባት ነፃ ቀጣና ስትሆን፤ በሉግዲ በኩል የሚገባው የጦር መሳሪያ በሁመራ በኩል በሁለት አቅጣጫ ይሰራጫል።

በሽሬ በኩል ወደ መሀል ትግራይ የሚገባው አንደኛው መስመር ሲሆን፤ ከሁመራ ወደ ጎንደርና መሀል አገር የሚሰራጭበት ደግሞ ሁለተኛው መስመር ነው። ወደትግራይ የሚሄደው የክምችቱ አካል ሲሆን÷ በጎንደር በተለያዬ አቅጣጫ ወደመሀል አገር የሚላከው ደግሞ የሽብርና የንግዱ አካል ነው ።

ሉግዲ ላይ ያለው የጦር መሳሪያ ዝውውር የሶሪያዋን ምዕራብ ‘አሊፖ’፣ የሊቢያዋን ‘ቤንጋዚ’፣ የየመኗን ‘ታአዝ’ እና ‘አርሃብ’ ከተማ የሚመስል ነው። ልዮነቱ እነዚህ ከተሞች የእርስ በርስ ጦርነት የሚካሄድባቸው የጦር ቀጣና መሆናቸው ሲሆን፤ ሉግዲ ደግሞ ጎረቤቶቹን በሽብር እያመሰ ራሱን ለነፃ ሀገር ምስረታ እያዘጋጀ ባለው ድርጅት [ህወሓት] ስር ያለች  የጦር መሳሪያ ማስገቢያ ኮሪደር  ማዕከል መሆኗ ብቻ ነው።

በትንሿ የድንበር ከተማ ሉግዲ በኩል ህወሓት ምን እየሰራ እንዳለ ማዕከላዊው መንግሥት ያውቃል ። ዝምታው ይሄን ያህል ተራዛሚ የሆነበት ምክንያት ለማናችንም ግልፅ አይደለም‼

የአገሪቱ ዳር ድንበር በመከላከያ ሰራዊት እንደሚጠበቅ በአዋጅ የተደነገገ ጉዳይ ሆኖ እያለ ÷ ቀጣናው ላይ ጥበቃው የላላ መሆኑ÷ በአካባቢው የህወሓት ጦር በእጥፍ እየተንቀሳቀሰ እንደሚገኝ በቂ መረጃዎች አሉ ።

የማዕከላዊው መንግሥት የትኩረት አቅጣጫ በኤርትራ ‘ሱከቱር’ እና በሱዳን ‘ሐምዳይት’ በኩል ብቻ መሆኑ÷ ህወሓት በሉግዲ በኩል የራሱን የጦር መሳሪያ ዝውውር ኮሪደር ከፍቷል።

የጦር መሳሪያ ዝውውር ውስጥ እጁን የዘፈቀው ይሄ አውሬ ድርጅት ኢትዮጵያን የደም ኩሬ ለማድረግ ተግቶ እየሰራ ነው።

በማዕከላዊው መንግሥት ስር ያሉት÷ የፀጥታና ደህንነት ተቋማት ባለፈው አንድ ዓመት ብቻ በጦር መሳሪያ ዝውውርና ሕገወጥ ትጥቅ በሚል 40,000 የጦር መሳሪያ መወረሱን ትላንት አንድ official ሪፖርት ላይ ያገኘሁት መረጃ ያመለክታል።

ለሽብር ቡድኖች እገዛ በማድረጉ÷ ሽብርንም በማበረታታቱ ከማዕከላዊው መንግሥት በኀይል የተወገደው ታሊባን ቶራቦራን የሙጥኝ ብሎ አያሌ የሽብር ጥፋቶችን እንዳደረሰ ይታወቃል። ዛሬም ወደ መንግሥትነት ለመመለስ ባለፈበት የ18 ዓመት የሽብር ተልዕኮው ላይ ይገኛል።

ታሊባን ለሽብር ተግባራቱ የፋይናንስ እና የሎጀስቲክስ ፍላጎቶቹን እያሟላ ያለው ድራግን ጨምሮ የጦር መሳሪያ ንግድና ሌሎች የኮንትሮባንድ ስራዎችን በመስራት ነው።

አሁን ህወሓት ከታሊባን የተለየ ተግባር እያከናወነ አይደለም። የጦር መሳሪያ ዝውውሩ አንድም የፋይናንስ አቅሙን ይጨምርለታል ። ሁለትም በጎረቤትና በመሀል አገር ኢንሰርጀንሲን ጨምሮ ሌሎች የሽብር ተግባራት እንዲበራከቱ ለማድረግ እየተጠቀመበት ይገኛል።

ህወሓት የአፍሪቃ ቀንድ የሠላምና ደኀንነት ስጋት ነው

ማዕከላዊው መንግሥት ከኢጋድ እና የአፍርቃ ሕብረት ጋር በመመካከር በሕግ እንዲታገድ ብሎም መሪዎቹ በICC እንዲጠይቁ በጋራ ተቀናጅተው ሊሰሩ ይገባል

ጊዜው በረዘመ ቁጥር ቀጣናው ወደ አስከፊ ትርምስ ውስጥ መግባቱ አይቀሬ ነው

ከአዘጋጆቹ፤ ይህ ዘገባ (December 8, 2019) ታትሞ የነበረ ሲሆን አሁን አስፈላጊነቶ ታይቶ በድጋሚ የታተመ ነው

ጎልጉል፤ የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Middle Column, Politics Tagged With: illegal weapon, operation dismantle tplf

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ባልደራስ የአገርን ደኅንነት አደጋ ላይ በመጣል ሊጠየቅ ይገባዋል ተባለ July 1, 2022 09:23 am
  • “ሚካኤል ችግኝ ነው። … ችግኝ ይተክላል” ቴዲ አፍሮ June 29, 2022 03:30 am
  • “የእኔን ልጆችና የልጅ ልጆች (22ቱንም) የቀበርኩት እኔ ነኝ” አቶ መሀመድ የሱፍ ከምዕራብ ወለጋ June 28, 2022 01:07 pm
  • የገዳ ሥርዓት እና የኦሮሞ ገዢ መደብ June 20, 2022 11:34 pm
  • “የወልቃይትን ጉዳይ ለድርድር የማናቀርበው ቀይ መስመራችን ነው” ርዕሰ መስተዳድር ይልቃል June 12, 2022 07:09 pm
  • የሰሜን ምዕራብ ዕዝና የአማራ ልዩ ኃይል ተከዜ ክፍለ ጦር ዕውቅናና ሽልማት ተሰጣቸው June 12, 2022 06:21 pm
  • ሀገር በቀል ባህላዊ የግጭት አፈታቶችን በተገቢው በመጠቀም ዘላቂ እርቅና ሰላምን ማምጣት ይቻላል June 12, 2022 05:40 pm
  • የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን በገረጂና በቀበና ያስገነባቸውን የመኖሪያ አፓርትመንቶች አስመረቀ June 12, 2022 05:35 pm
  • በኦነግ ሸኔ ፈርሶ የነበረውና ወታደራዊ ጠቀሜታ ያለው ድልድይ ተጠግኖ አገልግሎት መስጠት ጀመረ June 10, 2022 09:13 am
  • ጃዋር በዳውድ ኢብሣ ቀይ መስመር ተሰመረለት June 8, 2022 12:59 pm
  • ወልቃይት: ቢመረንም ለመዋጥና ራሳችንን ለመመልከት እንሞክር June 8, 2022 11:53 am
  • እብድ ይሻለዋል እንጂ አይድንም፤ ሐጂ ጃዋር አሁን ለምን ብቅ አለ? June 8, 2022 05:59 am
  • ሕዝብ ድምፅ የነፈጋቸው “ፓርቲዎች” የሽግግር መንግሥት ይቋቋም አሉ June 7, 2022 01:11 am
  • “አድጌ እንደናንተ መሆን እፈልጋለሁ” June 5, 2022 06:58 pm
  • በሳምንት ለ100 ያህል ሕሙማን አገልግሎት የሚሰጥ የኩላሊት ዕጥበት ማዕከል ሥራ ጀመረ May 30, 2022 02:20 am
  • የጥቁር አንበሳ ዕጩ መኮንኖች (ካዴቶች) ተመረቁ May 29, 2022 04:01 pm
  • “ኢትዮጵያን መንካት አይቻልም!!” በሚል ቁጭት ነው እየሠራን ያለነው May 29, 2022 01:04 pm
  • “ከሞፈርና ቀንበር ወደ ትራክተር” በሚል መርህ ለአማራ ገበሬዎች የግብርና ሜካናይዜሽን ተሰጠ May 29, 2022 02:02 am
  • ኢትዮ 360 “የወያኔ፣ የጁንታ ሚዲያ ነው” – ባለከዘራው ጄኔራል May 27, 2022 02:51 am
  • “እኛ የምናውቀው ነገር የለም፤ የሚያጣሉን ፖለቲከኞች ናቸው” የአማራ ወዳጃቸውን አደራ ቤት የመለሱ የቅማንት ተወላጅ May 27, 2022 01:40 am
  • ትግራይን አገር እናደርጋለን፤ “በውይይት እና በጦርነት” ሁሉንም ጉዳይ እንቋጫለን – የወንበዴው መሪ ደብረጽዮን May 26, 2022 09:18 am
  • “ሁለቱ የምዕራብ ዕዝ ተዋጊ ዶክተሮች” May 26, 2022 08:19 am
  • ወደ ትህነግ ሊተላለፍ የነበረ አምስት ሚሊዮን ብር ከ20 ተጠርጣሪዎች ጋር ተያዘ May 25, 2022 01:57 am
  • የጦርነቱ ስትራቴጂያዊ እውነታዎች May 19, 2022 09:37 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2022 · Goolgule