" ... ዓለም ከተፈጠረ ጀምሮ አሁን እስካለንበት ድረስ ታሪኩን መለስ ብለን ብንመለከት በሰው ዘር ላይ ግዛታቸውን ለመዘርጋት፣ ሰውን ባካልም ሆነ በመንፈስ ለመግዛት፣ ሁለት ተቃራኒ ኃይሎች ሲታገሉ እናያለን፡፡ ከነዚህ አንዱ የሀይለኞች፣ ያጥቂዎች፣ የጦር ኃይል፣ ሁለተኛው የደራሲያን የብእር ኃይል ናቸው፡፡ "የጦር ኃይል በየጊዜው፣ በየቦታው የሚነሱ ኃይለኞች ሰራዊት አደራጅተው፣ የጦር መሳሪያ አከማችተው፣ ሰውን እየጨቆኑ ለግል ድሎታቸውና ፍላጎታቸው አገልጋይ የሚያደርጉበት እውር ሀይል ነው፡፡ የብእር ኃይል በየጊዜው በየቦታው የሚነሱ ታላላቅ ደራሲያን ከስው ተለይተው፣ ከብእርና ከወረቀታቸው ጋር በየቤታቸው ተዘግተው፣ ምስጢረ ፍጥረትን እየመረመሩ፣ አዳዲስ ነገር እየፈጠሩ፣ ሰውን ከድንቁርና ሰንሰለት ተፈትቶ፣ ከእንሰሳ ባህርያት ጠርቶ፣ የመንፈስና የአካል ነጻነት አግኝቶ፣ ስርአት ያለው … [Read more...] about “… የጦር ኃይል … እና የብእር ኃይል …” ሃዲስ አለማየሁ
Literature
ጽፈኪን
“ምጽአተ ዐማራ” አዲስ መጽሐፍ
ይህ መጽሐፍ ባለ 657 ገፆች ነው። በዘጠኝ ምዕራፎች ተከፋፍሏል። እነርሱም፦ የኢትዮጵያና ኢትዮጵያዊነት መከፋፈል፣ የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ኃይማኖት ተከታዩና ዐማራው የከፈሉት ዋጋ የኢትዮጵያ አንድነት ትንሣኤ፣ የዐማራው የአንድነትና የፀረ-አንድነት ትግል ውጤት ቀዳማዊ ኃይለሥላሴ፤ የፍፁማዊ ዘውዳዊ አገዛዝ የአንድነት ግንባታ ሂደት ድምድም እና የኢትዮጵያ ዳግም ብተና ጽንስ የለውጥ ፈላጊው ትውልድ የኃይል አሰላለፍ ዘረኛው የትግሬ-ወያኔ ከ1972 እስከ 2007 ዓም ድረስ በዐማራው ነገድ ላይ ያደረሰው የዘር ማጥፋትና የዘር ማጽዳት ወንጀል ስለ ዐማራና ስለ ኢትዮጵያዊነት ምሑራን ምን ይላሉ? የመላው ዐማራ ሕዝብ ድርጅት (መዐሕድ)፦ ዐማራው ላይ የደረሰው ሰቆቃ የወለደው ነፍስ አድን ድርጅት ሞረሽ ወገኔ የዐማራ ድርጅት፦ የአሥራት ዘር ፍሬ … [Read more...] about “ምጽአተ ዐማራ” አዲስ መጽሐፍ
ደንቁሩ በአዋጅ!
እግዚአብሔር ዓይንን ፈጠረና እዩበት አለ፤ እግዚአብሔር ጆሮን ፈጠረና ስሙበት አለ፤ እግዚአብሔር አእምሮን ፈጠረና አስቡበት አለ፤ እግዚአብሔር አንደበትን ፈጠረና ተናገሩበት አለ፤ ወያኔ አይሆንም አለ! በዓይንህ አትይ፤ በጆሮህ አትስማ፤ በአእምሮህ አታስብ፤ በአንደበትህ አትናገር፤ አበሻ ተዋረደ! ዓለም እየሰማ ድንቁርና ታወጀበት! ማን ያሸንፋል? እግዚአብሔር አለ፤ ወይስ ወያኔ አለ? (ምንጭ: Prof. Mesfin Wolde-Mariam Blog) … [Read more...] about ደንቁሩ በአዋጅ!
ላም እሳት ወለደች!
አጉል ዘመን ገጥሟት በረት ብትከሳ፤ ከብቶች በመዥገሮች አዩ ብዙ አበሳ፡፡ ጡቶቿን አቃጣይ የነበልባል ጥጃ ላም እሳት ወለደች፤ ብ’ተው በማይተዋ ዘልለው ባልጠገቡ ወይፈኖች ነደደች፡፡ የከበረው ባህል ባለጌ ረጋግጦት እንደጨው ቀለለ፤ ወፍ ዘራሾች ነግሠው ባጥለቀለቁት ደም ምድር ተበከለ፡፡ አዎ፣ ላም እሳት ወለደች! እንደዮዲት ጉዲት እቶኑ የሚፋጅ፤ ዕረፍት በማያ’ቅ ሠይፍ እንደነደርቡሾች እንደግራኝ አህመድ፤ ጭንቅላትን ገምሶ አንገትን ቆራርጦ ዜጎችን የሚያነድ፡፡ “አጥንትና ደሜ ይሄው የናንተው ነው፤ እኔ ከሌለሁኝ እናተም እንዲያው ነው፤ እርቧችሁ ጠግቤ፣ ብድንም ሞታችሁ፤ ማንም ስለሌለ ከኔ ‘ሚለያችሁ፤ እስከመጨረሻው አጅቡኝ ባካችሁ፡፡ ” እያለ እሳት ጥጃው ሕዝብን ይማጠናል፤ መስሎት የማናውቀው ቁርበት ዘርጉ ይላል፡፡ ክፋትና ተንኮል ተፈጥሮው የሆነ፤ ሕግና … [Read more...] about ላም እሳት ወለደች!
ለመለስ የተፃፈ ደብዳቤና የመለስ መልስ
ከፍቃዱ ጌታቸው ለመለስ እንደምን አለህ ጋሼ እንደምን ነህ መለስ ትመጣለህ ስንል ቀረህ ሳትመለስ እኛማ ይሔውልህ ባንተ ሌጋሲና ባንተ ትልቅ ራዕይ በየአደባባዩ እንላለን ዋይ ዋይ ዛሬም ጀነራልህ ተኩስ ነው ትዕዛዙ ወገን ያጋድማል የግፍ አፈሙዙ ለምንድን ነው ስንል ስምክን አስቀድመው ከክርስቶስ በላይ ምስልህን አትመው ቅዱስ መጽሐፍ ይመስል ባንተ ራዕይና በሌጋሲህ ምለው ቢረፈርፉንም አላለቅንምና ደብዳቤ ላክንልህ ከሞት የተረፍነው! ... የሆነስ ሆነና ግን አንተ ደህና ነህ እኛማ ይኸውልህ ደርሰህ ስትናፍቀን አይሞትም የምትል ሙዚቃ ሞዝቀን መቃብርህን ልንስም አበባ ልናኖር ሥላሴ ብንመጣ ፌደራል ያይሃል እስረኛ ይመስል ሾልከህ እንዳትወጣ መቼም ሥላሴ ውስጥ ባለስም ነውና የሚቀበርበት አንተን አየት አርገን ዞር ስንል … [Read more...] about ለመለስ የተፃፈ ደብዳቤና የመለስ መልስ
መሬቱ
ጥምል እየዞረ በሰማዩ ማገር በመሬቱ ዙሪያ ዕውነት የሚናገር ጠባሳው ያልጠፋ የታሪክ አሻራ መሬቱ መሰለኝ ጠላት የሚያፈራ። አገር በቀል ይሁን የሰው አገር ባዕዳ ዐይን እየማረከ የሚጋብዝ እንግዳ ከጥንት ጀምሮ እንደ እሚታወቀው ጠላት የሚያፈራ ለምለሙ መሬት ነው። ለምለሙ መሬት ነው ጦርነት አብቅሎ ቤት አልቦ ያስቀረኝ ከቀዬ አፈናቅሎ። ለም መሆኑ ቀዬ አፈረ - መሬቱ ጠላቶቸን ጋብዞ ዛሬም እንደ ጥንቱ ኮሪያው ይሁን ህንዱ ወይ የዐረቢያው ጉምቱ እንዲያፈናቅለኝ ገፍትሮ በሀብቱ ምክኒያት የሆነኝ ጫካውና ዱሩ ጠላቴ ተግሬ ነው መባቀያ አፈሩ። አያበቅሉ አብቅሎ አያፈሩ አፍርቶ የሚያፈናቅለኝ ተጎጆየ አውጥቶ ተግሬ ነው ጠላቴ ተቆምኩበት ምድር ለምለሙ መሬቴ ገዳይ በሰናድር። ማጣት ዕርዛቴን ሞቴን እንዲፈጥር ተፈጥሮው አድርጎት የቆምኩበት ምድር ለምላሜ ለብሶ ሜዳ … [Read more...] about መሬቱ
እናቶች፣ “ሶሻል ሚዲያ”ና ህወሃት/ኢህአዴግ
አዲስ አበባ የሰፈር ሴቶችን ሰብስበው መግለጫ ስለ social media አጠቃቀም ስጡ ተብለው የሰጡት መግለጫ እና ከመግለጫው በኋላ ለእናቶች የተደረገ ኢንተርቪው። ዜና FBC ፦ “መንግስት በሶሻል ሚዲያው ላይ ህዝብ የሚቀሰቅሱትን ጸረ-ሰላም ሃይሎች ከሚኖሩበት አገር ጋር በመመካከር ለህግ ማቅረብ አለበት!” ሲሉ ነዋሪነታቸው በቀበሌ 07 ልደታ ክከ የሆነ እናቶች ተናገሩ ... ↩ ከዜናው በኋላ የእናቶች ኢንተርቪው፦ ☞ የመጀመሪያዋ ተጠያቂ እናት (በግምት ከ 60 - 65 አመት እድሜ)፦ ጋዜጠኛ፦ እናት ለቃለ መጠይቅ ፈቃደኛ ስለሆኑ አመሰግናለሁ እናት፦ እኔም አመሰግናለሁ እልልልልል ... ጋዜጠኛ፦ ምነው እናት? እልልታው ምንድነው?? እናት፦ የገደሉት ለህግ ይቅረቡ አይደለም እንዴ ሲባል የነበረው??? ጋዜጠኛ (በድንጋጤ ክው ብሎ)፦ የለም የለም እናቴ ሶሻል ሚዲያ ነው … [Read more...] about እናቶች፣ “ሶሻል ሚዲያ”ና ህወሃት/ኢህአዴግ
ግፍና ጎርፍ
ሰሚ ካጡ የሶማሌ ተረቶች አንዱ እንዲህ ይላል፡፡ አንድ ሰው የጠፋች የአካባቢውን ግመል ፍለጋ ጫካ ይገባል፡፡ ከብዙ መከራ በኋላ ያቺን ግመል አግኝቶ ከተማ ገባና ግመሏን ለባለቤቱ ሳይመልስ ሐሳቡን ቀይሮ ራሱ ያልባትና ይጋልባት ጀመር፡፡ ግመሏን ከአውሬ ለማዳን ጫካ ገብቶ የነበረው ሰውዬ እርሱ ራሱ ግመሏን መውሰዱ ብዙዎችን አስገረማቸው፡፡ ትንሽ ቆየና ከዚያች ከአንዷ ግመል ወተት እያለበ በግመሏ ላይ ተቀምጦ እየዞረ ለአካባቢው ሰው ወተት መሸጥ ጀመረ፡፡ ነገር ግን የግመሏ ወተት በአንድ ጊዜ ሀብታም ሊያደርገው አልቻለምና ሌላ ነገር አሰበ፡፡ በወተቱ ውስጥ ውኃ እየጨመረ ቀላቅሎ መሸጥ፡፡ ‹‹ሰውም ምነው የሰውየው አመሉም ወተቱም ተቀየረሳ›› እያለ ዝም ብሎ ይገዛ ጀመር፡፡ (ይገዛ የሚለው ቃል ጠብቆ እንዳይነበብ አሳስባለሁ) ሰውዬውም በግመል ወተቱ ላይ ውኃን እያበዛው፤ የግመሉም ቁጥር … [Read more...] about ግፍና ጎርፍ
የፍቅር ብልሃቱ
ልዩነትን አድንቅ አንድነትን አድምቅ እንቆቅልሽ ፍታ ጥላቻ ይረታ ሁሉም ብሔረሰብ ነውና ቤተሰብ “እኔ ኢትዮጵያዊ ነኝ” ማለት ተውክ አማራ ምንም እንኳን በአገር መንፈስህ ቢኮራ “እኔ ኦሮሞ ነኝ” ማለት ተውክ ኦሮሞ ምንም እንኳን ጥሪህ ሁሎ ቢያድር ከርሞ “ኢትዮጵያዊ አማራ” ሆነህ ስትሄድ “ኢትዮጵያዊ ኦሮሞ” አገኘህ መንገድ የልብ ትርታ ሲወጣ ገሃድ ብለው ሲጠብቁ እሳትና ጭድ ፍቅር ጣልቃ ገብቶ አደረገ ጉድ የፍቅር ብልሃቱ ግርም ማሰኘቱ አንቺዬ ድንቅ አገር ኢትዮጵያ የሚሉሽ ትግሬና ሶማሌ ደቡብን የያዝሽ ጉራጌ ጋምቤላ አፋርን ያቀፍሽ ስንቱን ልጠራ ነው በዙ ልጆችሽ ነግሩ ሲጠራ እንዲሁም ሲጣራ እኩልነት ሰፍኖ ፍቅርም ልቆ ገኖ ኦሮሞ አማራ ማለቱ ይረሳና ኢትዮጵያዊ ነኝም ማለት ይቀርና ከአሁን ማንነትህ አድገህ … [Read more...] about የፍቅር ብልሃቱ
የእናት ለቅሶ
እናት በፍቅር፣ ጽንስ ይዛ፣ ዘጠኝ ወር አርግዛ፣ ራስዋን ምግብ አድርጋ፣ በማኅጸንዋ ሸሽጋ፣ ሽሉን ወደሰውነት አሳድጋ፣ የፈጣሪን ባሕርይ ተጋርታ፣ ሰው ሆና ሰው ፈጣሪ የሕይወት አለኝታ፣ በጻዕር አምጣ ወልዳ፣ አቅፋ በፍቅር አጥብታ፣ ተጨንቃ አሳድጋ፣ እንቅልፍ አጥታ፣ ሲስቅ ሲያስቃት፣ ሲያለቅስ ሲያስለቅሳት፣ ስትቆጣው እንዲያድግላት እንዲማርላት፣ ክቡር ሰው ሆኖ እንዲያኮራት፣ ያላትን ሁሉ ከፍላ መስዋእት፣ በጉጉት ስትጠብቅ -- ጨካኞች ሬሳውን ጣሉላት፡፡ ማኅጸንዋ ተኮማተረ፤ አንጀትዋ አረረ፤ አስፋልቱ ላይ የተንጣለለው ደም፣ ከልጅዋ አካል ጠብታም አልቀረም፤ ሙት አደረጋት በቁም፤ ከማኅጸንዋ እንደፈሰሰ ተሰማት፤ ተወልዶ ያደገ ልጅ አስወረዳት፤ በወጣት ልጅዋ የፈራረሰ አካል እስዋም ፈራረሰች ወየው ልጄ! ስትል፤ አካልዋ ተፍረከረከ፤ ጉልበትዋ … [Read more...] about የእናት ለቅሶ










