ለረጅም አመታተ የጣልኩትን ብዕር ድር ካደራበት ሰገባው እንድመዝ አስገደደኝ - በ ኢትዮ-ሚዲያ (Ethiomedia) እና በጎልጉል (Googlgule) ድህረ-ገፆች ላይ ከወራት በፊት በዶክተር ፍቃዱ በቀለ በተባሉ ግለሰብ በ"የተቆለፈበት ቁልፍ" መፅሐፉ ላይ የቀረበ አንድ ፅሑፍ። "ሃያሲው" በዘመናችን አቻ ያላገኙለት (ወደር የሌለው) መፅሐፉ መሆኑን ነው የገለፁልን። "...የስነ-ጽሁፍም ዋና ዓላማው በአንድ ህብረተሰብ ውስጥ ያሉትን አስቀያሚም ሆነ ቆንጆ ነገሮች ስዕላዊ በሆነ መልክ መግለጽ ሲችሉና አንባቢውን በልዩ ሃሳብ ውስጥ ተመስጦ እንዲዋኝ ማድረግ ሲችሉ ብቻ ነው።..." በማለት ካብራሩ በኃላ ከ`ዚህ አንፃር "የተቆለፈበት ቁልፍ" እንደተዋጣለት መሰክርነታችውን ይሰጣሉ። አንዲህ ሲሉ "....በታሪካችን ውስጥ በመጀመሪያ ጊዜ በልዩ አቀራረብ የተዘጋጀና የተጻፈ ትምህርታዊ መጽሀፍ ነው … [Read more...] about “የተቆለፈበት ቁልፍ” በቃላት ቁልፍ ተቆላልፏል!
Literature
ጽፈኪን
“እኩል ደራ ደራ ከነ‘ሜቴ ጋራ!”
ገጣሚና ደራሲ... ከግዑዙ መሬት፣ ከመንደሩ ይልቅ ከዘር ማንዘሩ፣ ሰብዓዊነትን ያልማል ብዕሩ “የሰው ልጅ ልብ...” ነው አገሩና ድንበሩ! ሰብዓዊነት ነው ክብሩ፤ ገጣሚ አገር የለውም፣ “ዩኒቨርሱ”ም አይበቃውም፤ ሰዋዊ ህመም ያመዋል፣ ፈውሱም ይፈውሰዋል፣ ገጣሚ ያ ይበቃዋል! ወርዶ ወርዶ “ቀየ መንደር ውስጥ አይወድቅም” አዎ! ገጣሚ፣ ደራሲ እንዲያውም አገር የለውም፣ የበዓሉ አገሩ ሰው ነው፣ “...ህንጻው ምን ቢረዝም፣ ምን ቢጸዳ ቤቱ፣ መንገዱ ቢሰፋ ቢንጣለል አስፋልቱ፣ ሰው ሰው ካልሸተተ ምንድነው ውበቱ፣ የኔ ውብ ከተማ የኔ ውብ አገር፣ የሰው ልጅ ልብ ነው የሌለው ድንበር...” (ኦሮማይ) ጸጋዬም ጊንጪ ኢምንት ቢሆንበት ጉደር፣ አምቦ፣ ቡራዩ ... ጠ’ቦበት፣ አዲሳ’ባ ኢትዮጵያም ብታንስበት፣ ብዕሩ ፈርዖኦንን ተመኘ፣ ነፈርቲቲ እና አፍሮዳይትን … [Read more...] about “እኩል ደራ ደራ ከነ‘ሜቴ ጋራ!”
የተካደ ትውልድ
የተካደ ትውልድ አይዞህ ባይ የሌለው ታዳጊ የሌለው ወይ ጠባቂ መላክ፤ ወይ አበጀ በለው ደርሶ ከቀንበሩ የማይገላግለው የተካደ ትውልድ፤ አብዝቶ የጾመ፤ ተግቶ የጸለየ ጥቂት መና ሳይሆን፤ ጥይት ሲዘንብ ያየ እድሜ ይፍታህ ተብሎ፤ የተወለደ’ለት አምባሩ ካቴና፤ ማተቡ ሠንሠለት፡፡ ምቾትን የማያውቅ፤ ረፍት የተቀማ አልጋው ያጋም እሾህ፤ ምኝታው የሣማ የተካደ ትውልድ፤ ሞቶ እንኳ ሬሳው፤ አይላላለት ቀንበር በዘብ እጅ ተገድሎ፤ በሹም የሚቀበር ከጡት አስጥል በላይ፤ ኑሮ የመረረው እንዳይሄድ፤ ጎዳናው፤ የተደናገረው ድል ያልሰመረለት ትግል ሳይቸግረው የተካደ ትውልድ በሥጋ በነፍሱ በቀልቡ በገላው ኧረ ምንድን ይሆን ፤ ምንድን ይሆን መላው? (በዕውቀቱ ሥዩም) … [Read more...] about የተካደ ትውልድ
“[ሰዎች] አለሙያቸው ሙያ እየጫንባቸው አበላሽተናቸዋል” ወለላዬ
ሰላም ጎልጉሎች . . . እንኳን ለገና በዓል በሰላም አደረሳችሁ። ከኢትዮጵያ ዛሬ ጋር በግጥሞቼ ሳቢያ ቃለ መጠይቅ አድርጌ ነበር። እናንተም ግጥሞቼን በተገቢው ሁኔታ ያስተናገዳችሁልኝ ስለሆነ እናንተም (ዘንድ) ቢታተም እወዳለሁ። በድጋሚ መልካም በዓል ይሁንላችሁ። ወለላዬ መዝጊያ ትሁንልኝ መቶ ራት ግጥሞችን - ተሸክሜ ይዤ፤ ረብዕ ረቡዕ ስጥል - አንድ አንዷን መዝዤ በዚች ባሁኗ ቀን - በጨበጥናት ሳምንት፤ ወሩን ስደምረው - ሆነኝ ሁለት ዓመት፡፡ ዳግም በአዲስ ዓመት - እስከምንገናኝ፤ የዘንድሮው መዝጊያ - ይቺ ትሁንልኝ፡፡ (ወለላዬ) ወለላዬ በየሳምንቱ ረቡዕ ረቡዕ በኢትዮጵያ ዛሬ ድረ ገጽ ላይ ለሁለት ዓመታት ያህል ሳያቋርጥ 104 ግጥሞች በመጻፍ አስነብቦናል። በነዚህ ግጥሞቹ እኛን ሆኖ ውስጣችን ገብቶ ያልተናገርነውን ተናግሮልናል። ታዝበን ያለፍነውን … [Read more...] about “[ሰዎች] አለሙያቸው ሙያ እየጫንባቸው አበላሽተናቸዋል” ወለላዬ
የዛ ሰውዬ ድምጽ . . .
ፊቱ አሸቦ መስሎ፣ እንደደነገጠ፣ ተጎልጉሎ ወጥቶ፣ ዓይኑ እንደፈጠጠ፣ ባንኮኒው ጋ ሄዶ፣ ቢራውን ጨበጠ። የሆነውን እንጃ! ሁኔታው ያስፈራል፣ እንባው በጉንጩ ላይ፣ አቋርጦ ይፈሳል አልቅሶ ሲበቃው፣ ውጪ እየሰለለ፤ ያየውን በውስጡ፣ እያሰላሰለ፣ ገድለው ሲጥሏቸው፣ በዓይኖቼ አየሁ አለ። ወደ ተናጋሪው፣ አፍጠን እያየን፤ እንደልማዳችን፣ ዝም ተባባልን። ሰውዬው ቀጠለ፣ ገድለው ሲጥሏቸው፣ በዓይኖቼ አየሁ አለ! ዘለው ያልጠገቡ፣ እህል የተራቡ፣ አገር የተቀሙ፣ ፍትሕ የተጠሙ፣ አንድ ፍሬ ናቸው! ገና እንዳገኟቸው፣ ከበው ይዘዋቸው፣ መሣሪያ አስጠግተው፣ ወደ ግንባራቸው፣ ጭንቅላታቸውን ... ፈረካከሷቸው። እያለ ሲናገር፣ ሰውዬው ሲቆጣ፣ ሲያለቅስ ሲያማርር፣ እኔም ልክ እንደሱው፣ በዓይኖቹ ገብቼ፣ አንገቴን አቅፌ፣ በሁለት እጆቼ፣ ጉልበቴ እየራደ፣ ነፍሴ … [Read more...] about የዛ ሰውዬ ድምጽ . . .
ለጀግናው አትሌት ስንብት!
. . . በዚያ ቀውጢ ጊዜ - በዚያ ቀውጢ ዘመን፣ ከአገር በራቀበት - የደስታ ሰመመን፤ ያገር ፍቅር ስሜት - መገለጫ ፈርጦች፣ ብቸኛው አማራጭ - የደስታችን ምንጮች፣ ነበሩን! ነበሩ! “አረንጓዴ ጎርፎች”. . .፤ እንዲህ እንደዛሬው - ሳይዘምን ዘመኑ፣ ያለም መገናኛ - ሳይራቀቅ ኪኑ፣ ዩ ቲዩብ፣ ኢንተርኔት፣ ስማርት ፎን..ሳይኖር፣ ዜና መቀበያው - ራድዮናችን ነበር፤ “. . . ክቡራትና ክቡራን ውድ አድማጮቻችን..”፣ የኦሎምፒክ ውጤት፣ ልክ እንደደረሰን፣ እናስደምጣለን...”፤ በለሆሳስ ሙዚቃ መሳሪያ ቅንብር መሻገሪያ ዜማ፣ ከተራራ ጫፍ ላይ፣ ወይ ከሰማየ-ሰማያት ከሩቅ እሚሰማ፣ “የኛ ነው ድሉ-ድሉ፣ የኛ ነው ድሉ-ድሉ፣ በርቱና ታገሉ..”፤ አገር ትንፋሽ አጥሮት - ጸጥ-ረጭ ብሎ፣ ዐይኖቹን ጎልጉሎ - ራድዮን ላይ … [Read more...] about ለጀግናው አትሌት ስንብት!
የግርማ ይፍራሸዋ ፒያኖ ኮንሰርት በዋሺንግተን ዲሲ
ከ25 ዓመታት በላይ የፒያኖ ድርሰቶችን በመጻፍና በመጫወት የአገራችንን ስም በማስጠራት የቆየው ኢትዮጵያዊው ዜማ ደራሲ እና ፒያኒስት ግርማ ይፍራሸዋ በአሁኑ ቅዳሜ November 26 ምሽት ከ6:30 ጀምሮ በዋሺንግተን ዲሲ እና በአካባቢዋ ለሚገኙት አድናቂዎቹ ግሩም የሆነ የፒያኖ ሙዚቃ ትርኢት Washington Ethical Society አዳራሽ ለማቅረብ ተዘጋጅቷል። ግርማ የሙዚቃ ትምህርቱን የጀመረው በልጅነቱ ክራር በመጫወት ነበር። በመቀጠልም በያሬድ ሙዚቃ ት/ቤት (1975-1978 ዓ.ም)፣ Sofia State Conservatory of Music (1978-1986 ዓ.ም)፣London Royal Academy of Music (1989 ዓ.ም)፣ እናLeipzig Hochschule für Music und Theater (1991 ዓ.ም) ክላሲካል ሙዚቃን በመማር የድርሰትና የትርኢት ችሎታውን ለማዳበር … [Read more...] about የግርማ ይፍራሸዋ ፒያኖ ኮንሰርት በዋሺንግተን ዲሲ
ያለም ገዥ
ኮሳሳ አገዝፎ፣ ግዙፍ አኮስሶ የሾመውን ሽሮ፣ያሻውን አንግሶ በለወጠው አዲስ ክስተተ ሁኔታ ሀዘንና ደስታ፤ ደስታና ሀዘንን አቀያይሮ ቦታ በራሱ ህግጋት ዘመኑን ዳኝቶ ጊዜ ነው የሚኖር ዓለማችን ገዝቶ። ጥቅምት 2009 አብርሃም በየነ … [Read more...] about ያለም ገዥ
ይረገም!!
በክፉ ያነሳ ወርቃማውን ስምሽን፣ በሃሜት ያጎደፈ ፀዐዳ ክብርሽን፣ በክፋት ፈረሱ ወዳንቺ የጋለበ፣ በእሾኸም ምላሱ ሊወጋሽ ያሰበ፤ ሰላምሽን የነሳ፣ ባንቺ ላይ ሊሳለቅ፣ ሊቀልድ የቃጣ መልካም ህይወት ትክዳው! ነፍሱ ሰላም ትጣ!! ብርሃንሽን ሊያጠፋ ውበትሽን ሊያከስም፣ መዐዛሽን ሊበክል ህይወትሽን ሊያጨልም፣ በክፋት ያቀደ በሻገተ ህሊናው፣ ብርሃኑ ይደፈን ! ጨለማ ይውረሰው! ስትለመልሚ ስትፈኪ አይቶ፣ በአርኪ ፈገግታሽ በቅናት ተውጦ፣ የቆሸሸ እጁን ባንቺ የዘረጋ፣ ሽባ ይሁን ይስለል! አንደበቱ ይዘጋ! የዘመናት ስምሽን ዝናሽን ሊያጎድፍ፣ ከባዕድ አብሮ ወዲያ ሲያነፈንፍ፣ ህይወቱን በሙሉ ሳይሰራ ቁም-ነገር፣ ገብቶ ሲሽሎኮሎክ ከጢሻ ከቆንጥር...፤ ሊነክስ ያደባ የጠባውን ጡትሽን፣ ሊያጠፋ የቃጣ ሃቀኛውን ልጅሽን፣ የታሪክ መጠሪያ ቅርሳ-ቅርስ … [Read more...] about ይረገም!!
“ትራምፕ – ቢመረጥስ?! …”
… በበረዶ፣ በዝናም፣ በሐሩር፣ በቁሩ . . . መፈክር አንግበን፣ ላንቃችን እስኪታይ - አምባገነኖችን በጩኸት አውግዘን፣ የድምጽ-አልባውን ሕዝብ - የጭቆና ብሶት፣ ላለም ስናሰማ - ለሩብ ምዕተ-ዓመት፤ ጆሮ ዳባ ብለው - የተሳለቁብን፣ ከጨቋኝ ወግነው፣ በዶላር አፋፍተው… ነጻነታችንን በጅ-አዙር ያስቀሙን. . .፤ ቦ! ጊዜ ለኩሉ!... የተፈጥሮ አዙሪት-ህግ - የወር-ተራው እዚያም ደርሶ፣ በታላቋ አሜሪካ - “አምባገነን” ትራምፕ ነግሶ፣ ‘የባቢሎን ግምቡን‘ አጥሮ . . . ነጻነትን ፊጥኝ አስሮ፣ ህገ-መንግስት ተሰውቶ. . . ፍርድ ቤቱም ለርሱ አድልቶ...፣ የአሜሪካ ሃምሳ ስቴቶች - ሰላማዊ ሰልፍ ወጥተው፣ በመፈክር ተጥለቅልቀው - በራብ-አድማ ጠቁረው ከስተው፤ በላያችን የወረደ ፣ መብረቅ... ዝናም ወርዶባቸው፣ የነጻነት ረሃብ፣ ጥሙ - ዘልቆ ገብቶ … [Read more...] about “ትራምፕ – ቢመረጥስ?! …”




![“[ሰዎች] አለሙያቸው ሙያ እየጫንባቸው አበላሽተናቸዋል” ወለላዬ](https://www.goolgule.com/wp-content/uploads/2017/01/fake-mask-300x225.jpg)





