• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የተካደ ትውልድ

January 23, 2017 08:13 am by Editor 2 Comments

የተካደ ትውልድ
አይዞህ ባይ የሌለው
ታዳጊ የሌለው
ወይ ጠባቂ መላክ፤ ወይ አበጀ በለው
ደርሶ ከቀንበሩ የማይገላግለው

የተካደ ትውልድ፤
አብዝቶ የጾመ፤ ተግቶ የጸለየ
ጥቂት  መና ሳይሆን፤ ጥይት ሲዘንብ ያየ
እድሜ ይፍታህ ተብሎ፤ የተወለደ’ለት
አምባሩ ካቴና፤ ማተቡ ሠንሠለት፡፡
ምቾትን የማያውቅ፤ ረፍት የተቀማ
አልጋው ያጋም እሾህ፤ ምኝታው የሣማ

የተካደ ትውልድ፤

ሞቶ እንኳ ሬሳው፤ አይላላለት ቀንበር
በዘብ  እጅ ተገድሎ፤ በሹም የሚቀበር
ከጡት አስጥል በላይ፤ ኑሮ የመረረው
እንዳይሄድ፤  ጎዳናው፤ የተደናገረው
ድል ያልሰመረለት ትግል ሳይቸግረው

የተካደ ትውልድ
በሥጋ በነፍሱ
በቀልቡ በገላው
ኧረ ምንድን  ይሆን ፤ ምንድን ይሆን መላው?

(በዕውቀቱ ሥዩም)

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Literature Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Comments

  1. Ezira says

    January 24, 2017 04:37 pm at 4:37 pm

    በእዉቀቱ ሥዩም እጥር ምጥን ያለችውን የግጥም ስንኝህን አነበብኳት። የግጥምህ የመጨረሻ መደምደሚያ በጥያቄ የተቋጨ መሆኑን ሳይ ለጥያቄህ መልስ ይሆን ዘንድ ይሄንን ለመፃፍ ወደድኩ።

    መላው እንደ አያያዙና እንደ አመጣጡ ቆርጦ መታገል ብቻ ነው። የነጻነት ዋጋ ውድ ነው ። በ ዉድ ዋጋ የሚገኝ ነገር ደግሞ ዉድ ህይወትን ሁሉ ይጠይቃል። ዓለማችንን ከጥፋት ማዕበል ተመልሳ እንደትቆም ያደረገው ልዩ ተምሳሌችን ኢየሱስ ክርስቶስ ውድ ህይወቱን ከፍሏል። ኢየሱስ ክርስቶስ ለስው ልጆች መዳን ሲል ዉድ ህይወቱን ሁሉ ከፍሎልናል ብለው የሚያምኑና የሚከተሉት ምዕመናን ዛሬ በዓለማችን ላይ ብዙሃን እና ለቁጥር የሚያታክቱ ናቸው። የስው ልጅም እንዳለከው በተፈጥሮው ሰው በመሆኑ ብቻ ሊያገኘው የሚገባውን መብቱን የተነጠቀ ሲመስለውና መነጠቁን ካወቀ ለነጻነቱ ሲል “በሥጋ በነፍሱ በቀልቡ በገላው” መስዋትንነትን ክፍሎ የነፃነቱ የመብቱ ባለቤት መሆኑ አይቀሬ ነው። ይሄንን አይቀሬነት እስኪያረጋግጥና የነፃነቱ ባለቤት እስኪሆን ድረስ እያንዳንዱ ትዉልድ (በየትዉልድ ዘመኑ) ከፊቱ የሚጋረጥበትን ወይም የሚያደናቅፈዉን እንቅፋት ታግሎ ማሸነፍ ተፍጥሯዊ ግዴታው ነው። በመሆኑም በተፈጥሮ ህግ እንደሚናጋ ስለምናውቅ ነው ጨለማን የማንፈራው ለማለት ነው። በእዉቀቱ ሥዩም ጠፈተህ፤ ጠፍተህ ከረመህ አሁን በዚች እጥር ምጥን ባለች ግጥምህ ብቅ ስላልክ ዴግሞ እንኳን ደህና መጣህ ለማለትም ጭምር ነው።

    Reply
  2. አትንኩት መላኩ says

    January 27, 2017 04:10 pm at 4:10 pm

    እውንትህን እግዚአብሔር። ይስ

    ጥህ እንዴት ትርድህው ባክህ

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የአየለ ጫሚሶ ቅንጅት ፈረሰ January 18, 2021 02:31 pm
  • ህወሓት ተሠረዘ!!! January 18, 2021 01:32 pm
  • ዓሲምባ፣ ሣልሳዊ ወያኔና ባይቶና ከመፍረሳቸው በፊት ማብራሪያ እንዲሰጡ ተነገራቸው January 18, 2021 01:00 pm
  • ቤተሰቦች አስከሬን መውሰድ እንደሚችሉ ተነገረ January 14, 2021 06:48 pm
  • ስብሃት፤ “ከሞትን ቆይተናል፤ … አሁን የቀብር ሥነ-ስርዓታችን” እየተፈጸመ ነው January 14, 2021 01:37 pm
  • “ተመልሰን እንነሳለን” ያሉት ህወሓቶች ተመልሰው ወደማይነሱበት ተሸኙ January 13, 2021 01:12 pm
  • አፋር ነፃ አውጪ (ኡጉጉሙን) ለመጠቀም የታቀደው የህወሃት ሤራ ከሽፏል January 13, 2021 01:10 pm
  • ህወሃትን ወደ ጅቡቲ ለማሻገር ሲሰሩ የነበሩ የአፋር ታጣቂዎች በሰላም ወደ ክልሉ ገቡ January 13, 2021 06:47 am
  • በታህሳስ ወር ብቻ ከ344 ሚሊየን ብር በላይ የኮንትሮባንድ ዕቃ ተያዘ January 13, 2021 06:10 am
  • የብልፅግና ፓርቲ ቀጣይ ፈተና ምን ሊሆን ይችላል? January 13, 2021 04:10 am
  • ለትምህርት እንዲሆነን January 11, 2021 01:20 pm
  • “ከተቀበሩበት የጃርት ጉድጓድ ነው ያወጣናቸው” መቶ አለቃ ስዩም ቱርቦ January 11, 2021 12:11 pm
  • የተደመሰሱና በቁጥጥር ሥር የዋሉ የወንበዴው አባላት ይፋ ሆነ January 7, 2021 01:16 pm
  • ዐቢይና መኮንኖቹ በመቀሌ፤ “ድሉ የመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ነው” December 13, 2020 02:36 pm
  • ወንበዴው ህወሓት ከ1.4 ትሪሊዮን ብር በላይ ዘርፎ በውጭ አገራት ባንኮች አስቀምጧል December 8, 2020 01:05 am
  • ማይካድራ – የትህነግ የዘር ማጥፋት ጥግ ቋሚ ምስክር December 8, 2020 12:57 am
  • የወልቃይት ጠገዴ እናቶች ሰቆቃ ሲታወስ December 8, 2020 12:50 am
  • የደብረጽዮን ዋሻ December 7, 2020 11:30 pm
  • ባለ ከዘራው ኮሎኔል December 7, 2020 05:15 pm
  • ሰላማዊ ሕይወት በማይጨው December 7, 2020 04:12 pm
  • ተጠርጣሪ የፌዴራልና የአዲስ አበባ ፖሊሶች የመያዣ ትዕዛዝ ወጣባቸው December 7, 2020 11:46 am
  • ከ3 ሺህ በላይ ተተኳሽ ጥይቶች በወልዲያ ጉምሩክ ሊያሳልፉ የሞከሩ 4 ግለሰቦች ተያዙ! December 7, 2020 11:18 am
  • ወንበዴዎቹ ይጠቀሙባቸው የነበሩ ተሽከርካሪዎችና የግል ሰነዶቻቸው ተያዙ December 7, 2020 10:50 am
  • ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ በሶማሌ ክልል ተመሠረተ December 7, 2020 10:31 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2021 · Goolgule