• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የተካደ ትውልድ

January 23, 2017 08:13 am by Editor 2 Comments

የተካደ ትውልድ
አይዞህ ባይ የሌለው
ታዳጊ የሌለው
ወይ ጠባቂ መላክ፤ ወይ አበጀ በለው
ደርሶ ከቀንበሩ የማይገላግለው

የተካደ ትውልድ፤
አብዝቶ የጾመ፤ ተግቶ የጸለየ
ጥቂት  መና ሳይሆን፤ ጥይት ሲዘንብ ያየ
እድሜ ይፍታህ ተብሎ፤ የተወለደ’ለት
አምባሩ ካቴና፤ ማተቡ ሠንሠለት፡፡
ምቾትን የማያውቅ፤ ረፍት የተቀማ
አልጋው ያጋም እሾህ፤ ምኝታው የሣማ

የተካደ ትውልድ፤

ሞቶ እንኳ ሬሳው፤ አይላላለት ቀንበር
በዘብ  እጅ ተገድሎ፤ በሹም የሚቀበር
ከጡት አስጥል በላይ፤ ኑሮ የመረረው
እንዳይሄድ፤  ጎዳናው፤ የተደናገረው
ድል ያልሰመረለት ትግል ሳይቸግረው

የተካደ ትውልድ
በሥጋ በነፍሱ
በቀልቡ በገላው
ኧረ ምንድን  ይሆን ፤ ምንድን ይሆን መላው?

(በዕውቀቱ ሥዩም)

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Literature Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Comments

  1. Ezira says

    January 24, 2017 04:37 pm at 4:37 pm

    በእዉቀቱ ሥዩም እጥር ምጥን ያለችውን የግጥም ስንኝህን አነበብኳት። የግጥምህ የመጨረሻ መደምደሚያ በጥያቄ የተቋጨ መሆኑን ሳይ ለጥያቄህ መልስ ይሆን ዘንድ ይሄንን ለመፃፍ ወደድኩ።

    መላው እንደ አያያዙና እንደ አመጣጡ ቆርጦ መታገል ብቻ ነው። የነጻነት ዋጋ ውድ ነው ። በ ዉድ ዋጋ የሚገኝ ነገር ደግሞ ዉድ ህይወትን ሁሉ ይጠይቃል። ዓለማችንን ከጥፋት ማዕበል ተመልሳ እንደትቆም ያደረገው ልዩ ተምሳሌችን ኢየሱስ ክርስቶስ ውድ ህይወቱን ከፍሏል። ኢየሱስ ክርስቶስ ለስው ልጆች መዳን ሲል ዉድ ህይወቱን ሁሉ ከፍሎልናል ብለው የሚያምኑና የሚከተሉት ምዕመናን ዛሬ በዓለማችን ላይ ብዙሃን እና ለቁጥር የሚያታክቱ ናቸው። የስው ልጅም እንዳለከው በተፈጥሮው ሰው በመሆኑ ብቻ ሊያገኘው የሚገባውን መብቱን የተነጠቀ ሲመስለውና መነጠቁን ካወቀ ለነጻነቱ ሲል “በሥጋ በነፍሱ በቀልቡ በገላው” መስዋትንነትን ክፍሎ የነፃነቱ የመብቱ ባለቤት መሆኑ አይቀሬ ነው። ይሄንን አይቀሬነት እስኪያረጋግጥና የነፃነቱ ባለቤት እስኪሆን ድረስ እያንዳንዱ ትዉልድ (በየትዉልድ ዘመኑ) ከፊቱ የሚጋረጥበትን ወይም የሚያደናቅፈዉን እንቅፋት ታግሎ ማሸነፍ ተፍጥሯዊ ግዴታው ነው። በመሆኑም በተፈጥሮ ህግ እንደሚናጋ ስለምናውቅ ነው ጨለማን የማንፈራው ለማለት ነው። በእዉቀቱ ሥዩም ጠፈተህ፤ ጠፍተህ ከረመህ አሁን በዚች እጥር ምጥን ባለች ግጥምህ ብቅ ስላልክ ዴግሞ እንኳን ደህና መጣህ ለማለትም ጭምር ነው።

    Reply
  2. አትንኩት መላኩ says

    January 27, 2017 04:10 pm at 4:10 pm

    እውንትህን እግዚአብሔር። ይስ

    ጥህ እንዴት ትርድህው ባክህ

    Reply

Leave a Reply to አትንኩት መላኩ Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ባልደራስ የአገርን ደኅንነት አደጋ ላይ በመጣል ሊጠየቅ ይገባዋል ተባለ July 1, 2022 09:23 am
  • “ሚካኤል ችግኝ ነው። … ችግኝ ይተክላል” ቴዲ አፍሮ June 29, 2022 03:30 am
  • “የእኔን ልጆችና የልጅ ልጆች (22ቱንም) የቀበርኩት እኔ ነኝ” አቶ መሀመድ የሱፍ ከምዕራብ ወለጋ June 28, 2022 01:07 pm
  • የገዳ ሥርዓት እና የኦሮሞ ገዢ መደብ June 20, 2022 11:34 pm
  • “የወልቃይትን ጉዳይ ለድርድር የማናቀርበው ቀይ መስመራችን ነው” ርዕሰ መስተዳድር ይልቃል June 12, 2022 07:09 pm
  • የሰሜን ምዕራብ ዕዝና የአማራ ልዩ ኃይል ተከዜ ክፍለ ጦር ዕውቅናና ሽልማት ተሰጣቸው June 12, 2022 06:21 pm
  • ሀገር በቀል ባህላዊ የግጭት አፈታቶችን በተገቢው በመጠቀም ዘላቂ እርቅና ሰላምን ማምጣት ይቻላል June 12, 2022 05:40 pm
  • የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን በገረጂና በቀበና ያስገነባቸውን የመኖሪያ አፓርትመንቶች አስመረቀ June 12, 2022 05:35 pm
  • በኦነግ ሸኔ ፈርሶ የነበረውና ወታደራዊ ጠቀሜታ ያለው ድልድይ ተጠግኖ አገልግሎት መስጠት ጀመረ June 10, 2022 09:13 am
  • ጃዋር በዳውድ ኢብሣ ቀይ መስመር ተሰመረለት June 8, 2022 12:59 pm
  • ወልቃይት: ቢመረንም ለመዋጥና ራሳችንን ለመመልከት እንሞክር June 8, 2022 11:53 am
  • እብድ ይሻለዋል እንጂ አይድንም፤ ሐጂ ጃዋር አሁን ለምን ብቅ አለ? June 8, 2022 05:59 am
  • ሕዝብ ድምፅ የነፈጋቸው “ፓርቲዎች” የሽግግር መንግሥት ይቋቋም አሉ June 7, 2022 01:11 am
  • “አድጌ እንደናንተ መሆን እፈልጋለሁ” June 5, 2022 06:58 pm
  • በሳምንት ለ100 ያህል ሕሙማን አገልግሎት የሚሰጥ የኩላሊት ዕጥበት ማዕከል ሥራ ጀመረ May 30, 2022 02:20 am
  • የጥቁር አንበሳ ዕጩ መኮንኖች (ካዴቶች) ተመረቁ May 29, 2022 04:01 pm
  • “ኢትዮጵያን መንካት አይቻልም!!” በሚል ቁጭት ነው እየሠራን ያለነው May 29, 2022 01:04 pm
  • “ከሞፈርና ቀንበር ወደ ትራክተር” በሚል መርህ ለአማራ ገበሬዎች የግብርና ሜካናይዜሽን ተሰጠ May 29, 2022 02:02 am
  • ኢትዮ 360 “የወያኔ፣ የጁንታ ሚዲያ ነው” – ባለከዘራው ጄኔራል May 27, 2022 02:51 am
  • “እኛ የምናውቀው ነገር የለም፤ የሚያጣሉን ፖለቲከኞች ናቸው” የአማራ ወዳጃቸውን አደራ ቤት የመለሱ የቅማንት ተወላጅ May 27, 2022 01:40 am
  • ትግራይን አገር እናደርጋለን፤ “በውይይት እና በጦርነት” ሁሉንም ጉዳይ እንቋጫለን – የወንበዴው መሪ ደብረጽዮን May 26, 2022 09:18 am
  • “ሁለቱ የምዕራብ ዕዝ ተዋጊ ዶክተሮች” May 26, 2022 08:19 am
  • ወደ ትህነግ ሊተላለፍ የነበረ አምስት ሚሊዮን ብር ከ20 ተጠርጣሪዎች ጋር ተያዘ May 25, 2022 01:57 am
  • የጦርነቱ ስትራቴጂያዊ እውነታዎች May 19, 2022 09:37 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2022 · Goolgule