• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የዛ ሰውዬ ድምጽ . . .

January 8, 2017 02:13 am by Editor Leave a Comment

ፊቱ አሸቦ መስሎ፣ እንደደነገጠ፣
ተጎልጉሎ ወጥቶ፣ ዓይኑ እንደፈጠጠ፣
ባንኮኒው ጋ ሄዶ፣ ቢራውን ጨበጠ።
የሆነውን እንጃ! ሁኔታው ያስፈራል፣
እንባው በጉንጩ ላይ፣ አቋርጦ ይፈሳል
አልቅሶ ሲበቃው፣ ውጪ እየሰለለ፤
ያየውን በውስጡ፣ እያሰላሰለ፣
ገድለው ሲጥሏቸው፣ በዓይኖቼ አየሁ አለ።

ወደ ተናጋሪው፣ አፍጠን እያየን፤
እንደልማዳችን፣ ዝም ተባባልን።
ሰውዬው ቀጠለ፣
ገድለው ሲጥሏቸው፣ በዓይኖቼ አየሁ አለ!
ዘለው ያልጠገቡ፣
እህል የተራቡ፣
አገር የተቀሙ፣
ፍትሕ የተጠሙ፣
አንድ ፍሬ ናቸው!
ገና እንዳገኟቸው፣
ከበው ይዘዋቸው፣
መሣሪያ አስጠግተው፣ ወደ ግንባራቸው፣
ጭንቅላታቸውን … ፈረካከሷቸው።

እያለ ሲናገር፣
ሰውዬው ሲቆጣ፣ ሲያለቅስ ሲያማርር፣
እኔም ልክ እንደሱው፣ በዓይኖቹ ገብቼ፣
አንገቴን አቅፌ፣ በሁለት እጆቼ፣
ጉልበቴ እየራደ፣ ነፍሴ እየበነነች፣
አውጣኝ! ከዚህ ቦታ፣ አድነኝ እያለች፣
ስትለማመጠኝ!
የደም ፍንጣቂ፣ አካሌን ሲያለብሰኝ
እሱ ቦታ ቆሜ፣ እሱን ሆኜ አየሁኝ።

ሰውዬው ቀጠለ፣
ቴሌቭዥን አይቶ፣ እኚህ ናቸው አለ።
ቢራውን ጨለጠ፣
ዓይኑን አፈጠጠ፣
ውሸታሞች ናቸው! ሽብርተኛ አይደሉም፣
ጨርሶ! በጃቸው፣ መሣሪያም አልያዙም፣
አይቻለሁ በዓይኔ፣ ነጻ ልጆች ናቸው፣
ምንም ሳያጠፉ፣ ነው የገደሏቸው!
ኡ! ኡ! አለ ሰውዬው፣ እንደሰማ መርዶ፣
በዜናው እወጃ፣ ክፉኛ ተናዶ
ነገሩ እየቆጨኝ፣ እያንገበገበኝ፣
ጀብረር እንዲያደርገኝ፣
ፍራት እንዲርቀኝ፣
አልኮሌን ደገምኩኝ።

ሰውዬው ተናግሮ አልወጣልህ ቢለው፣
ኡ! ኡ! ብሎ ጮኾ፣ ማልቀስም አማረው!
እሪ! አለ ሰውዬው፣ ንዴቱ ጨመረ፣
ጩኸቱን ለቀቀው፣ ቤቱ ተሸበረ።
ተንጋግቶ ደረሰ፣ ፌደራልም መጣ፣
ይጎትቱት ጀመር፣ እውጪ እንዲወጣ፣
ይሄኔ ተነሳሁ፣ አትነኩትም! አልኩኝ፣
ሰውዬውን ላስጥል፣ ከመሃል ገባሁኝ።
ምን አ’ረገ! አልኳቸው፣
ጥፋቱን ንገሩኝ? ብዬ ጠየኳቸው!
ሽብርተኛ ሲሞት፣ ተንሰቅስቆ አልቅሷል፣
ሕዝብ መሃል ሆኖ፣ ሰላም አደፍርሷል፣
ብለው ሲናገሩ፣ እንደ እብድ አ’ረገኝ፣
ጭራሽ አትወስዱትም! አትነኩትም አልኩኝ።
ያለው ሁሉ እንደኔ፣ በአንድ ላይ አደመ፣
መሃላቸው ገብቶ፣ አሰፍስፎ ቆመ።
ከዛ ቤቱ ሁሉ፣ መተረማመሱ፣
ትንሽ ትዝ ይለኛል፣ ጥይት መተኮሱ
ካለሁበት ቦታ፣ ለሊት ብንን ስል፣
ማንም በሌለበት፣ በጨለማ ክፍል፣
ዘለው ያልጠገቡ፣
እህል የተራቡ፣
አገር የተቀሙ፣
ፍትሕ የተጠሙ፣
አንድ ፍሬ ናቸው!
ገና እንዳገኟቸው፣
ከበው ይዘዋቸው፣
ጭንቅላታቸውን … ፈረካከሷቸው።
እያለ ይጮሃል፣
የዛ ሰውዬ ድምጽ፣ አሁንም ይስማል።

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Literature Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • “የገቡበት ገብተን አንድ ሰው አናስቀርም – በተለይ አመራሩን” ጄኔራል ብርሃኑ ጁላ February 15, 2021 11:46 pm
  • የትግራይ ገበሬና የከተማ ነዋሪ በሠራዊታችን ላይ አንድ ጥይት አልተኮሰም – ሪር አድሚራል ክንዱ February 4, 2021 01:51 pm
  • ኢንተርፖል፤ የህወሃት ሳምሪዎች የማይካድራ ጭፍጭፋ ከቦኮሃራም የከፋ ነው February 4, 2021 11:10 am
  • ጄኔራሎች “ተገድለዋል” በሚል የሀሰት መረጃ ሲያሰራጭ የነበረው ግለሰብ በቁጥጥር ስር ዋለ February 4, 2021 08:48 am
  • በትግራይ ክልል በሴቶች ላይ ተፈጸመ የተባለውን ጥቃት የሚያጣራ ግብረ ኃይል መቀሌ ገባ February 3, 2021 12:06 pm
  • ፓርቲዎች የምርጫ መወዳደሪያ ምልክቶቻቸውን ወሰዱ February 3, 2021 10:29 am
  • በአዲስ አበባ የተወረረው መሬት፣ ባለቤት አልባ ቤቶችና ሕንጻዎች ይፋ ሆኑ January 26, 2021 11:16 am
  • የብሔራዊ መረጃና ደህንነት አክቲቪስቶችን በሕግ ተጠያቂ አደርጋለሁ አለ January 26, 2021 10:32 am
  • የሰባት ቤት አገው የፈረሰኞች ማኅበር 81ኛ የምስረታ በዓል January 26, 2021 07:17 am
  • በጋምቤላ ህወሃትንና ኦነግ ሸኔን ትረዳላችሁ ተብለው የታሰሩ እንዲፈቱ ተጠየቀ January 25, 2021 03:07 pm
  • “…ሰብዓዊ እርዳታ እየቀረበ አይደለም የሚሉ አካላት የፖለቲካ ትርፍ ለማግኘት ነው” – ዶ/ር ሙሉ ነጋ January 25, 2021 01:02 pm
  • የሶማሌና ኦሮሚያ መሥተዳድሮች ወሰንን በተመለከተ የሰላምና የጋራ ልማት ስምምነት አደረጉ January 25, 2021 12:50 pm
  • 125ተኛውን የአድዋ ድል በዓል በድምቀት ሊከበር ነው January 25, 2021 09:34 am
  • በመቀሌ ከ350 ሚሊዮን ብር በላይ የህክምና ግብዓቶች ክምችት መኖሩ ታወቀ January 25, 2021 02:47 am
  • ዊንጉ አፍሪካ (wingu.africa) በዓይነቱ የመጀመሪያ የሆነ የመረጃ ማዕከል ሊገነባ ነው January 24, 2021 01:23 pm
  • ኢትዮጵያ ድሮኖችን ማምረት ልትጀምር ነው January 24, 2021 02:40 am
  • የአየለ ጫሚሶ ቅንጅት ፈረሰ January 18, 2021 02:31 pm
  • ህወሓት ተሠረዘ!!! January 18, 2021 01:32 pm
  • ዓሲምባ፣ ሣልሳዊ ወያኔና ባይቶና ከመፍረሳቸው በፊት ማብራሪያ እንዲሰጡ ተነገራቸው January 18, 2021 01:00 pm
  • ቤተሰቦች አስከሬን መውሰድ እንደሚችሉ ተነገረ January 14, 2021 06:48 pm
  • ስብሃት፤ “ከሞትን ቆይተናል፤ … አሁን የቀብር ሥነ-ስርዓታችን” እየተፈጸመ ነው January 14, 2021 01:37 pm
  • “ተመልሰን እንነሳለን” ያሉት ህወሓቶች ተመልሰው ወደማይነሱበት ተሸኙ January 13, 2021 01:12 pm
  • አፋር ነፃ አውጪ (ኡጉጉሙን) ለመጠቀም የታቀደው የህወሃት ሤራ ከሽፏል January 13, 2021 01:10 pm
  • ህወሃትን ወደ ጅቡቲ ለማሻገር ሲሰሩ የነበሩ የአፋር ታጣቂዎች በሰላም ወደ ክልሉ ገቡ January 13, 2021 06:47 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2021 · Goolgule