• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የዛ ሰውዬ ድምጽ . . .

January 8, 2017 02:13 am by Editor Leave a Comment

ፊቱ አሸቦ መስሎ፣ እንደደነገጠ፣
ተጎልጉሎ ወጥቶ፣ ዓይኑ እንደፈጠጠ፣
ባንኮኒው ጋ ሄዶ፣ ቢራውን ጨበጠ።
የሆነውን እንጃ! ሁኔታው ያስፈራል፣
እንባው በጉንጩ ላይ፣ አቋርጦ ይፈሳል
አልቅሶ ሲበቃው፣ ውጪ እየሰለለ፤
ያየውን በውስጡ፣ እያሰላሰለ፣
ገድለው ሲጥሏቸው፣ በዓይኖቼ አየሁ አለ።

ወደ ተናጋሪው፣ አፍጠን እያየን፤
እንደልማዳችን፣ ዝም ተባባልን።
ሰውዬው ቀጠለ፣
ገድለው ሲጥሏቸው፣ በዓይኖቼ አየሁ አለ!
ዘለው ያልጠገቡ፣
እህል የተራቡ፣
አገር የተቀሙ፣
ፍትሕ የተጠሙ፣
አንድ ፍሬ ናቸው!
ገና እንዳገኟቸው፣
ከበው ይዘዋቸው፣
መሣሪያ አስጠግተው፣ ወደ ግንባራቸው፣
ጭንቅላታቸውን … ፈረካከሷቸው።

እያለ ሲናገር፣
ሰውዬው ሲቆጣ፣ ሲያለቅስ ሲያማርር፣
እኔም ልክ እንደሱው፣ በዓይኖቹ ገብቼ፣
አንገቴን አቅፌ፣ በሁለት እጆቼ፣
ጉልበቴ እየራደ፣ ነፍሴ እየበነነች፣
አውጣኝ! ከዚህ ቦታ፣ አድነኝ እያለች፣
ስትለማመጠኝ!
የደም ፍንጣቂ፣ አካሌን ሲያለብሰኝ
እሱ ቦታ ቆሜ፣ እሱን ሆኜ አየሁኝ።

ሰውዬው ቀጠለ፣
ቴሌቭዥን አይቶ፣ እኚህ ናቸው አለ።
ቢራውን ጨለጠ፣
ዓይኑን አፈጠጠ፣
ውሸታሞች ናቸው! ሽብርተኛ አይደሉም፣
ጨርሶ! በጃቸው፣ መሣሪያም አልያዙም፣
አይቻለሁ በዓይኔ፣ ነጻ ልጆች ናቸው፣
ምንም ሳያጠፉ፣ ነው የገደሏቸው!
ኡ! ኡ! አለ ሰውዬው፣ እንደሰማ መርዶ፣
በዜናው እወጃ፣ ክፉኛ ተናዶ
ነገሩ እየቆጨኝ፣ እያንገበገበኝ፣
ጀብረር እንዲያደርገኝ፣
ፍራት እንዲርቀኝ፣
አልኮሌን ደገምኩኝ።

ሰውዬው ተናግሮ አልወጣልህ ቢለው፣
ኡ! ኡ! ብሎ ጮኾ፣ ማልቀስም አማረው!
እሪ! አለ ሰውዬው፣ ንዴቱ ጨመረ፣
ጩኸቱን ለቀቀው፣ ቤቱ ተሸበረ።
ተንጋግቶ ደረሰ፣ ፌደራልም መጣ፣
ይጎትቱት ጀመር፣ እውጪ እንዲወጣ፣
ይሄኔ ተነሳሁ፣ አትነኩትም! አልኩኝ፣
ሰውዬውን ላስጥል፣ ከመሃል ገባሁኝ።
ምን አ’ረገ! አልኳቸው፣
ጥፋቱን ንገሩኝ? ብዬ ጠየኳቸው!
ሽብርተኛ ሲሞት፣ ተንሰቅስቆ አልቅሷል፣
ሕዝብ መሃል ሆኖ፣ ሰላም አደፍርሷል፣
ብለው ሲናገሩ፣ እንደ እብድ አ’ረገኝ፣
ጭራሽ አትወስዱትም! አትነኩትም አልኩኝ።
ያለው ሁሉ እንደኔ፣ በአንድ ላይ አደመ፣
መሃላቸው ገብቶ፣ አሰፍስፎ ቆመ።
ከዛ ቤቱ ሁሉ፣ መተረማመሱ፣
ትንሽ ትዝ ይለኛል፣ ጥይት መተኮሱ
ካለሁበት ቦታ፣ ለሊት ብንን ስል፣
ማንም በሌለበት፣ በጨለማ ክፍል፣
ዘለው ያልጠገቡ፣
እህል የተራቡ፣
አገር የተቀሙ፣
ፍትሕ የተጠሙ፣
አንድ ፍሬ ናቸው!
ገና እንዳገኟቸው፣
ከበው ይዘዋቸው፣
ጭንቅላታቸውን … ፈረካከሷቸው።
እያለ ይጮሃል፣
የዛ ሰውዬ ድምጽ፣ አሁንም ይስማል።

Filed Under: Literature Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

Recent Posts

  • ሕገወጡ ትህነግ ወጣቶችን ለዳግም ዕልቂት እያሰናዳ ለፈረንጆች “ኢትዮጵያን አውግዙልኝ” እያለ ነው June 11, 2026 12:57 am
  • በሐዘንና ግልፅ ደብዳቤ ስም የተሸፈነ የድህረ ምርጫ ሀገር የማተራመስ ስትራቴጂ June 10, 2026 12:19 am
  • የጽምዶ ልክፍት June 9, 2026 12:49 am
  • ገዳዩ ማነው? አስገዳዩስ ማነው? June 5, 2026 02:37 pm
  • ጽንፈኝነት ግን በኢትዮጵያ ምድር ፈጽሞ ቦታ የለውም! June 5, 2026 01:47 pm
  • የትብብሩ “ብናሸንፍም ፓርላማ አንገባም” መግለጫ “ወንበር ስታጡ ነው” የሚል ከፍተኛ ተቃውሞ አስነሳ June 4, 2026 12:04 am
  • አዲሱ የትራምፕ የምርጫ መመሪያ፡ የአሜሪካ ዲፕሎማቶችን አፍ ያስዘጋ፤ ተቃዋሚዎች ተስፋ ያስቆረጠ June 3, 2026 08:50 pm
  • “ኢህአፓ ከምርጫው በኋላ ይሰነጠቃል” May 29, 2026 07:07 pm
  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
Copyright © 2026 · Goolgule