• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ለመለስ የተፃፈ ደብዳቤና የመለስ መልስ

October 11, 2016 08:26 pm by Editor 3 Comments

ከፍቃዱ ጌታቸው ለመለስ

እንደምን አለህ ጋሼ እንደምን ነህ መለስ
ትመጣለህ ስንል ቀረህ ሳትመለስ
እኛማ ይሔውልህ
ባንተ ሌጋሲና ባንተ ትልቅ ራዕይ
በየአደባባዩ እንላለን ዋይ ዋይ
ዛሬም ጀነራልህ ተኩስ ነው ትዕዛዙ
ወገን ያጋድማል የግፍ አፈሙዙ
ለምንድን ነው ስንል ስምክን አስቀድመው
ከክርስቶስ በላይ ምስልህን አትመው
ቅዱስ መጽሐፍ ይመስል
ባንተ ራዕይና በሌጋሲህ ምለው
ቢረፈርፉንም አላለቅንምና
ደብዳቤ ላክንልህ ከሞት የተረፍነው!
…
የሆነስ ሆነና ግን አንተ ደህና ነህ
እኛማ ይኸውልህ
ደርሰህ ስትናፍቀን
አይሞትም የምትል ሙዚቃ ሞዝቀን
መቃብርህን ልንስም አበባ ልናኖር ሥላሴ ብንመጣ
ፌደራል ያይሃል እስረኛ ይመስል ሾልከህ እንዳትወጣ
መቼም ሥላሴ ውስጥ
ባለስም ነውና የሚቀበርበት
አንተን አየት አርገን ዞር ስንል ድንገት
እነፊታውራሪ
ግራ’ዝማች
ቀኝ’ዝማች
ፊተኛ ባለስም የሆኑት አባቶች
ያለዘብ ቆመዋል እነ አብዲሳ አጋ
ጀግና መሃል ሳለህ ምነው በድንህ ሰጋ!
…
የሆነስ ሆነና
ኃየሎም ደህና ነው
እዛም ትግል ይመራል
እስር ቤት ሰባብሮ ታራሚ ያስፈታል
እዛም ከፊት ሆኖ ጭቁን ያታግላል
እዛም በጀግንነት በለኮሳት ሻማ
ነፃ ነኝ ባለባት ርዕሰ ከተማ
ትንሽ ግሮሰሪ ይገባ ይሆን ደፍሮ
እዛስ ጀማል ያሲን ፈጠረ አምባጓሮ
ኃየሎምን ሰዋው በሐሺሽ ናላው ዞሮ
እኛማ ይኸውልህ ብዙ ኃየሎሞች ፈጥረን ስናበቃ
እልፍ ጀማል ያሲን ይሆናል ጥበቃ
ይኸው ባደባባይ የጀግኖቻችን ደም በየቦታው ፈሶ
አለ ጀማል ያሲን ሞት ሚበይንበት ፍርድ ቤቱ ፈርሶ!!
…
ግን አንተ ደህና ነህ
አቡነ ጳውሎስስ ብፁው እንዴት ናቸው
እዚያም እንደምድሩ አንድ አንቀጽ ያክላል መጠሪያ ስማቸው
ደረታቸው ግድም “ሽጉጥ” የሚያደርጉት አለ መስቀላቸው
እኛማ ይኸውልህ
ዳያስፖራ ጳጳስ ሾመን ባደባባይ
ከበዓል ቀን ውጪ ፊታቸውን አናይ
ሰው ሲሞት
ህዝብ ሲያልቅ
እምነት ሲተራመስ አያውቁም ግሳጤ
ዝም ዝም ናቸው
ቆባቸው የጳጳስ ነብሳቸው የአጤ!!
…
እንደምን አለህ ጋሼ እንደምን ነህ መለስ
ትመጣለህ ስንል ቀረህ ሳትመለስ
…
…
…
ከቻልክ ፃፍልን ለደብዳቤያችን መልስ!!**

ከመለስ ለፍቃዱ ጌታቸው
(ወለላዬ)

ደብዳቤህ ደርሶኛል ሰሞኑን የላከው
እንዴት! ከረምክልኝ? ፍቃዱ ጌታቸው
ነበልባሉ መሃል፣ በሲዖል አዳራሽ
በተነጠፈልኝ ሠፊ የእሳት ፍራሽ
እየተጠበስኩኝ፣ በቁጭት በምሬት
ጽሑፉን በሙሉ አንብቤ ጨረስኩት
ምነው ቀረህ ያልከኝ በዛው ሳትመለስ
አጣድፎ ወስዶኝ ነው አባቴ ዳቢሎስ
ያስጨኹኛል ያልከው በየአደባባዩ
ባላስጮኹኽ ነበር እዚህ እኔን ቢያዩ
ውሸት ቦታም ብሆን እውነት ለመናገር
መከራ እየቀመስኩ እያየሁ ነው አሳር

ሥላሴ በመሄድ እኔን የፈለከኝ
እንደው ለፋህ እንጂ እዛ የታለሁኝ
ለሥልጣን ዕድሜያቸው ለማወናበጃ
አ’ርገው አስቀምጠውኝ እኔን መቀለጃ
ሌጋሲው እያሉ እያወናበዱ
ሰማሁኝ በስሜ እንደሚነግዱ
እንኳንስ የተውኩት ዕራይ ሊኖረኝ
የራሴው ራዕይ ለራሴም አልበጀኝ
አስራ ዘጠኝ ዓመት በከተማ መሃል
አስራ ሰባት ዓመት በበረሃ ትግል
ሃያ አንድ ዓመታት ሀገር ሳተራምስ
ሳላየው ከርሜ የኔን ጉድጓድ መማስ
ከሄድኩበት ቀረኹ በዛው ሳልመለስ
ሌሎቹም አይቀሩም ተጠርቷል ስማቸው
አንተስ! እንደምነህ ፍቃዱ ጌታቸው?

የህወሓት አባላት ኃየሎም ምናምን
አሰፋ ማሞና ክንፈ ገ/መድህን
በደህና ጊዜ ነው ወደዚህ የመጡት
ይብላኝ በአሁን ሰዓት በሥልጣን ላይ ላሉት
በህዝብ ተይዘው ልክ! እንደጋዳፊ
እየተወገሩ በርግጫ በጥፊ!
ይመጣሉ እዚሁ አይቀርም ሞታቸው
ይፈንጩ ግድ የለም እስከዛ ተዋቸው

እንደው ለመሆኑ በረከት ስምኦን
እንዴት አደረጋት የቆየች ህመሙን?
እንዴትስ! ዘገየ እስካሁን ሳይመጣ?
ፊቱስ ምን መሰለ? ጠቆረ ወይ ነጣ?
እነ አቦይ ስብሓት፣ እነ ስዩም መስፍን
እነ ገነት ዘውዴ፣ እነ ደብረጽዮን
እነ አባይ ፀሓዬ፣ ቴዎድሮስ አድኃኖም
ሳሞራ፣ አባዱላ፣ እነ ኃይለማርያም
ወርቅነህ ገበየሁ፣ እርከበ እቁባይ
እያወናበዱ ተቀምጠው አንድ ላይ
እስከመቼ ድረስ ሊኖሩ አስበዋል?
ከኔ ከተለዩ ስንት ሰው ገድለዋል?
ምን ያህል ገዘፉ፣ ምን ያህል ከበሩ?
ስንት ብር አሸሹ? ስንት ፎቆች ሠሩ?
የተማከርነውን የአማራንስ ማጥፋት
ከኦሮሞ ጋራ ማስነሳቱን ግጭት
እንዴት አደረጉ ከምን አደረሱት?
ዕቅዱ ተሳካ እነሱው ጨረሱት?
እንደው በከንቱ ነው መግደል ማሰራቸው
በቅርብ ይመጣሉ ግዴለም ተዋቸው
አንተስ እንደምነህ ፍቃዱ ጌታቸው?

አባ ጳውሎስንም ያነሳህ መሰለኝ
ወደዛ ተዋቸው አሁን ምን ሊረቡኝ
አክብሬ አስመጥቼ ጎኔ ሳደርጋቸው
ሳጠፋ ገስፀው በአባትነታቸው
ምናለበት ነበር ቢመክሩ ቢቆጡኝ
ልጄ ልጄ እያሉ ለዚህ ከሚያበቁኝ
አሁንማ አብረውኝ የሲዖልን ስቃይ
እየቀመሱ ነው ከኔ ጋር አንድ ላይ
የራሳቸው ጉዳይ ሁሉንም ተዋቸው!
ፊትም እማይረቡ ወራዳዎች ናቸው
ደግሜ ልናገር ወራዳዎች ናቸው
አንተስ እንደምነህ ፍቃዱ ጌታቸው?
***

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Literature Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Comments

  1. Rasdejen says

    October 17, 2016 08:34 pm at 8:34 pm

    Wai Wai Wai:
    https://www.youtube.com/watch?v=D_2HYQVoB1c

    Reply
  2. Rasdejen says

    October 17, 2016 08:45 pm at 8:45 pm

    Melese’s State of Emergency:
    https://www.youtube.com/watch?v=9EOQQd8VwlI

    Reply
  3. Rasdejen says

    October 17, 2016 08:57 pm at 8:57 pm

    TPLF’S major contr. to Ethiopians:

    https://www.youtube.com/watch?v=MxIZAjxMhHQ

    Melese, no birth of yours shall be given chance unless and otherwise the person denies you and remains proper human.

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule