• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ለመለስ የተፃፈ ደብዳቤና የመለስ መልስ

October 11, 2016 08:26 pm by Editor 3 Comments

ከፍቃዱ ጌታቸው ለመለስ

እንደምን አለህ ጋሼ እንደምን ነህ መለስ
ትመጣለህ ስንል ቀረህ ሳትመለስ
እኛማ ይሔውልህ
ባንተ ሌጋሲና ባንተ ትልቅ ራዕይ
በየአደባባዩ እንላለን ዋይ ዋይ
ዛሬም ጀነራልህ ተኩስ ነው ትዕዛዙ
ወገን ያጋድማል የግፍ አፈሙዙ
ለምንድን ነው ስንል ስምክን አስቀድመው
ከክርስቶስ በላይ ምስልህን አትመው
ቅዱስ መጽሐፍ ይመስል
ባንተ ራዕይና በሌጋሲህ ምለው
ቢረፈርፉንም አላለቅንምና
ደብዳቤ ላክንልህ ከሞት የተረፍነው!
…
የሆነስ ሆነና ግን አንተ ደህና ነህ
እኛማ ይኸውልህ
ደርሰህ ስትናፍቀን
አይሞትም የምትል ሙዚቃ ሞዝቀን
መቃብርህን ልንስም አበባ ልናኖር ሥላሴ ብንመጣ
ፌደራል ያይሃል እስረኛ ይመስል ሾልከህ እንዳትወጣ
መቼም ሥላሴ ውስጥ
ባለስም ነውና የሚቀበርበት
አንተን አየት አርገን ዞር ስንል ድንገት
እነፊታውራሪ
ግራ’ዝማች
ቀኝ’ዝማች
ፊተኛ ባለስም የሆኑት አባቶች
ያለዘብ ቆመዋል እነ አብዲሳ አጋ
ጀግና መሃል ሳለህ ምነው በድንህ ሰጋ!
…
የሆነስ ሆነና
ኃየሎም ደህና ነው
እዛም ትግል ይመራል
እስር ቤት ሰባብሮ ታራሚ ያስፈታል
እዛም ከፊት ሆኖ ጭቁን ያታግላል
እዛም በጀግንነት በለኮሳት ሻማ
ነፃ ነኝ ባለባት ርዕሰ ከተማ
ትንሽ ግሮሰሪ ይገባ ይሆን ደፍሮ
እዛስ ጀማል ያሲን ፈጠረ አምባጓሮ
ኃየሎምን ሰዋው በሐሺሽ ናላው ዞሮ
እኛማ ይኸውልህ ብዙ ኃየሎሞች ፈጥረን ስናበቃ
እልፍ ጀማል ያሲን ይሆናል ጥበቃ
ይኸው ባደባባይ የጀግኖቻችን ደም በየቦታው ፈሶ
አለ ጀማል ያሲን ሞት ሚበይንበት ፍርድ ቤቱ ፈርሶ!!
…
ግን አንተ ደህና ነህ
አቡነ ጳውሎስስ ብፁው እንዴት ናቸው
እዚያም እንደምድሩ አንድ አንቀጽ ያክላል መጠሪያ ስማቸው
ደረታቸው ግድም “ሽጉጥ” የሚያደርጉት አለ መስቀላቸው
እኛማ ይኸውልህ
ዳያስፖራ ጳጳስ ሾመን ባደባባይ
ከበዓል ቀን ውጪ ፊታቸውን አናይ
ሰው ሲሞት
ህዝብ ሲያልቅ
እምነት ሲተራመስ አያውቁም ግሳጤ
ዝም ዝም ናቸው
ቆባቸው የጳጳስ ነብሳቸው የአጤ!!
…
እንደምን አለህ ጋሼ እንደምን ነህ መለስ
ትመጣለህ ስንል ቀረህ ሳትመለስ
…
…
…
ከቻልክ ፃፍልን ለደብዳቤያችን መልስ!!**

ከመለስ ለፍቃዱ ጌታቸው
(ወለላዬ)

ደብዳቤህ ደርሶኛል ሰሞኑን የላከው
እንዴት! ከረምክልኝ? ፍቃዱ ጌታቸው
ነበልባሉ መሃል፣ በሲዖል አዳራሽ
በተነጠፈልኝ ሠፊ የእሳት ፍራሽ
እየተጠበስኩኝ፣ በቁጭት በምሬት
ጽሑፉን በሙሉ አንብቤ ጨረስኩት
ምነው ቀረህ ያልከኝ በዛው ሳትመለስ
አጣድፎ ወስዶኝ ነው አባቴ ዳቢሎስ
ያስጨኹኛል ያልከው በየአደባባዩ
ባላስጮኹኽ ነበር እዚህ እኔን ቢያዩ
ውሸት ቦታም ብሆን እውነት ለመናገር
መከራ እየቀመስኩ እያየሁ ነው አሳር

ሥላሴ በመሄድ እኔን የፈለከኝ
እንደው ለፋህ እንጂ እዛ የታለሁኝ
ለሥልጣን ዕድሜያቸው ለማወናበጃ
አ’ርገው አስቀምጠውኝ እኔን መቀለጃ
ሌጋሲው እያሉ እያወናበዱ
ሰማሁኝ በስሜ እንደሚነግዱ
እንኳንስ የተውኩት ዕራይ ሊኖረኝ
የራሴው ራዕይ ለራሴም አልበጀኝ
አስራ ዘጠኝ ዓመት በከተማ መሃል
አስራ ሰባት ዓመት በበረሃ ትግል
ሃያ አንድ ዓመታት ሀገር ሳተራምስ
ሳላየው ከርሜ የኔን ጉድጓድ መማስ
ከሄድኩበት ቀረኹ በዛው ሳልመለስ
ሌሎቹም አይቀሩም ተጠርቷል ስማቸው
አንተስ! እንደምነህ ፍቃዱ ጌታቸው?

የህወሓት አባላት ኃየሎም ምናምን
አሰፋ ማሞና ክንፈ ገ/መድህን
በደህና ጊዜ ነው ወደዚህ የመጡት
ይብላኝ በአሁን ሰዓት በሥልጣን ላይ ላሉት
በህዝብ ተይዘው ልክ! እንደጋዳፊ
እየተወገሩ በርግጫ በጥፊ!
ይመጣሉ እዚሁ አይቀርም ሞታቸው
ይፈንጩ ግድ የለም እስከዛ ተዋቸው

እንደው ለመሆኑ በረከት ስምኦን
እንዴት አደረጋት የቆየች ህመሙን?
እንዴትስ! ዘገየ እስካሁን ሳይመጣ?
ፊቱስ ምን መሰለ? ጠቆረ ወይ ነጣ?
እነ አቦይ ስብሓት፣ እነ ስዩም መስፍን
እነ ገነት ዘውዴ፣ እነ ደብረጽዮን
እነ አባይ ፀሓዬ፣ ቴዎድሮስ አድኃኖም
ሳሞራ፣ አባዱላ፣ እነ ኃይለማርያም
ወርቅነህ ገበየሁ፣ እርከበ እቁባይ
እያወናበዱ ተቀምጠው አንድ ላይ
እስከመቼ ድረስ ሊኖሩ አስበዋል?
ከኔ ከተለዩ ስንት ሰው ገድለዋል?
ምን ያህል ገዘፉ፣ ምን ያህል ከበሩ?
ስንት ብር አሸሹ? ስንት ፎቆች ሠሩ?
የተማከርነውን የአማራንስ ማጥፋት
ከኦሮሞ ጋራ ማስነሳቱን ግጭት
እንዴት አደረጉ ከምን አደረሱት?
ዕቅዱ ተሳካ እነሱው ጨረሱት?
እንደው በከንቱ ነው መግደል ማሰራቸው
በቅርብ ይመጣሉ ግዴለም ተዋቸው
አንተስ እንደምነህ ፍቃዱ ጌታቸው?

አባ ጳውሎስንም ያነሳህ መሰለኝ
ወደዛ ተዋቸው አሁን ምን ሊረቡኝ
አክብሬ አስመጥቼ ጎኔ ሳደርጋቸው
ሳጠፋ ገስፀው በአባትነታቸው
ምናለበት ነበር ቢመክሩ ቢቆጡኝ
ልጄ ልጄ እያሉ ለዚህ ከሚያበቁኝ
አሁንማ አብረውኝ የሲዖልን ስቃይ
እየቀመሱ ነው ከኔ ጋር አንድ ላይ
የራሳቸው ጉዳይ ሁሉንም ተዋቸው!
ፊትም እማይረቡ ወራዳዎች ናቸው
ደግሜ ልናገር ወራዳዎች ናቸው
አንተስ እንደምነህ ፍቃዱ ጌታቸው?
***

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Literature Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Comments

  1. Rasdejen says

    October 17, 2016 08:34 pm at 8:34 pm

    Wai Wai Wai:
    https://www.youtube.com/watch?v=D_2HYQVoB1c

    Reply
  2. Rasdejen says

    October 17, 2016 08:45 pm at 8:45 pm

    Melese’s State of Emergency:
    https://www.youtube.com/watch?v=9EOQQd8VwlI

    Reply
  3. Rasdejen says

    October 17, 2016 08:57 pm at 8:57 pm

    TPLF’S major contr. to Ethiopians:

    https://www.youtube.com/watch?v=MxIZAjxMhHQ

    Melese, no birth of yours shall be given chance unless and otherwise the person denies you and remains proper human.

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • በጦርነቱ የተጎዱ አካባቢዎችን ለማቋቋም የሚውል የ15 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር ድጋፍ የዓለም ባንክ May 16, 2022 10:22 am
  • በአዲስ አበባ 1 ሺህ 98 የብሬን እና 2 ሺህ 162 የክላሽ ጥይት ተያዘ May 16, 2022 10:10 am
  • በአዲስ አበባ ከተማ በግለሰብ መኖሪያ ቤት ከ5 ሺህ በላይ የአሜሪካ ዶላርና የተለያዩ አገራት ገንዘቦች ተያዙ May 16, 2022 09:53 am
  • አገር አፍራሹ ትህነግ ለቀለብ፣ መድኃኒትና ሥራ ማስኬጃ 76 ቢሊዮን ብር ቀርጥፏል May 16, 2022 08:30 am
  • እየተባባሰ ከመጣው የማህበራዊ ሚዲያ አጭበርባሪዎች ዜጎች ራሳቸውን እንዲጠብቁ ተጠየቀ May 15, 2022 09:38 am
  • የትህነግና ሸኔ መሠልጠኛ የምትባለው ዩጋንዳ መከላከያ ሚ/ር ከኤታማዦር ሹሙ ጋር ተወያዩ May 13, 2022 09:55 am
  • በትግራይ የውጊያ ምልመላው ጉዳይ May 11, 2022 02:37 am
  • መከላከያ በተጨማሪ ድሮን፣ በሥልጠና፣ በዝግጅት ራሱን አብቅቷል May 11, 2022 01:35 am
  • ትህነግ ለሌላ ውጊያ እየተዘጋጀ ነው ተባለ May 10, 2022 01:04 pm
  • ኤርትራ 8 ሩስያ ሠራሽ ድሮኖችን ተረክባለች May 10, 2022 12:37 am
  • ሙስሊምና ክርስቲያን በአንድነት የሚያከብረው የአኾላሌ ባሕላዊ ጭፈራ May 9, 2022 01:46 pm
  • በወልዲያ ፋኖዎች ተመረቁ May 9, 2022 12:51 pm
  • “ሠራዊታችን ድልን በአስተማማኝ መልኩ ማምጣት በሚችል ቁመና ላይ” ጀኔራል ጌታቸው May 9, 2022 11:57 am
  • ዋጋው 64 ሚሊዮን ብር የሚሆን (16 ኪሎ) ሕገወጥ ወርቅ ተያዘ May 9, 2022 11:51 am
  • አብን ክርስቲያን ታደለን ለመጨረሻ ጊዜ አስጠነቀቀ፤ 10 አባላቱን አገደ May 9, 2022 08:58 am
  • ራሱ አቡክቶ፣ ራሱ አሟሽሾ፣ ራሱ ጋግሮ በሰዓት 460 እንጀራ የሚያወጣ ፈጠራ May 9, 2022 08:17 am
  • በህገ ወጥ መንገድ 19 ህጻናትን ሲያዘዋወሩ የነበሩ 6 ሴቶች ተያዙ May 8, 2022 12:39 am
  • በአርሲ ሙስሊሞች ለቤ/ክ ማሠሪያ 3 ሚሊዮን ብርና 20 የቀንድ ከብት ሰጡ May 6, 2022 09:35 am
  • በአዲስ አበባ የሚኖረው የትህነግ ደጋፊ ማንነት በማስረጃ May 4, 2022 11:04 pm
  • ሙስሊም ወንድማማች የቤ/ክ ዘራፊዎችን በቁጥጥር ሥር አዋሉ May 4, 2022 09:04 am
  • ከ6 ሺህ የዓሳ ጫጩት ወደ 80 ሺህ May 4, 2022 08:57 am
  • ተስፋቢሱ ቴድሮስ May 3, 2022 12:16 pm
  • ከሽፏል! April 6, 2022 11:58 am
  • “ሩሲያ ዩክሬይንን ወረረች” እየተባለ ስለሚነዛው ወሬ ጥቂት እውነታዎች March 8, 2022 11:30 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2022 · Goolgule