• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ለመለስ የተፃፈ ደብዳቤና የመለስ መልስ

October 11, 2016 08:26 pm by Editor 3 Comments

ከፍቃዱ ጌታቸው ለመለስ

እንደምን አለህ ጋሼ እንደምን ነህ መለስ
ትመጣለህ ስንል ቀረህ ሳትመለስ
እኛማ ይሔውልህ
ባንተ ሌጋሲና ባንተ ትልቅ ራዕይ
በየአደባባዩ እንላለን ዋይ ዋይ
ዛሬም ጀነራልህ ተኩስ ነው ትዕዛዙ
ወገን ያጋድማል የግፍ አፈሙዙ
ለምንድን ነው ስንል ስምክን አስቀድመው
ከክርስቶስ በላይ ምስልህን አትመው
ቅዱስ መጽሐፍ ይመስል
ባንተ ራዕይና በሌጋሲህ ምለው
ቢረፈርፉንም አላለቅንምና
ደብዳቤ ላክንልህ ከሞት የተረፍነው!
…
የሆነስ ሆነና ግን አንተ ደህና ነህ
እኛማ ይኸውልህ
ደርሰህ ስትናፍቀን
አይሞትም የምትል ሙዚቃ ሞዝቀን
መቃብርህን ልንስም አበባ ልናኖር ሥላሴ ብንመጣ
ፌደራል ያይሃል እስረኛ ይመስል ሾልከህ እንዳትወጣ
መቼም ሥላሴ ውስጥ
ባለስም ነውና የሚቀበርበት
አንተን አየት አርገን ዞር ስንል ድንገት
እነፊታውራሪ
ግራ’ዝማች
ቀኝ’ዝማች
ፊተኛ ባለስም የሆኑት አባቶች
ያለዘብ ቆመዋል እነ አብዲሳ አጋ
ጀግና መሃል ሳለህ ምነው በድንህ ሰጋ!
…
የሆነስ ሆነና
ኃየሎም ደህና ነው
እዛም ትግል ይመራል
እስር ቤት ሰባብሮ ታራሚ ያስፈታል
እዛም ከፊት ሆኖ ጭቁን ያታግላል
እዛም በጀግንነት በለኮሳት ሻማ
ነፃ ነኝ ባለባት ርዕሰ ከተማ
ትንሽ ግሮሰሪ ይገባ ይሆን ደፍሮ
እዛስ ጀማል ያሲን ፈጠረ አምባጓሮ
ኃየሎምን ሰዋው በሐሺሽ ናላው ዞሮ
እኛማ ይኸውልህ ብዙ ኃየሎሞች ፈጥረን ስናበቃ
እልፍ ጀማል ያሲን ይሆናል ጥበቃ
ይኸው ባደባባይ የጀግኖቻችን ደም በየቦታው ፈሶ
አለ ጀማል ያሲን ሞት ሚበይንበት ፍርድ ቤቱ ፈርሶ!!
…
ግን አንተ ደህና ነህ
አቡነ ጳውሎስስ ብፁው እንዴት ናቸው
እዚያም እንደምድሩ አንድ አንቀጽ ያክላል መጠሪያ ስማቸው
ደረታቸው ግድም “ሽጉጥ” የሚያደርጉት አለ መስቀላቸው
እኛማ ይኸውልህ
ዳያስፖራ ጳጳስ ሾመን ባደባባይ
ከበዓል ቀን ውጪ ፊታቸውን አናይ
ሰው ሲሞት
ህዝብ ሲያልቅ
እምነት ሲተራመስ አያውቁም ግሳጤ
ዝም ዝም ናቸው
ቆባቸው የጳጳስ ነብሳቸው የአጤ!!
…
እንደምን አለህ ጋሼ እንደምን ነህ መለስ
ትመጣለህ ስንል ቀረህ ሳትመለስ
…
…
…
ከቻልክ ፃፍልን ለደብዳቤያችን መልስ!!**

ከመለስ ለፍቃዱ ጌታቸው
(ወለላዬ)

ደብዳቤህ ደርሶኛል ሰሞኑን የላከው
እንዴት! ከረምክልኝ? ፍቃዱ ጌታቸው
ነበልባሉ መሃል፣ በሲዖል አዳራሽ
በተነጠፈልኝ ሠፊ የእሳት ፍራሽ
እየተጠበስኩኝ፣ በቁጭት በምሬት
ጽሑፉን በሙሉ አንብቤ ጨረስኩት
ምነው ቀረህ ያልከኝ በዛው ሳትመለስ
አጣድፎ ወስዶኝ ነው አባቴ ዳቢሎስ
ያስጨኹኛል ያልከው በየአደባባዩ
ባላስጮኹኽ ነበር እዚህ እኔን ቢያዩ
ውሸት ቦታም ብሆን እውነት ለመናገር
መከራ እየቀመስኩ እያየሁ ነው አሳር

ሥላሴ በመሄድ እኔን የፈለከኝ
እንደው ለፋህ እንጂ እዛ የታለሁኝ
ለሥልጣን ዕድሜያቸው ለማወናበጃ
አ’ርገው አስቀምጠውኝ እኔን መቀለጃ
ሌጋሲው እያሉ እያወናበዱ
ሰማሁኝ በስሜ እንደሚነግዱ
እንኳንስ የተውኩት ዕራይ ሊኖረኝ
የራሴው ራዕይ ለራሴም አልበጀኝ
አስራ ዘጠኝ ዓመት በከተማ መሃል
አስራ ሰባት ዓመት በበረሃ ትግል
ሃያ አንድ ዓመታት ሀገር ሳተራምስ
ሳላየው ከርሜ የኔን ጉድጓድ መማስ
ከሄድኩበት ቀረኹ በዛው ሳልመለስ
ሌሎቹም አይቀሩም ተጠርቷል ስማቸው
አንተስ! እንደምነህ ፍቃዱ ጌታቸው?

የህወሓት አባላት ኃየሎም ምናምን
አሰፋ ማሞና ክንፈ ገ/መድህን
በደህና ጊዜ ነው ወደዚህ የመጡት
ይብላኝ በአሁን ሰዓት በሥልጣን ላይ ላሉት
በህዝብ ተይዘው ልክ! እንደጋዳፊ
እየተወገሩ በርግጫ በጥፊ!
ይመጣሉ እዚሁ አይቀርም ሞታቸው
ይፈንጩ ግድ የለም እስከዛ ተዋቸው

እንደው ለመሆኑ በረከት ስምኦን
እንዴት አደረጋት የቆየች ህመሙን?
እንዴትስ! ዘገየ እስካሁን ሳይመጣ?
ፊቱስ ምን መሰለ? ጠቆረ ወይ ነጣ?
እነ አቦይ ስብሓት፣ እነ ስዩም መስፍን
እነ ገነት ዘውዴ፣ እነ ደብረጽዮን
እነ አባይ ፀሓዬ፣ ቴዎድሮስ አድኃኖም
ሳሞራ፣ አባዱላ፣ እነ ኃይለማርያም
ወርቅነህ ገበየሁ፣ እርከበ እቁባይ
እያወናበዱ ተቀምጠው አንድ ላይ
እስከመቼ ድረስ ሊኖሩ አስበዋል?
ከኔ ከተለዩ ስንት ሰው ገድለዋል?
ምን ያህል ገዘፉ፣ ምን ያህል ከበሩ?
ስንት ብር አሸሹ? ስንት ፎቆች ሠሩ?
የተማከርነውን የአማራንስ ማጥፋት
ከኦሮሞ ጋራ ማስነሳቱን ግጭት
እንዴት አደረጉ ከምን አደረሱት?
ዕቅዱ ተሳካ እነሱው ጨረሱት?
እንደው በከንቱ ነው መግደል ማሰራቸው
በቅርብ ይመጣሉ ግዴለም ተዋቸው
አንተስ እንደምነህ ፍቃዱ ጌታቸው?

አባ ጳውሎስንም ያነሳህ መሰለኝ
ወደዛ ተዋቸው አሁን ምን ሊረቡኝ
አክብሬ አስመጥቼ ጎኔ ሳደርጋቸው
ሳጠፋ ገስፀው በአባትነታቸው
ምናለበት ነበር ቢመክሩ ቢቆጡኝ
ልጄ ልጄ እያሉ ለዚህ ከሚያበቁኝ
አሁንማ አብረውኝ የሲዖልን ስቃይ
እየቀመሱ ነው ከኔ ጋር አንድ ላይ
የራሳቸው ጉዳይ ሁሉንም ተዋቸው!
ፊትም እማይረቡ ወራዳዎች ናቸው
ደግሜ ልናገር ወራዳዎች ናቸው
አንተስ እንደምነህ ፍቃዱ ጌታቸው?
***

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Literature Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Comments

  1. Rasdejen says

    October 17, 2016 08:34 pm at 8:34 pm

    Wai Wai Wai:
    https://www.youtube.com/watch?v=D_2HYQVoB1c

    Reply
  2. Rasdejen says

    October 17, 2016 08:45 pm at 8:45 pm

    Melese’s State of Emergency:
    https://www.youtube.com/watch?v=9EOQQd8VwlI

    Reply
  3. Rasdejen says

    October 17, 2016 08:57 pm at 8:57 pm

    TPLF’S major contr. to Ethiopians:

    https://www.youtube.com/watch?v=MxIZAjxMhHQ

    Melese, no birth of yours shall be given chance unless and otherwise the person denies you and remains proper human.

    Reply

Leave a Reply to Rasdejen Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ጎርጎራ – የመጻዒው ዘመን ሙሽራ! የዉበት ፈርጥ! January 17, 2023 04:18 pm
  • ሁለተኛው መስቀል አደባባይ January 17, 2023 04:13 pm
  • በአቡዳቢ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን January 17, 2023 04:08 pm
  • በንፋስ ስልክ ላፍቶ ስምንት የመሬት ሌቦች ተያዙ January 16, 2023 11:36 am
  • ሺሻ ሲያስጨሱ በተገኙ ሆቴሎችና የምሽት ጭፈራ ቤቶች ላይ እርምጃ ተወሰደ January 16, 2023 08:50 am
  • በሐሰተኛ መታወቂያ የደኅንነት አባል ነን ብለው ሲያጭበረብሩ የነበሩ ተያዙ January 13, 2023 02:03 pm
  • ተሽከርካሪ ወንበር ለትግራይ – “ናይ ኣካል ጉዱኣት ተሽከርካሪ ዘለዎ ወንበር” January 12, 2023 07:17 pm
  • የአማራው ኩራት፣ የኢትዮጵያ ዘብ፣ የትህነግን ቅስም ሰባሪ! January 12, 2023 04:00 pm
  • በኢትዮጵያ ላይ የተጣሉ ማዕቀብ እና ሌሎች አስገዳጅ ሕጎች ሙሉ ለሙሉ ተሰረዙ January 12, 2023 01:52 pm
  • የቻይና ዕዳ ስረዛ “Payday Loan Diplomacy” ወይስ ኢትዮጵያን ያዳነ ተግባር? January 12, 2023 11:00 am
  • የአዲስ አበባ አስተዳደር ከቋንቋ ጋር በተያያዘ ውሳኔ አስተላለፈ January 12, 2023 10:46 am
  • “አምባሳደሩ” የቀድሞ ጌቶቻቸውን እንዲያቋቁሙ ተሾሙ January 11, 2023 03:47 pm
  • መከላከያ ሸኔን የሚዋጉ ሚሊሻዎችን አሠልጥኖ አስመረቀ January 10, 2023 05:37 pm
  • በሰባት ተጠርጣሪዎች ላይ ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመሰረተ January 10, 2023 03:36 pm
  • የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ አቅጣጫ January 6, 2023 03:26 pm
  • “ከዕብሪቱ አስተንፍሰነዋል” – ኢሳያስ January 2, 2023 07:29 pm
  • [ኢትዮጵያን] “አስታክኮ ኤርትራን መውጋት ለሚፈልግ ኃይል አንተባበርም” January 2, 2023 07:11 pm
  • የ፰ ወር ሕጻንና ጨቅላ ወንዶች የሚደፈሩባት ትግራይ December 14, 2022 02:49 pm
  • “ሰውን ለመርዳት ሰው መሆን ብቻ በቂ ነው” የደጎች አውራ የመቄዶኒያው ቢንያም በለጠ December 14, 2022 09:59 am
  • “የሀብት ምዝገባ መረጃው ለሕዝብ ክፍት ይደረግ “ December 13, 2022 10:30 am
  • የኢትዮጵያ ዓለምአቀፋዊ የሌብነት ደረጃ December 13, 2022 09:42 am
  • ለብረት አቅላጮች ለመሸጥ በኤሌክትሪክ የብረት ማማዎች ስርቆት የ100 ሚሊዮን ብር ኪሳራ December 13, 2022 09:26 am
  • በትግራይ የሰላም ስምምነቱን መሠረት ያደረገ የሽግግር ፍትሕ እንደሚፈጸም ተገለጸ December 13, 2022 09:20 am
  • ከ30 ሚሊየን ብር በላይ በሚሆን ሌብነት የተከሰሱት የደኅንነት መ/ቤት ሠራተኞች ክስ ተመሰረተ December 13, 2022 09:06 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule