በደርግ ዘመነ መንግሥት የኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትርና የትምህርት ሚኒስትር የነበሩት ኮ/ል ጎሹ ወልዴ ዛሬ አዲስ አበባ ገብተዋል። የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ ወ/ሮ ሂሩት ዘመንና እና በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የአሜሪካ ጉዳዮች ዳይሬክተር ጀነራል አቶ ነብያት ጌታቸውን ጨምሮ ከፍተኛ የመንግስት የሥራ ሃላፊዎች አቀባበል አድርግውላቸዋል። የቀድሞው ሚኒስትር በቦሌ አለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ የደርግን አገዛዝ በመቃወም ሃላፊነታቸውን በፈቃዳቸው ከለቀቁና ኑሯቸውን በአሜሪካ ካደረጉ ጀምሮ ላለፉት 32 አመታት የአገራቸውን መሬት ሲረግጡ የመጀመሪያቸው መሆኑን ገልፀዋል። ኮ/ል ጎሹ ወልዴ አመጣጣቸው የአገሪቱን አጠቃላይ የለውጥ ሂደት ለማየት፣ ለረጅም ጊዜ የናፈቋቸውን ዘመድ ወዳጆች ለማግኘትና የተጀመረውን የሰላም፣ የፍቅርና የመደመር ሂደት በሚችሉት መጠን … [Read more...] about ኮ/ል ጎሹ ወልዴ አዲስ አበባ ገቡ
Left Column
በሐሰት ውንጀላ ተመራማሪ ተማሪዎች በግፍ ተገደሉ
ከአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ለዶክትሬት ማጠናቀቂያ ጥናታቸው ወደ ምዕራብ ጎጃም ዞን ጎንጅ ቆለላ ወረዳ ወደ አዲስ አለም ከተማ ተጉዘው የነበሩ ግለሰቦች ላይ በተፈፀመ ጥቃት ሁለቱ ሲገደሉ አንዱ መቁሰሉን የዞኑ የመንግሥት ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ለአሜሪካ ድምፅ ተናገሩ። አጥኒዎቹ በከተማው ባለው አንድ ትምሕርት ቤት ውስጥ ለምርምር የሚሆን የሽንትና የዐይነ ምድር ናሙና እየሰበሰቡ ባሉበት ወቅት፤ “ሦስት ተማሪዎች ሞቱ” የሚል ወሬ በመሰራጨቱ ተቆጥተው በመጡ የአካባቢው ወጣቶች በደረሰባቸው ከፍተኛ ጥቃት ሕይወታቸው ማለፉን የምዕራብ ጎጃም ዞን የመንግስት ኮሙዩኒኬሽን መምሪያ ኃላፊ አቶ አንማው ዳኛቸው ለአሜሪካ ድምፅ ተናግረዋል። በተጨማሪም ለቤተ ክርስቲያን ህንፃ ግንባታ ግልጋሎት የሚውል ሲሚንቶ በራሳቸው መኪና ጭነው ወደ አካባቢው ተጉዘው የነበሩ ጥንዶች ንብረትም መቃጠሉ … [Read more...] about በሐሰት ውንጀላ ተመራማሪ ተማሪዎች በግፍ ተገደሉ
“እርካብና መንበር” – ሙሴ እና ዐብይ*
ሳይታሰብ ብልጭ ብላ እንደገና ድርግም ያለችው የለውጥ ጭላንጭል፣ በእያንዳንዱ ልብ ውስጥ ተቋጥራ የነበረች የተስፋ ስንቅንም ይዛ ጭልጥ ያለች ይመስላል። አዕምሯችን ይህንን ቅጽበታዊ ለውጥ ለመቀበል ቢቸግረውም፣ በሌላኛው መነጽር ስንመለከተው ግን ይህ ሊሆን ግድ ይላል። በተዓምር የቆመች የዚህች የደም ምድር እጣ ፈንታን መጽሃፉ በአንዲት ምዕራፍ ውስጥ እንደቋጫት እንገነዘባለን። አይናችንን በደንብ ካልገለጥን ግን ነገሩን ላናየው እንችላለን። ስለዚህ መፅሐፉን ማንበብ ብቻ በቂ አይደለም። መረዳትንም ይጠይቃል። በደንብ የተረዳው ሰው፣ በለሆሳስ የተላለፈ መልዕክቱን ያገኘዋል። መልዕክቱም ግልጽ ነው። የነጻነት ተጋድሎ። በዚህ ፍልሚያ ውስጥ ሶስት ተዋንያን ይኖራሉ። ተሻጋሪ ሕዝብ፣ አሻጋሪ ሰው እና አሳዳጅ ሃይል። ከብዙ ትንቅንቅ እና ተጋድሎ በኋላ የአሳዳጁ ገቢር ከትዕይንቱ ይወጣና ሁለቱ … [Read more...] about “እርካብና መንበር” – ሙሴ እና ዐብይ*
ኢትዮጵያዊነትና የብሔር ማንነት ተደጋጋፊ ወይስ ተገዳዳሪ?
“ኢትዮጵያ አገራችን የየራሳችን አኩሪ ባህል ያለን፣ የየራሳችን መልክዓ ምድር፣ አሰፋፈር የነበረንና ያለን፣ ብሔር ብሐረሰቦችና ሕዝቦች በተለያዩ መስኮችና የግንኙነት ደረጃዎች ተሳስረን አብረን የኖርንባትና የምንኖርባት አገር በመሆንዋ ያፈራነው የጋራ ጥቅምና አመለካከት አለን ብለን ስለምናምን፣ መጪው የጋራ ዕድላችን መመሥረት ያለበት ከታሪካችን የወረስነውን የተዛባ ግንኙነት በማረምና የጋራ ጥቅማችንን በማሳደግ ላይ መሆኑን በመቀበል ጥቅማችንን፣ መብታችንንና ነፃነታችንን በጋራና በተደጋጋፊነት ለማሳደግና አንድ የኢኮኖሚ ማኅበረሰብ የመገንባቱን አስፈላጊነት በማመን እኛ የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ይኼንን ሕገ መንግሥት በተወካዮቻቸው አማካይነት አፅድቀነዋል።” ከላይ የተገለጸው በ1987 ዓ.ም. ከፀደቀው የኢትዮጵያ ሕገ መንግሥት መግቢያ ላይ የተወሰደና አገሪቱ ካለፉት 23 … [Read more...] about ኢትዮጵያዊነትና የብሔር ማንነት ተደጋጋፊ ወይስ ተገዳዳሪ?
የጎሳ ፖለቲካ ጣጣ፣ ‘ሀዘናችን ቅጥ አጣ’
ከአንድ ሃዘን ወደ ሌላ፤ ላለፉት ጥቂት ወራት ክልላትን እያዳረሰ ያለውና ጎሳ ላይ ያነጣጠረው ግጭት ከቡራዩ ሃዘን ሳናገግም በዚህ ሳምንት ደግሞ ዳግም ወደ ቤኒሻንጉል ጉሙዝ ዞረ። በክልሉ ይኖሩ የነበሩ የኦሮሞ፣ አማራ እና የሌሎች ብሔር ተወላጆች ላይ ሌላ አስከፊ ጥቃት መፈጸሙን መርዶ ሰማን። ሰዎች ተገድለዋል፤ በአሥር ሺዎች ተፈናቅለዋል። ለዚህም ጥቃት የተለያዩ ኃይሎች እንደ ምክንያት እየተጠቀሱ ነው። ከእንዲህ ያለው አስነዋሪ እና እጅግ ኋላ ቀር ከሆነ የጎጠኝነት ስሜት እንዴት ይሆን የምንላቀቀው? በጎጥ ጥላቻ ላይ ምህለቁን የጣለው ዘር ተኮር ፖለቲካችንስ መቼ ይሆን የሚጸዳው? ከእንዲህ ያለው ቅርቃር ለመውጣት እንደ ሰው ማሰብ ብቻ ይበቃን ነበር። ከዚያም ሲያልፍ የአንድ አገር ልጆች በመሆናችን ብቻ ልንተዛዘን፣ ልንደጋገፍ እና አብረን ልንኖር በቻልን ነበር። ይህ ሁሉ ቢቀር በየጎሳ … [Read more...] about የጎሳ ፖለቲካ ጣጣ፣ ‘ሀዘናችን ቅጥ አጣ’
የጠብ ሱስ
ከጅብ ከበሮ የተሰራ አታሞ ዘወትር እንብላው፤ እንብላው ይላል የሚል ተረት ሰምቻለሁ ልበል? አዎ፤ ሳልሰማ አልቀርም። ሀሳቡም ግን ጅብ ቆዳ ሆኖ እንኳን (ቆዳ ሆኖ ብቻ አይደለም አታሞ ተለጉሞበትም) ያው የተፈጥሮ እንብላ ባይ ባህሪውን አይተውም ማለት ይመስለኛል። ያው ቢሞትም ቆዳው የጅብ ነዋ። ይህን ምሳሌ ያስታወሰኝ የሰሞኑ የአምስት የዖሮሞ ድርጅቶች ያወጡት ጠብ ያለሽ በዳቦ አይነት መግለጫ ነው። በእርግጥ የኢትዮጵያ የፖለቲካ ድርጅቶች አይነተኛ ተግባር ምናልባትም ቋሚ ስራ መግለጫ ማውጣት ስለሆነ ድርጅቶቹ ያው እንደለመደው ሰብሰብ ብለው እስቲ መግለጫ እናውጣ ቢሉ ያባት ይባል ነበር። የነዚህኞቹ ግን የዘር አዋጅ እንጂ መግለጫ የሚባል ስላልሆነ በእውነቱ በጥብቅ የሚያነጋግርም የሚያስተዛዝብም ምናልባትም ደግሞ ህግ ካለም በህግ የሚያስጠይቅ ግዴለም አቅልለን እንመልከተው ካልን ደግሞ … [Read more...] about የጠብ ሱስ
የክልሎች የመሬት ቅርምት እና ትውልድ አምካኝ የትምህርት ፓሊሲ
1) መነሻ እውነታዎች፤ በዚህ ቋንቋን መሰረት ባደረ የጎሳ ፌዴራል ስርዓት፦ (ሀ) ጊዜ ያነሳቸው ባለጉልበቶች በጎሳና በቋንቋ ተቧድነው የኢትዮጵያን ህዝብ የጋራ መሬትና የተፈጥሮ ሃብትን ኢፍትሃዊ በሆነ መንገድ አግበስብሰው በመያዝ ከዚህ መስመር አትለፍ፣ ይህ የኔ ክልል ነው አንተን አይመለከትህም፣ መጤዎች ከክልላችንን ለቃችሁ ውጡ፣ መሬቱን እንፈልገዋለን ወደ ሃገራችሁ ሂዱ እያሉ የሃገሪቷን ዜጎች ተወልደው ካደጉበት፣ አድገው ከተዳሩበት፣ ወልደው ከከበዱበት ከሃገራቸው ላይ እንደ ዋዛ ቤተስብ በሚያፈርሱበትና በሚያፈናቅሉበት፣ በተለይም አንዱ የሃገር ባለቤትና አፈናቃይ ሌላው በሃገሩ ላይ ባዳና ሁለተኛ ዜጋ በሆነበት ሁኔታ፣ (ለ) ጥቂቶች የሃገርን ሃብትን ዘርፈውና የንፁሃንን ደም አፍሰው፣ በየእስር ቤቱ ዜጎችን ቶርቸር እያደረጉና እያሰቃዩ ከህግ በላይ ሆነው ሰውንም እግዚአብሔርን … [Read more...] about የክልሎች የመሬት ቅርምት እና ትውልድ አምካኝ የትምህርት ፓሊሲ
“በመንግስት አመራር ውስጥ ‘እኔ አውቅላችኋለሁ’ የሚል ደዌ ተጠናውቶን ቆይቷል” አቶ ገዱ አንዳርጋቸው
ገዱ አንዳርጋቸው በምሁራን መድረክ ያድረጉት የመክፈቻ ንግግር ክቡር አቶ ደመቀ መኮንን የኢፌድሪ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር የተከበራችሁ ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች! እንኳን ወደ አማራ ክልል መዲና ውቢቷ ባህርዳር ከተማ በሠላም መጣችሁ! ከነገሬ ሁሉ በማስቀደም የአማራ ክልል መንግስት እና ህዝብ የጐደለውን ትሞሉለት ዘንድ ምክራችሁን እና የሙያ ድጋፋችሁን በመሻት ለልጆቹ ያደረገውን ይህን ታሪካዊ ጥሪ ያለምንም ማቅማማት ተቀብላችሁ እዚህ በመካከላችን በመገኘታችሁ ከልብ የመነጨ ምስጋና አቀርባለሁ። በረጅሙ የሃገራችን ኢትዮጵያ ታሪክ ውስጥ የአማራ ህዝብ በስልጣኔ፣ በተለይም በመንግስት አስተዳደር፣ በታሪክ፣ በኪነ-ጥበብ፣ በስነ-ፅሁፍ፣ በአርበኝነት ተጋድሎ እንዲሁም በኢኮኖሚ ዕድገት ለሃገር ያበረከተው ድርሻ ትልቅና አይረሴ ቢሆንም ያለፈው ግማሽ ምዕተ-ዓመት … [Read more...] about “በመንግስት አመራር ውስጥ ‘እኔ አውቅላችኋለሁ’ የሚል ደዌ ተጠናውቶን ቆይቷል” አቶ ገዱ አንዳርጋቸው
Abiy lamented about the country’s lack of project management competency in his first press release
I've not yet watched the Press Release (PR) Abiy gave this morning. However, I was given a short clip taken from the PR where he was talking about why mega projects are failing in Ethiopia. He is right on the money. He pinpointed the culprit - the country's lack of capacity to implement the principles of Project Management. This is not the first time he was lamenting about it. A couple of months ago, I remember Abiy talking to the business community where he emphasized the need to build the … [Read more...] about Abiy lamented about the country’s lack of project management competency in his first press release
አብርሃ ደስታ ስለ ህወሓቶች፤ “አሳልፈን አንሰጣቸውም”
"አብርሃ ደስታ ሆይ!" ጃዋር በኦነግ የፊደል መማርያ ማደጉን እና አንተም በወያኔ የጥላቻ መማርያ ደብተር ማደግህን ለዛሬ የተበረዘ አስተሳሰባችሁ አስተዋጽኦ ቦኖረውም (ለዛወም ይሆናል “ኢትዮጵያ አውት ኦፍ ኦሮሚያ” ብሎ ጃዋር ሲል ፖለቲካው ይመቸኛል ያልከው) ትንሽ ስታድግ አክራሪ ብሔረተኛነትክን ትንሽም ቢሆን ማሻሻል ነበረብህ። ሆኖም ፈቀቅ አላልክም። አፈር በል! በፖለቲካው እየሸበትክ ስትመጣ “ሰከን ስትል” የኋለ ኋላ የምትናገራቸው ነገሮች መልሰው ይከነክኑሃል። አብርሃ ደስታ ዞሮ ዞሮ የወያኔ ጀሌ ነው እያልን ስንናገር፤ ብዙ ሰዎች አላመኑም ነበር። ጀሌ ማለት የግድ አባል መሆን ማለት አይደለም። ድሮ የተከናነበበትን ማጃጃያ ነጠላውን ጥሎ ዛሬ በግልጽ ስለወያኔዎች ወንጀለኞች ጥብቅና ቆሞ እየተከራከረ ነው። ድሮም ዛሬም ከወያኔ የተደመረ እንጂ ከወያኔ የተለየ ሰው አልነበረም … [Read more...] about አብርሃ ደስታ ስለ ህወሓቶች፤ “አሳልፈን አንሰጣቸውም”










