• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“በመንግስት አመራር ውስጥ ‘እኔ አውቅላችኋለሁ’ የሚል ደዌ ተጠናውቶን ቆይቷል” አቶ ገዱ አንዳርጋቸው

August 26, 2018 10:51 am by Editor Leave a Comment

ገዱ አንዳርጋቸው በምሁራን መድረክ ያድረጉት የመክፈቻ ንግግር

  • ክቡር አቶ ደመቀ መኮንን የኢፌድሪ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር
  • የተከበራችሁ ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች!

እንኳን ወደ አማራ ክልል መዲና ውቢቷ ባህርዳር ከተማ በሠላም መጣችሁ!

ከነገሬ ሁሉ በማስቀደም የአማራ ክልል መንግስት እና ህዝብ የጐደለውን ትሞሉለት ዘንድ ምክራችሁን እና የሙያ ድጋፋችሁን በመሻት ለልጆቹ ያደረገውን ይህን ታሪካዊ ጥሪ ያለምንም ማቅማማት ተቀብላችሁ እዚህ በመካከላችን በመገኘታችሁ ከልብ የመነጨ ምስጋና አቀርባለሁ።

በረጅሙ የሃገራችን ኢትዮጵያ ታሪክ ውስጥ የአማራ ህዝብ በስልጣኔ፣ በተለይም በመንግስት አስተዳደር፣ በታሪክ፣ በኪነ-ጥበብ፣ በስነ-ፅሁፍ፣ በአርበኝነት ተጋድሎ እንዲሁም በኢኮኖሚ ዕድገት ለሃገር ያበረከተው ድርሻ ትልቅና አይረሴ ቢሆንም ያለፈው ግማሽ ምዕተ-ዓመት በዘመናዊ ትምህርት የጐለመሰው የክልሉ ተወላጅ ቁጥሩ ከፍ እያለ የመገኘቱን ያክል ተሣትፎው ግን እየቀዘቀዘ መጥቷል።

ለዚህ ዋነኛ ምክንያቱ አሳታፊ /አካታች/ የመንግስት አስተዳደር አለመኖሩና በመንግስት አመራር ውስጥ “እኔ አውቅላችኋለሁ” የሚል ደዌ ተጠናውቶን መቆየቱ ነው። ይህ ጉዳይ በሁሉም የሙያ ዘርፍ አንቱ የሚባሉና ለሃገራችንም ሆነ ለዓለም የተረፉ ምርጥ ምሁራን ለፈለቁበት የአማራ ህዝብ “የዐባይን እናት ውሃ ጠማት” እንደሚሉት አይነት ሆኖበት ቆይቷል። በመመካከር ፈንታ መወቃቀስ፣ በመደጋገፍ ፈንታ መገፈታተር፣ በፍቅር አብሮ መሥራት እና አብሮ መብላት የአባት አደር ሆኖ ሳለ የአንድነትና ወንድማማችነት ጽዩፋን እየሆን እንገኛለን።

ለዚህ ሁሉ ችግር ተወቃሽ ባይጠፋም ወቃሽ ሆኖ መቅረብ የሚችለው ግን ትልቁ የአማራ ህዝብ ብቻ በመሆኑና የህዝባችን ዐቢይ ፍላጐትም ሁላችንም የምንችለውን ያክል ሠርተን ከችግር እንድናወጣው ሥለሆነ ዛሬ በመካከላችሁ የቆምኩት ይህንኑ ጥሪ ለማሥተላለፍ ብቻ ነው።

ወንድሞች እና እህቶች !!

መማር ማለት በርካታ መፃህፍትን ውጦ መቀመጥ ብቻ አይደለም። እንደ እውነቱ ከሆነ መማር በዩኒቨርሲቲ በሚሰጥ የሊቅነት ማረጋገጫ ወረቀት ብቻ ሊገለጥ አይችልም። በእኔ እምነት መማር የህዝብን ህመም አብሮ ታሞ መፈወስ መቻል ነው።

ትምህርት የተጨነቀን ህዝብ ከችግር ለማውጣት የሚያስችል መሣሪያ ሆኖ ካልተገኘ ልሂቃን ሲፈልጉት ብቻ የሚጠቀሙበት ተከቶ የተቀመጠ ትርፍ ሃብት ይሆናል። የክልላችን ህዝብም ይሁን ሃገራችን ዘመናትን ያስቆጠሩ በርከት ያሉ ችግሮች አሉባቸው። ችግሮቹን መንግስት ብቻውን ታግሎ ሊፈታቸው እንደማይችል አሣምረን ተረድተናል። ዛሬ የሁላችሁንም በር ለማንኳኳት ስንወስን ሃገር በዕውቀት እንጂ በልበ ብርሃንነት እንደማይመራ ተገንዝበን ነው። ሃገር በመገንባት ሂደት ውስጥ ህዝብ፣ መንግስት እና ባለሃብቶች ትልቅ ድርሻ አላቸው። ይሁን እንጂ ሁሉም በዕውቀትና በጥበብ ካልተሳሰሩና ካልተደጋገፋ ወንዝ መሻገር አይችሉም።

ምሁራን ያለችውን እውቀት ወደ ተጨባጭ ጠቀሜታ መቀየር የሚችሉት ብቻቸውን በመጓዝ አይደለም። ከመንግስት ጋር አብሮ መሥራትም ፖለቲከኛነት አይደለም። ይልቁንም ዕውቀትን ወደ ህዝብ ለማድረስ ዋነኛ ድልድይ ከሆነው አካል ጋር አብሮ መስራት ነው። የፖለቲካ ሣይንስ ምሁራን እንደሚናገሩትም የአንፃራዊነት ጉዳይ ካልሆነ በስተቀር ከፖለቲካ ፈፅሞ ነፃ የሆነ ሰው የለም።

ስለሆነም ተገቢነት የሌለውን የፖለቲካ ሃሜት በመፍራት ወይም ይህንኑ ሰበብ በማድረግ መራራቅ ለማናችንም አይበጀንም። ተራርቀን አይተነዋል፤ ዘመን ተሻጋሪ የልማት ገድል መፈፀም የሚያስችል እውቀትና ችሎታ እያለን “የጋን መብራት” ከመባል አላለፍንም። መለያየት፣ ፊት መዟዟር፣ በአለፈው ታሪካችን መወቃቀስም ሆነ የይስሙላ መቀራረብ ይብቃን።

የአማራ ህዝብ ችግር የሚፈታው ከልብ የመነጨ ፍቅር፣ አንድነት፣ እውነተኛ እህትማማችነትና ወንድማማችነት በመካከላችን ሲገነባ ነው። አማራ ክልል ፀጋው ያልተጓደለበት፣ ሁሉም ዘርፍ እንስራ ብንል ልማትን ለማምጣትና ህዝቡን ተጠቃሚ ለማድረግ ወሳኝ የሚባል የሃብት መሠረት ያለው ክልል ነው። በእስካሁኑ ጉዟችን በገባን ልክ ህዝቡን ከድህነት ለማላቀቅ ያቅማችንን ተፍጨርጭረናል። ያም ሆኖ ያስመዘገብነው ውጤት ህዝባችን ሙሉ በሙሉ ከችግር ያላቀቀ አይደለም። የምናደርገው ሩጫ ብልሃት ቢጨመርበት፣ በዕውቀት ቢደገፍ ድህነት ከክልላችንና ከሃገራችን የሚቆይበት እድሜ በብዙ እጥፍ ሊያጥር ይቻል እንደነበር አሣምረን እንገነዘባለን።

የምናደርግላችሁ ጥሪ የይስሙላ አይደለም፣ ታሪካዊ ግዴታችሁ የሆነውን ይህን የአብረን እንስራ የጥሪ ደወል ሠምታችሁ በአንድነት በመሠባሰብና በተግባር አብሮ ለመራመድ ለቆረጣችሁ ምንጊዜም ከጐናችሁ በመሆን ለዚህ ተግባር የሚያስፈልገውን የመንግስት አገልግሎት በቀናነት ለመስጠት ዝግጁ ነን። ይህ አጋጣሚ ለእናንተ ግዴታ አይደለም። ይልቁንም ለረጅም ጊዜ ስትመኙት የነበረ ዕድል እንደሆነ አውቃለሁ። ዕድሉን መስጠት እና ሁኔታውን ማመቻቸት የመንግስት ድርሻ ቢሆንም መጠቀም ግን የእናንተ ብቻ ነው። ለመተባበርም ታሪክ ለመቀየርም እኔና እናንተ ከማንም አናንስም። ሳናጣ የጐደለብን፣ ሣይነጥፍ የደረቀብን፣ እያለን እንደሌለን የምንቆጠር ደካሞች አይደለንም።

እኛ የጠፋውን የማልማት፣ የጐበጠውን የማቃናት፣ የተቋጠረውን የመፍታት፣ የተወሳሰበውን መልክ የማስያዝ ብቃትና ተሠጥኦ ያለን ልዩ ልጆች ነን። አንድ ሆነን በመስራት ከእኛ አልፈን ለሃገርም የሚበቃ ትሩፋት መፍጠር እንችላለን። እነሆ መንገዱ ተከፍቷል፣ የጥላቻ መጋረጃውም ተቀዷልና በመሃሉ በመመላለስ ቤታችንን ቤት እናድርገው።

በድጋሜ አክብራችሁን ስለተገኛችሁ እያመሰገንኩ በዚህ አጋጣሚ ይህ ታሪካዊ የምሁራን መማክርት ጉባዔ እንዲቋቋም ምሁራን ለክልሉ ህዝብ ዕድገት የቻሉትን ሁሉ እንዲሰሩ በሚያዚያ ወር በዚሁ በባህር ዳር ከተማ ተገናኝተው ታሪካዊ መሠረት ድንጋይ ያስቀመጡ ምሁራንና በዚሁ ጉባዔ በተላለፈው ውሣኔ መሠረት የመማክርት ጉባዔ ለማዘጋጀት አስፈላጊ የሆኑ መነሻ ጽሁፍ ረቂቅ መተዳደሪያ ደንብ እና ፍኖተ ካርታ በማዘጋጀት ትክክለኛ የሆነውን የምሁራን ትጋት በአሣዩን እና የአንድነት ተምሣሌት በመሆን ሌት ተቀን ለሰሩ የኮሚቴ አባላት ያለኝን ምስጋና ለማቅረብ ቃላት የለኝም። በተጨማሪም ከዚህ መማክርት ጉባኤ መክፈቻ ቀን ቀደም ብሎ በሙያቸው በመደራጀት የክልሉን የግብርና ልማት ዘርፍ ለማገዝ ሥራ ለጀመሩ የግብርና ባለሙያዎች እና ተመራማሪዎች ላሳዩት ቁርጠኝነት ከልብ የመነጨ ምስጋና አቀርባለሁ።

አመሰግናለሁ!!!
ምንጭ፦ የአቶ ንጉሱ ጥላሁን ፌስቡክ ገፅ


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ። ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው።

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: andm, gedu, Left Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ሤራ አክሻፊው ጎንደር ለሦስተኛ ጊዜ ታሪክ ሠራ May 10, 2023 09:25 am
  • ማር በከፍተኛ ደረጃ የኮንትሮባንድ ሰለባ ሆኗል May 9, 2023 09:24 am
  • ኦነግ በኦሮሚያ ሪፈረንደም እንዲካሄድ መጠየቁ ለሰላም ንግግሩ ዕንቅፋት ሆነ May 4, 2023 01:12 am
  • መረጃ ቲቪ ያጋራው አሳሳች መረጃ May 2, 2023 12:37 pm
  • “ከፈጣሪ በታች መከላከያ የሁላችን ዋስ ጠበቃ ነው፤ ትልቅ ይቅርታ እንጠይቃለን” April 13, 2023 10:19 am
  • በትግራይ የ”ልጆቻችን የት ናቸው?” ጥያቄ እየተሰማ ነው April 13, 2023 08:56 am
  • በትህነግ የፈረሰው የአክሱም ኤርፖርት ያስከተለው ዘርፈብዙ ኪሣራ April 13, 2023 03:21 am
  • “የከተማው ነዋሪ በመሰላቸቱ ተፈናቃዮች ከፍተኛ የምግብ ችግር” ገጥሟቸዋል April 12, 2023 09:23 am
  • ከዕድሜ ልክ እስከ 20 ዓመት ቅጣት ተበይኖባቸዋል April 11, 2023 02:58 pm
  • የኡጋንዳ የክልሎች ሚኒስትር በቆርቆሮ ሌብነት ተጠርጥረው ታሰሩ April 10, 2023 03:59 pm
  • ታከለ ከተነሳ በኋላ የመዐድን ሌቦች እየተያዙ ነው April 6, 2023 02:53 pm
  • አገር ለማተራመስ ያለመ የምሁራን፣ የሚዲያ ባለቤቶችና አክቲቪስቶች ህቡዕ ቡድን ተያዘ April 4, 2023 10:07 am
  • በ10 ዓመት ውስጥ ከ44 ቢሊየን ዶላር በላይ ሸሽቷል April 4, 2023 09:26 am
  • አየር ጨብጦ አሁን ያለውን መንግሥት ከሥልጣን ልቀቁ አይሆንም March 29, 2023 09:47 am
  • ሦስት ትውልድ የበላ የሐሰት ትርክት! March 23, 2023 11:59 am
  • “ሽብርተኝነቱን ማንሳቱ በትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ለማቋቋም ይረዳል” – ዶ/ር ጌዲዮን March 22, 2023 05:05 pm
  • አስነዋሪ ተግባር ሲፈጸምባቸው የነበሩ የምሽት ክለቦች ተዘጉ March 22, 2023 12:57 pm
  • ህወሓትን ከሽብርተኝነት እንዲሰረዝ የወሰናችሁ ሁሉ ተጠያቂዎች ናችሁ – ኢዜማ March 22, 2023 12:06 pm
  • የኡጋንዳ ፓርላማ የተመሳሳይ ጾታ ግንኙነትን በእስር የሚያስቀጣ ወንጀል የሚያደርግ ረቂቅ ሕግ አጸደቀ March 22, 2023 12:44 am
  • በጌታቸው ምርጫ ማግስት በትግራይ ሕዝባዊ ዐመፅ ተጀመረ March 21, 2023 11:01 pm
  • በትግራይ ሥልጣንና ንጉሥ ፈጣሪነት ከአድዋ ወደ ራያ ተሻገረ March 19, 2023 03:45 am
  • ኤርሚያስ ከጌታቸው ረዳ ጋር ምሥጢራዊ የስልክ ግንኙነት ነበረው March 19, 2023 02:44 am
  • እየተገባደደ ያለው የምስራቅ አፍሪቃ የትራንስፖርት ኮሪደርና ለውጥ የናፈቃት ኤርትራ March 15, 2023 04:44 pm
  • በባዶ እግር በሮም አበበን ለመድገም March 15, 2023 01:40 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule