• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የጠብ ሱስ

September 29, 2018 12:51 pm by Editor Leave a Comment

ከጅብ ከበሮ የተሰራ አታሞ ዘወትር እንብላው፤ እንብላው ይላል የሚል ተረት ሰምቻለሁ ልበል? አዎ፤ ሳልሰማ አልቀርም። ሀሳቡም ግን ጅብ ቆዳ ሆኖ እንኳን (ቆዳ ሆኖ ብቻ አይደለም አታሞ ተለጉሞበትም) ያው የተፈጥሮ እንብላ ባይ ባህሪውን አይተውም ማለት ይመስለኛል። ያው ቢሞትም ቆዳው የጅብ ነዋ።

ይህን ምሳሌ ያስታወሰኝ የሰሞኑ የአምስት የዖሮሞ ድርጅቶች ያወጡት ጠብ ያለሽ በዳቦ አይነት መግለጫ ነው። በእርግጥ የኢትዮጵያ የፖለቲካ ድርጅቶች አይነተኛ ተግባር ምናልባትም ቋሚ ስራ መግለጫ ማውጣት ስለሆነ ድርጅቶቹ ያው እንደለመደው ሰብሰብ ብለው እስቲ መግለጫ እናውጣ ቢሉ ያባት ይባል ነበር። የነዚህኞቹ ግን የዘር አዋጅ እንጂ መግለጫ የሚባል ስላልሆነ በእውነቱ በጥብቅ የሚያነጋግርም የሚያስተዛዝብም ምናልባትም ደግሞ ህግ ካለም በህግ የሚያስጠይቅ ግዴለም አቅልለን እንመልከተው ካልን ደግሞ ታላቅ የፖለቲካ ነውር ነው።

በዳይ ተበዳይ፣ ገዳይ አጋዳይ፣ አጥፊ ጨፍጫፊ ሳንል ሁሉን ይቅር ለግዜር ብለን በፍቅር አዲስ መንገድ እንጀምር፤ አርባጉጉ በደኖ፣ ጉዳፈርዳ ጨለንቆ ሳንል ያለፈውን ጠባሳ ለታሪክ አበሳ ወደ  ኋላ ጥለን ባዲስ መንፈስ የጋራ ሀገራችንን እንገንባ በምንባባልበት በዚህ መልካም ጊዜ ይህን የመሰለ የጠብ ድግስ ማሰናዳት ምን ይሉታል። የዖሮሞ ህዝብ ከሌሎች ወገኖቹ ጋር ሆኖ የጠብና ጥላቻ ታሪክን በመለወጥ ጣና ኬኛ ኢትዮጵያ ኬኛ እያለ የሰላምና የፍቅር ዜማ ሲያዜም የነዚህ ዖሮሞ ድርጅቶች ሰይፍ አንሱ እንጫረስ ጥሪ የጤና ነው። ትላላችሁ? ገና ሩጠው ያልጠገቡ ለጋ የዖሮሞ፤ ያማራና ሌሎችም ዜጎች የረገፉትስ ለዚህ ነበር? የነዚህ ቀንበጥ ወጣቶች ደም ሳይደርቅስ አዲስ እልቂት መሻት ከእድሜ ጠገብ የዖሮሞ ፖለቲከኞች የምንጠብቀው ነው?

እርግጥ መግለጫውን (ምን መግለጫ የጦርነት አዋጅ ልበለው እንጂ) ለማውጣት በአዲስ አበባ ከተሰበሰቡት የዖሮሞ ድርጅቶች ከጥቂት ግለሰቦች በቀር ብዙዎቹ ለእልቂትና ግጭት አዲስ አይደሉም። በዖሮሞ ህዝብ ስም ብዙ የሰሩ ናቸው። እናም ጭር ሲል አልወድም ቢሉ ላይገርም ይችላል። ግን የዖሮሞ ህዝብ ከወንድሞቹ ጋር ደም ቢፋሰስ ምን ይጠቀማሉ? የዚህ ደግ ህዝብ የመከራ ዘመንስ ቢያበቃ ምን ይጎዳሉ? ብሎ መጠየቅ ያስፈልጋል።

ፍቅር፣ መቻቻልና ሰላም ከምንጊዜውም በላይ እጅግ አስፈላጊ በሆነበት በዚህ ወቅት ወደኋላ ሄዶ የቂም ድሪቶ መጎተት አያስፈልግም እንጂ ይህንን መርዘኛ መግለጫ ካወጣው ስብስብ መሃከል እኮ አያሌ ኢትዮጵያውያንን በዘር ለይቶ የጨፈጨፉና ያስጨፈጨፉ  ግፈኞች አይኖሩም ብላችሁ ነው? እነዚህ ሰዎች ደም ካላዩ ህልውና የላቸውም። የዖሮሞ ህዝብ ከሌላው ወገኑ ጋር ሰላም የሆነ ቀን አይናቸው ደም ይለብሳል። የህልውናቸ ፍፃሜ የደረሰ ያህል እረፍት ያጣሉ። ለነርሱ የህዝብ ግችት የህልውና ዋስትናቸው ነው። እንዲያ ባይሆን ኖሮ እዚህም እዚያም በሰበብ ባስባቡ የንፁሃን ደም በሚፈስበት በዚህ ወቅት፣ ህዝብ በፍቅርና ሰላም እንዲቀራረብ በሚለፋበት በዚህ ወቅት፣ እርስ በእርስ በመጠፋፋት ሀገር እንዳይጠፋ ጀግኖች የዖሮሞ ልጆች እየወደቁ እየተነሱ ባሉበት በዚህ ፈታኝ ጊዜ፣ የጦርነት አዋጅ የሚመስል መግለጫ ተብዬ የነገር ፍለጋ ሀተታ መፃፍ ያስፈልግ ነበር? በባህሪያቸው በኢትዮጵያውያን የእርስ በርስ ግችት ሲያተርፉ የኖሩና የኢትዮጵያ ህዝብ ሰላም የሚያከስራቸው ቡድኖች ባይሆኑ ኖሮ በሰላም ጊዜ ብቻ በጥሞና ክርክርና ውይይት መቀመጥ ያለባቸውን ስሜት የሚያስቆጡ ኮርኳሪ አጀንዳዎችን መጎተት ያስፈልግ ነበር። እነዚህ ቡድኖች በእርግጥ ለዖሮሞ ህዝብ ሰላምና ከሌሎች ወገኖቹ ጋር በፍቅር እንዲኖር የሚመኙ ቢሆኑ ኖሮ በዚህ ደግ ህዝብ ላይ ሌላው ወገን ጥርጣሪ የሚችር ተንኳሽ እና መርዘኛ ፕሮፓጋንዳ መዝራት ይገባ ነበር?

እነዚህ ሰዎች የደም ሰዎች ባይሆኑ ኖሮ ያላበሳቸው ለተቸፈቸፉ ህጻናት፣ ክብራቸው በገዛ ቀያቸውና ብታቸው ለተደፈሩ ለታረዱ ኢትዮጵያውያን ወገኖቻቸው አንዲት የሀዘን መግለጫ የምትሆን የሰባዊነት ማሳያ ቅንጣት ቃል ሊተነፍሱ እንዴት ህሊናቸው ያምፅባቸው ነበር? እናም ከጅብ ቆዳ የተሰራው ከበሮ እንብላው እንብላው እንደሚል ሁሉ በደም ታሪክ የተሰሩ ቡድኖችም ዛሬም ደም ደም ቢሉ ያሳዝን ይሆናል እንጂ አይገርምም።

እነዚህ ቡድኖችና ከነሚድያቸው ለጦርነት አዋጅ አዲስ አበባ የገቡ መሰል ድርጅቶች ከለከፋቸው የህዝብ ደም ሱስ ሌላ ይህን ህዝብ የሚያቃቅር ክፉ መግለጫ በዚህ ወቅት እንዲያወጡ የገፋቸው ተጨማሪ ምክንያት ሳይኖራቸው አይቀርም።

ይህም የዖሮሞን ህዝብ ጨምሮ የኢትዮጵያውያንን ሁሉ ልብ የማረከው የነዶክተር አቢይና ለማ መገርሳ የፍቅርና የሰላም ጥሪ ያሳደረባቸው ስልጣን የማጣት ጉጉት ነው። የነዚህ ጀግና የዖሮሞ የለውጥ ሀይሎች ከልሎች ወንድሞቻቸው ጋር ሆነው ያሳዩት ተጋድሎ ያስገኘላቸው የህዝብ ድጋፍ ለነዚህ የድል አጥቢያ አርበኛ የዖሮሞ ድርጅቶች የስልጣን እርካብ ሊያደርጉት ያቀዱትን የዖሮሞ ህዝብ ድጋፍ የሚያሳጣቸው ስለመሰላቸው በፍርሃት ተንጠዋል። በመሆኑም በፍቅር ያልማረኩትን የዖሮሞ ህዝብ የጠብ ጎራ ፈጥረው ከጎናቸው እንዲሰለፍ ለማድረግ የጥላቻ መርዝ ከመቀመም የተሻለ መንገድ ይፈልጉ ዘንድ ተፈጥሯቸው አልፈቀደላቸውም። እናም ከዖሮሞ ህዝብ የተገኙ የለውጥ መሪዎቹን ያለጥርጣሬ ሆ ብሎ የደገፈውን ኢትዮጵያዊ እነሆ ዖሮሞን ሊያጠፋ ተነሳ ሲሉ አሟረቱ። እግዚአብሄር ይቅር ይበላቸው።

ቸር ያሰማን ጃል

zobar2006@gmail.com


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ። ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው።

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ከፍተኛ የፋኖ አመራሮች መገደላቸው ተነገረ May 6, 2025 10:40 pm
  • ሃይማኖትን ለተራ የፖለቲካ ሸቀጥ ማዋል ውርደት ነው April 24, 2025 12:43 am
  •  የኬሪያ ኢብራሒም ኑዛዜ “ብትንትናችን ወጥቷል” April 22, 2025 12:08 am
  • ለወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን አመራሮች ወታደራዊ ሥልጠና ተሰጠ April 16, 2025 11:44 pm
  • ዓቅም እንደሌለው የገመገመው ሻዕቢያ ፊቱን ከጦርነት ወደ ዲፕሎማሲ እያዞረ ነው   April 15, 2025 12:32 am
  • “አንድ የፋኖ ተቋም (የእስክንድር) ተመሥርቷል፤ ሌሎቹ ደግሞ እንዲሁ አንድ ተቋም መሥርተው ወደዚህ ይመጡ” አበበ ጢሞ April 11, 2025 12:07 am
  • መለስ (ለገሰ) ዜናዊ – ተዋርዶ ያዋረደን! April 9, 2025 10:28 pm
  • የተከዜ ዘብ: የሉዓላዊነት መጠበቂያ April 8, 2025 11:49 pm
  • አዲስ አበባ አስተዳደር የሪፖርተርን የተዛባ መረጃ ኮነነ፤ ሕጋዊ እርምጃ እወስዳለሁ አለ April 8, 2025 10:06 pm
  • ሀሰተኛውን የሪፖርተር ዘገባ ንግድ ባንክ በጽኑ ተቃወመ፤ እርማትም ጠየቀ April 8, 2025 09:48 pm
  • “ኦሮሚያ ላይ ወይም ሌላ ቦታ ላይ ስታደርገው ከነበረ ትግራይ ወስጥም የማታደርግበት ምንም ምክንያት አይኖርህም” ነው ጌታቸው ረዳ April 7, 2025 10:22 pm
  • “TPLF’s belief in a strong federal government was always tied to its own dominance in Addis Ababa” April 7, 2025 10:15 pm
  • Counter-Video by EBC Challenges EBS Broadcast, Sparks Public Outcry Over Alleged Misinformation March 31, 2025 02:36 am
  • የኤሊያስ መሠረትን ፌክ መረጃ ማን ያጋልጥ? February 19, 2025 06:00 pm
  • አዘርባጃን፡ የሻዕቢያን ሸምቀቆ ማጥበቂያ?! February 19, 2025 12:29 am
  • የአሜሪካ ድምፅ/ቪኦኤ ይዘጋ ተባለ  February 12, 2025 03:37 am
  • የብልፅግና ፓርቲ ሹመኛ ካድሬዎች February 3, 2025 11:07 am
  • ትግሉን የጎዳው የእስክንድር ነጋ አካሄድ February 3, 2025 10:29 am
  • ኤሊያስ መሠረት “ጭምብሉ ዛሬ ወለቀ”፤ ተከፋይ ነው! February 2, 2025 05:32 pm
  • የፋሲል ግንብ እድሳት እንዴት ተካሄደ? የመንጣቱ ምክንያት? January 23, 2025 03:41 pm
  • ታሪካዊዉ የፋሲል ቤተመንግሥት ለምን ነጣ? January 23, 2025 03:04 pm
  • የኢትዮጵያ አየር መንገድ በተወልደ አስተዳደር ዘመን ለተሠራ ስህተት 425ሺ ዶላር ተቀጣ December 14, 2024 01:44 am
  • በትግራይ ከሞትና ከአካላዊ ጉዳት የተረፉት ለስደት ተዳርገዋል November 27, 2024 12:09 pm
  • የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት አሠራሩን እንዲያርም ጥብቅ መመሪያ ተሰጠው November 27, 2024 11:31 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule