• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የጠብ ሱስ

September 29, 2018 12:51 pm by Editor Leave a Comment

ከጅብ ከበሮ የተሰራ አታሞ ዘወትር እንብላው፤ እንብላው ይላል የሚል ተረት ሰምቻለሁ ልበል? አዎ፤ ሳልሰማ አልቀርም። ሀሳቡም ግን ጅብ ቆዳ ሆኖ እንኳን (ቆዳ ሆኖ ብቻ አይደለም አታሞ ተለጉሞበትም) ያው የተፈጥሮ እንብላ ባይ ባህሪውን አይተውም ማለት ይመስለኛል። ያው ቢሞትም ቆዳው የጅብ ነዋ።

ይህን ምሳሌ ያስታወሰኝ የሰሞኑ የአምስት የዖሮሞ ድርጅቶች ያወጡት ጠብ ያለሽ በዳቦ አይነት መግለጫ ነው። በእርግጥ የኢትዮጵያ የፖለቲካ ድርጅቶች አይነተኛ ተግባር ምናልባትም ቋሚ ስራ መግለጫ ማውጣት ስለሆነ ድርጅቶቹ ያው እንደለመደው ሰብሰብ ብለው እስቲ መግለጫ እናውጣ ቢሉ ያባት ይባል ነበር። የነዚህኞቹ ግን የዘር አዋጅ እንጂ መግለጫ የሚባል ስላልሆነ በእውነቱ በጥብቅ የሚያነጋግርም የሚያስተዛዝብም ምናልባትም ደግሞ ህግ ካለም በህግ የሚያስጠይቅ ግዴለም አቅልለን እንመልከተው ካልን ደግሞ ታላቅ የፖለቲካ ነውር ነው።

በዳይ ተበዳይ፣ ገዳይ አጋዳይ፣ አጥፊ ጨፍጫፊ ሳንል ሁሉን ይቅር ለግዜር ብለን በፍቅር አዲስ መንገድ እንጀምር፤ አርባጉጉ በደኖ፣ ጉዳፈርዳ ጨለንቆ ሳንል ያለፈውን ጠባሳ ለታሪክ አበሳ ወደ  ኋላ ጥለን ባዲስ መንፈስ የጋራ ሀገራችንን እንገንባ በምንባባልበት በዚህ መልካም ጊዜ ይህን የመሰለ የጠብ ድግስ ማሰናዳት ምን ይሉታል። የዖሮሞ ህዝብ ከሌሎች ወገኖቹ ጋር ሆኖ የጠብና ጥላቻ ታሪክን በመለወጥ ጣና ኬኛ ኢትዮጵያ ኬኛ እያለ የሰላምና የፍቅር ዜማ ሲያዜም የነዚህ ዖሮሞ ድርጅቶች ሰይፍ አንሱ እንጫረስ ጥሪ የጤና ነው። ትላላችሁ? ገና ሩጠው ያልጠገቡ ለጋ የዖሮሞ፤ ያማራና ሌሎችም ዜጎች የረገፉትስ ለዚህ ነበር? የነዚህ ቀንበጥ ወጣቶች ደም ሳይደርቅስ አዲስ እልቂት መሻት ከእድሜ ጠገብ የዖሮሞ ፖለቲከኞች የምንጠብቀው ነው?

እርግጥ መግለጫውን (ምን መግለጫ የጦርነት አዋጅ ልበለው እንጂ) ለማውጣት በአዲስ አበባ ከተሰበሰቡት የዖሮሞ ድርጅቶች ከጥቂት ግለሰቦች በቀር ብዙዎቹ ለእልቂትና ግጭት አዲስ አይደሉም። በዖሮሞ ህዝብ ስም ብዙ የሰሩ ናቸው። እናም ጭር ሲል አልወድም ቢሉ ላይገርም ይችላል። ግን የዖሮሞ ህዝብ ከወንድሞቹ ጋር ደም ቢፋሰስ ምን ይጠቀማሉ? የዚህ ደግ ህዝብ የመከራ ዘመንስ ቢያበቃ ምን ይጎዳሉ? ብሎ መጠየቅ ያስፈልጋል።

ፍቅር፣ መቻቻልና ሰላም ከምንጊዜውም በላይ እጅግ አስፈላጊ በሆነበት በዚህ ወቅት ወደኋላ ሄዶ የቂም ድሪቶ መጎተት አያስፈልግም እንጂ ይህንን መርዘኛ መግለጫ ካወጣው ስብስብ መሃከል እኮ አያሌ ኢትዮጵያውያንን በዘር ለይቶ የጨፈጨፉና ያስጨፈጨፉ  ግፈኞች አይኖሩም ብላችሁ ነው? እነዚህ ሰዎች ደም ካላዩ ህልውና የላቸውም። የዖሮሞ ህዝብ ከሌላው ወገኑ ጋር ሰላም የሆነ ቀን አይናቸው ደም ይለብሳል። የህልውናቸ ፍፃሜ የደረሰ ያህል እረፍት ያጣሉ። ለነርሱ የህዝብ ግችት የህልውና ዋስትናቸው ነው። እንዲያ ባይሆን ኖሮ እዚህም እዚያም በሰበብ ባስባቡ የንፁሃን ደም በሚፈስበት በዚህ ወቅት፣ ህዝብ በፍቅርና ሰላም እንዲቀራረብ በሚለፋበት በዚህ ወቅት፣ እርስ በእርስ በመጠፋፋት ሀገር እንዳይጠፋ ጀግኖች የዖሮሞ ልጆች እየወደቁ እየተነሱ ባሉበት በዚህ ፈታኝ ጊዜ፣ የጦርነት አዋጅ የሚመስል መግለጫ ተብዬ የነገር ፍለጋ ሀተታ መፃፍ ያስፈልግ ነበር? በባህሪያቸው በኢትዮጵያውያን የእርስ በርስ ግችት ሲያተርፉ የኖሩና የኢትዮጵያ ህዝብ ሰላም የሚያከስራቸው ቡድኖች ባይሆኑ ኖሮ በሰላም ጊዜ ብቻ በጥሞና ክርክርና ውይይት መቀመጥ ያለባቸውን ስሜት የሚያስቆጡ ኮርኳሪ አጀንዳዎችን መጎተት ያስፈልግ ነበር። እነዚህ ቡድኖች በእርግጥ ለዖሮሞ ህዝብ ሰላምና ከሌሎች ወገኖቹ ጋር በፍቅር እንዲኖር የሚመኙ ቢሆኑ ኖሮ በዚህ ደግ ህዝብ ላይ ሌላው ወገን ጥርጣሪ የሚችር ተንኳሽ እና መርዘኛ ፕሮፓጋንዳ መዝራት ይገባ ነበር?

እነዚህ ሰዎች የደም ሰዎች ባይሆኑ ኖሮ ያላበሳቸው ለተቸፈቸፉ ህጻናት፣ ክብራቸው በገዛ ቀያቸውና ብታቸው ለተደፈሩ ለታረዱ ኢትዮጵያውያን ወገኖቻቸው አንዲት የሀዘን መግለጫ የምትሆን የሰባዊነት ማሳያ ቅንጣት ቃል ሊተነፍሱ እንዴት ህሊናቸው ያምፅባቸው ነበር? እናም ከጅብ ቆዳ የተሰራው ከበሮ እንብላው እንብላው እንደሚል ሁሉ በደም ታሪክ የተሰሩ ቡድኖችም ዛሬም ደም ደም ቢሉ ያሳዝን ይሆናል እንጂ አይገርምም።

እነዚህ ቡድኖችና ከነሚድያቸው ለጦርነት አዋጅ አዲስ አበባ የገቡ መሰል ድርጅቶች ከለከፋቸው የህዝብ ደም ሱስ ሌላ ይህን ህዝብ የሚያቃቅር ክፉ መግለጫ በዚህ ወቅት እንዲያወጡ የገፋቸው ተጨማሪ ምክንያት ሳይኖራቸው አይቀርም።

ይህም የዖሮሞን ህዝብ ጨምሮ የኢትዮጵያውያንን ሁሉ ልብ የማረከው የነዶክተር አቢይና ለማ መገርሳ የፍቅርና የሰላም ጥሪ ያሳደረባቸው ስልጣን የማጣት ጉጉት ነው። የነዚህ ጀግና የዖሮሞ የለውጥ ሀይሎች ከልሎች ወንድሞቻቸው ጋር ሆነው ያሳዩት ተጋድሎ ያስገኘላቸው የህዝብ ድጋፍ ለነዚህ የድል አጥቢያ አርበኛ የዖሮሞ ድርጅቶች የስልጣን እርካብ ሊያደርጉት ያቀዱትን የዖሮሞ ህዝብ ድጋፍ የሚያሳጣቸው ስለመሰላቸው በፍርሃት ተንጠዋል። በመሆኑም በፍቅር ያልማረኩትን የዖሮሞ ህዝብ የጠብ ጎራ ፈጥረው ከጎናቸው እንዲሰለፍ ለማድረግ የጥላቻ መርዝ ከመቀመም የተሻለ መንገድ ይፈልጉ ዘንድ ተፈጥሯቸው አልፈቀደላቸውም። እናም ከዖሮሞ ህዝብ የተገኙ የለውጥ መሪዎቹን ያለጥርጣሬ ሆ ብሎ የደገፈውን ኢትዮጵያዊ እነሆ ዖሮሞን ሊያጠፋ ተነሳ ሲሉ አሟረቱ። እግዚአብሄር ይቅር ይበላቸው።

ቸር ያሰማን ጃል

zobar2006@gmail.com


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ። ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው።

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule