• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

በሐሰት ውንጀላ ተመራማሪ ተማሪዎች በግፍ ተገደሉ

October 26, 2018 03:34 pm by Editor 4 Comments

ከአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ለዶክትሬት ማጠናቀቂያ ጥናታቸው ወደ ምዕራብ ጎጃም ዞን ጎንጅ ቆለላ ወረዳ ወደ አዲስ አለም ከተማ ተጉዘው የነበሩ ግለሰቦች ላይ በተፈፀመ ጥቃት ሁለቱ ሲገደሉ አንዱ መቁሰሉን የዞኑ የመንግሥት ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ለአሜሪካ ድምፅ ተናገሩ።

አጥኒዎቹ በከተማው ባለው አንድ ትምሕርት ቤት ውስጥ ለምርምር የሚሆን የሽንትና የዐይነ ምድር ናሙና እየሰበሰቡ ባሉበት ወቅት፤ “ሦስት ተማሪዎች ሞቱ” የሚል ወሬ በመሰራጨቱ ተቆጥተው በመጡ የአካባቢው ወጣቶች በደረሰባቸው ከፍተኛ ጥቃት ሕይወታቸው ማለፉን የምዕራብ ጎጃም ዞን የመንግስት ኮሙዩኒኬሽን መምሪያ ኃላፊ አቶ አንማው ዳኛቸው ለአሜሪካ ድምፅ ተናግረዋል።

በተጨማሪም ለቤተ ክርስቲያን ህንፃ ግንባታ ግልጋሎት የሚውል ሲሚንቶ በራሳቸው መኪና ጭነው ወደ አካባቢው ተጉዘው የነበሩ ጥንዶች ንብረትም መቃጠሉ ታውቋል። በዚህ ድርጊት ተሳትፈዋል በሚል የተጠረጠሩም 30 ሰዎች በቁጥጥር ስር መዋላቸውን ተናግረዋል።

በተፈፀመው ድርጊት የአካባቢው ማኅበረሰብም ሆነ መንግሥት ማዘኑን አቶ አንማው ገልፀው በድርጊቱ ተሳትፈዋል የተባሉትን ማሰር መቀጠሉን ጠቁመዋል።

ምንጭ፦የአሜሪካ ድምፅ ሬዲዮ

https://www.goolgule.com/wp-content/uploads/2018/10/4867e13d-1a23-491d-b88b-15cbf4e55614_16k_2.mp3
Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: News Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Comments

  1. Tesfa says

    October 27, 2018 05:17 pm at 5:17 pm

    እባብ ያየ በገመድ ይደነግጣል እንዲሉ የሃገራችን ሰው በራሱ የቀትር ጥላ ዙሪያ መደንበር ከጀመረ ዘመናት ተቆጥረዋል። የዛሬውን መደንበር ከአለፉት ድንባሬዎች ለየት የሚያረገው ደግሞ ሰው የሚከተለው ዘርና ቋንቋ ነክ የክልል ፓለቲካ በመሆኑ ነው። በሆያ ሆየ የሰው ደም የሚፈስባት ይህች ሃገር ባላንጣዋ ብዙ ቢሆንም ይበልጥ ችግሯን የሚያባብሱት በአብራኳ የተፈጠሩ አጥፊ ሃይሎች ናቸው። ብቀላ ብቀላን እየወለደ ስንገዳደል ኖረናል እንኖራለንም። ሰው በዓይኑ ባላየው ነገር ምሥክር የሚቆምባት ሃገራችን በዘር ፓለቲካ የሰከረ የሚራወጥባት ምድር ሆናለች። የሌላውን ሥራ እየኮነነ ራሱ ተመልሶ የኮነነውን ተግባር የሚደግም አረመኔ ብቻ የተጠራቀመባት። ይህን የግፍ ግድያ ከሻሸመኔው ግድያ የሚለየው አንዳች ነገር የለም። የሰው ደም ያፈሰሰ ሁሉ ደሙ ይፈሳል የሚለው የእምነት ትምህርት ችላ ተብሎ ሁሉም በየጎጡ የሚያቅራራበት የውሸት መለከት ነፊዎች የድረሱልኝ ጥሪ የሚያናፍሱበት ይህች ሃገር መቼ ይሆን መከራዋ የሚገታው? ቆይቶ ማየት ነው።

    Reply
    • አብነት says

      November 6, 2018 02:20 am at 2:20 am

      ትክክል በጣም ያሳዝናል እንድ ባልተጣራ ወሬ በስው ነፍስ መፍሪድ መቆም አለበት :: እንዴት ኢትዪጵያዊ ነገ በኔ ኡይገባውም ?? ሁለት የዚህ ባማራ ላይ መድሀኒት ተደርጎ ነበር የሚለው ታሪክ በገለልተኛ እንዲመረመር መደረግ እለበት ለምን ለማጣራት እርምጃ ይወሰድ ተብሎ ለዶር አብይ ጥያቄ ኣልቀረበም ? ከታመነበት :: ዝም ብሎ ማውራት የነዚህ ልጆችን ደም አፈሰሰ :: እናት እኮ አላቸው ቤተሰብ አላቸው :: የሰማነውንነገር የማጣራት ባህል በፍጥነት ማጎላበት ይኖርብናል ለአገራችን ካሰብን ::

      Reply
  2. gi Haile says

    October 27, 2018 06:23 pm at 6:23 pm

    ምን ያድርጉ በጣም ያሳዝናል ይህ ሁሉ በቀደመው 27,አመት ጊዜ ውስጥ በእክምናው ዘርፎች ብዙ እገወጥ ተግባራት ተፈጽመዋል ይባላል። ተሸፋፍኖ የቀረው በክትባት መልክ ብዙ ሴቶች እንዳይወልዱ ተደርጓል የሚል ወሬዎች ይወራሉ መንግሥት ግን ይህንን ጉዳይ ችላ ብሎ መመልከት እና በድብቅ ማቆየቱ ተገቢ አይደለም ።ሕዝብ መልስ ይፈልጋል የቀደሙት የጤና ጥበቃ ምንስቴር ዶር ቴዎድሮስ አዳኖም ለዚህ የሕዝብ ጥያቄዎች መልስ መስጠት ነበረባቸው። አሁንም ለነዚህ ልጆች መሞት ተማሪዎች የማያውቁት ነጠር ግን ሕዝቡ በሆዱ የያዘው ቂም በቀል ነውና። በመጀመሪያ በሕዝብ ጤና ለሠይ ተፈጸመ የተባለው ነገር እውነት ከሆነ መጣራት አለበት ለሕዝብም ይፋ ሊደረግና ተጠያቂነት ሊኖር ይገባል ። እነዚህ ተማሪዎች ግን የሞቱት በማያውቁት ነገር ነውና በጣምም ያሳዝናል። እውነትን በመደበቅ ወገኖቻችን ማጣታችን ግፍ የግፍም ግፈሰ ነዉ ። አይጥ በበለ ዳዋ ተመታ መለት ይህ ነው ።

    Reply
  3. obika says

    November 23, 2018 12:58 pm at 12:58 pm

    Beahunu gize itiyopiya wusxi mannim inde fallage sawun magdal yetelamade new. Injiner simanyew simotuminim altebalem wallagga 70000 sew siffanaqal zim yesumale liyyuhayil tan hullu saw sigedil zim . jamal kashogi siggaddal midire awuropa tenawete. Ine indemimasileny anbessa park wusxi yaallen yimwsilenyal.

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የአየለ ጫሚሶ ቅንጅት ፈረሰ January 18, 2021 02:31 pm
  • ህወሓት ተሠረዘ!!! January 18, 2021 01:32 pm
  • ዓሲምባ፣ ሣልሳዊ ወያኔና ባይቶና ከመፍረሳቸው በፊት ማብራሪያ እንዲሰጡ ተነገራቸው January 18, 2021 01:00 pm
  • ቤተሰቦች አስከሬን መውሰድ እንደሚችሉ ተነገረ January 14, 2021 06:48 pm
  • ስብሃት፤ “ከሞትን ቆይተናል፤ … አሁን የቀብር ሥነ-ስርዓታችን” እየተፈጸመ ነው January 14, 2021 01:37 pm
  • “ተመልሰን እንነሳለን” ያሉት ህወሓቶች ተመልሰው ወደማይነሱበት ተሸኙ January 13, 2021 01:12 pm
  • አፋር ነፃ አውጪ (ኡጉጉሙን) ለመጠቀም የታቀደው የህወሃት ሤራ ከሽፏል January 13, 2021 01:10 pm
  • ህወሃትን ወደ ጅቡቲ ለማሻገር ሲሰሩ የነበሩ የአፋር ታጣቂዎች በሰላም ወደ ክልሉ ገቡ January 13, 2021 06:47 am
  • በታህሳስ ወር ብቻ ከ344 ሚሊየን ብር በላይ የኮንትሮባንድ ዕቃ ተያዘ January 13, 2021 06:10 am
  • የብልፅግና ፓርቲ ቀጣይ ፈተና ምን ሊሆን ይችላል? January 13, 2021 04:10 am
  • ለትምህርት እንዲሆነን January 11, 2021 01:20 pm
  • “ከተቀበሩበት የጃርት ጉድጓድ ነው ያወጣናቸው” መቶ አለቃ ስዩም ቱርቦ January 11, 2021 12:11 pm
  • የተደመሰሱና በቁጥጥር ሥር የዋሉ የወንበዴው አባላት ይፋ ሆነ January 7, 2021 01:16 pm
  • ዐቢይና መኮንኖቹ በመቀሌ፤ “ድሉ የመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ነው” December 13, 2020 02:36 pm
  • ወንበዴው ህወሓት ከ1.4 ትሪሊዮን ብር በላይ ዘርፎ በውጭ አገራት ባንኮች አስቀምጧል December 8, 2020 01:05 am
  • ማይካድራ – የትህነግ የዘር ማጥፋት ጥግ ቋሚ ምስክር December 8, 2020 12:57 am
  • የወልቃይት ጠገዴ እናቶች ሰቆቃ ሲታወስ December 8, 2020 12:50 am
  • የደብረጽዮን ዋሻ December 7, 2020 11:30 pm
  • ባለ ከዘራው ኮሎኔል December 7, 2020 05:15 pm
  • ሰላማዊ ሕይወት በማይጨው December 7, 2020 04:12 pm
  • ተጠርጣሪ የፌዴራልና የአዲስ አበባ ፖሊሶች የመያዣ ትዕዛዝ ወጣባቸው December 7, 2020 11:46 am
  • ከ3 ሺህ በላይ ተተኳሽ ጥይቶች በወልዲያ ጉምሩክ ሊያሳልፉ የሞከሩ 4 ግለሰቦች ተያዙ! December 7, 2020 11:18 am
  • ወንበዴዎቹ ይጠቀሙባቸው የነበሩ ተሽከርካሪዎችና የግል ሰነዶቻቸው ተያዙ December 7, 2020 10:50 am
  • ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ በሶማሌ ክልል ተመሠረተ December 7, 2020 10:31 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2021 · Goolgule