• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

በሐሰት ውንጀላ ተመራማሪ ተማሪዎች በግፍ ተገደሉ

October 26, 2018 03:34 pm by Editor 4 Comments

ከአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ለዶክትሬት ማጠናቀቂያ ጥናታቸው ወደ ምዕራብ ጎጃም ዞን ጎንጅ ቆለላ ወረዳ ወደ አዲስ አለም ከተማ ተጉዘው የነበሩ ግለሰቦች ላይ በተፈፀመ ጥቃት ሁለቱ ሲገደሉ አንዱ መቁሰሉን የዞኑ የመንግሥት ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ለአሜሪካ ድምፅ ተናገሩ።

አጥኒዎቹ በከተማው ባለው አንድ ትምሕርት ቤት ውስጥ ለምርምር የሚሆን የሽንትና የዐይነ ምድር ናሙና እየሰበሰቡ ባሉበት ወቅት፤ “ሦስት ተማሪዎች ሞቱ” የሚል ወሬ በመሰራጨቱ ተቆጥተው በመጡ የአካባቢው ወጣቶች በደረሰባቸው ከፍተኛ ጥቃት ሕይወታቸው ማለፉን የምዕራብ ጎጃም ዞን የመንግስት ኮሙዩኒኬሽን መምሪያ ኃላፊ አቶ አንማው ዳኛቸው ለአሜሪካ ድምፅ ተናግረዋል።

በተጨማሪም ለቤተ ክርስቲያን ህንፃ ግንባታ ግልጋሎት የሚውል ሲሚንቶ በራሳቸው መኪና ጭነው ወደ አካባቢው ተጉዘው የነበሩ ጥንዶች ንብረትም መቃጠሉ ታውቋል። በዚህ ድርጊት ተሳትፈዋል በሚል የተጠረጠሩም 30 ሰዎች በቁጥጥር ስር መዋላቸውን ተናግረዋል።

በተፈፀመው ድርጊት የአካባቢው ማኅበረሰብም ሆነ መንግሥት ማዘኑን አቶ አንማው ገልፀው በድርጊቱ ተሳትፈዋል የተባሉትን ማሰር መቀጠሉን ጠቁመዋል።

ምንጭ፦የአሜሪካ ድምፅ ሬዲዮ

https://www.goolgule.com/wp-content/uploads/2018/10/4867e13d-1a23-491d-b88b-15cbf4e55614_16k_2.mp3
Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Comments

  1. Tesfa says

    October 27, 2018 05:17 pm at 5:17 pm

    እባብ ያየ በገመድ ይደነግጣል እንዲሉ የሃገራችን ሰው በራሱ የቀትር ጥላ ዙሪያ መደንበር ከጀመረ ዘመናት ተቆጥረዋል። የዛሬውን መደንበር ከአለፉት ድንባሬዎች ለየት የሚያረገው ደግሞ ሰው የሚከተለው ዘርና ቋንቋ ነክ የክልል ፓለቲካ በመሆኑ ነው። በሆያ ሆየ የሰው ደም የሚፈስባት ይህች ሃገር ባላንጣዋ ብዙ ቢሆንም ይበልጥ ችግሯን የሚያባብሱት በአብራኳ የተፈጠሩ አጥፊ ሃይሎች ናቸው። ብቀላ ብቀላን እየወለደ ስንገዳደል ኖረናል እንኖራለንም። ሰው በዓይኑ ባላየው ነገር ምሥክር የሚቆምባት ሃገራችን በዘር ፓለቲካ የሰከረ የሚራወጥባት ምድር ሆናለች። የሌላውን ሥራ እየኮነነ ራሱ ተመልሶ የኮነነውን ተግባር የሚደግም አረመኔ ብቻ የተጠራቀመባት። ይህን የግፍ ግድያ ከሻሸመኔው ግድያ የሚለየው አንዳች ነገር የለም። የሰው ደም ያፈሰሰ ሁሉ ደሙ ይፈሳል የሚለው የእምነት ትምህርት ችላ ተብሎ ሁሉም በየጎጡ የሚያቅራራበት የውሸት መለከት ነፊዎች የድረሱልኝ ጥሪ የሚያናፍሱበት ይህች ሃገር መቼ ይሆን መከራዋ የሚገታው? ቆይቶ ማየት ነው።

    Reply
    • አብነት says

      November 6, 2018 02:20 am at 2:20 am

      ትክክል በጣም ያሳዝናል እንድ ባልተጣራ ወሬ በስው ነፍስ መፍሪድ መቆም አለበት :: እንዴት ኢትዪጵያዊ ነገ በኔ ኡይገባውም ?? ሁለት የዚህ ባማራ ላይ መድሀኒት ተደርጎ ነበር የሚለው ታሪክ በገለልተኛ እንዲመረመር መደረግ እለበት ለምን ለማጣራት እርምጃ ይወሰድ ተብሎ ለዶር አብይ ጥያቄ ኣልቀረበም ? ከታመነበት :: ዝም ብሎ ማውራት የነዚህ ልጆችን ደም አፈሰሰ :: እናት እኮ አላቸው ቤተሰብ አላቸው :: የሰማነውንነገር የማጣራት ባህል በፍጥነት ማጎላበት ይኖርብናል ለአገራችን ካሰብን ::

      Reply
  2. gi Haile says

    October 27, 2018 06:23 pm at 6:23 pm

    ምን ያድርጉ በጣም ያሳዝናል ይህ ሁሉ በቀደመው 27,አመት ጊዜ ውስጥ በእክምናው ዘርፎች ብዙ እገወጥ ተግባራት ተፈጽመዋል ይባላል። ተሸፋፍኖ የቀረው በክትባት መልክ ብዙ ሴቶች እንዳይወልዱ ተደርጓል የሚል ወሬዎች ይወራሉ መንግሥት ግን ይህንን ጉዳይ ችላ ብሎ መመልከት እና በድብቅ ማቆየቱ ተገቢ አይደለም ።ሕዝብ መልስ ይፈልጋል የቀደሙት የጤና ጥበቃ ምንስቴር ዶር ቴዎድሮስ አዳኖም ለዚህ የሕዝብ ጥያቄዎች መልስ መስጠት ነበረባቸው። አሁንም ለነዚህ ልጆች መሞት ተማሪዎች የማያውቁት ነጠር ግን ሕዝቡ በሆዱ የያዘው ቂም በቀል ነውና። በመጀመሪያ በሕዝብ ጤና ለሠይ ተፈጸመ የተባለው ነገር እውነት ከሆነ መጣራት አለበት ለሕዝብም ይፋ ሊደረግና ተጠያቂነት ሊኖር ይገባል ። እነዚህ ተማሪዎች ግን የሞቱት በማያውቁት ነገር ነውና በጣምም ያሳዝናል። እውነትን በመደበቅ ወገኖቻችን ማጣታችን ግፍ የግፍም ግፈሰ ነዉ ። አይጥ በበለ ዳዋ ተመታ መለት ይህ ነው ።

    Reply
  3. obika says

    November 23, 2018 12:58 pm at 12:58 pm

    Beahunu gize itiyopiya wusxi mannim inde fallage sawun magdal yetelamade new. Injiner simanyew simotuminim altebalem wallagga 70000 sew siffanaqal zim yesumale liyyuhayil tan hullu saw sigedil zim . jamal kashogi siggaddal midire awuropa tenawete. Ine indemimasileny anbessa park wusxi yaallen yimwsilenyal.

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am
  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm
  • የተመሠረተው የፋኖ አደረጃጀት ዋነኛ ዓላማው ድርድር መሆኑ ተነገረ May 14, 2025 11:07 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule