በድሬደዋ የፀጥታ አካላት በጋራ ባካሄዱት የክትትልና ቁጥጥር ስራ በህገ -ወጥ መንገድ የሚንቀሳቀሱ የሀገርን ጨምሮ የተለያዩ ሀገራት የገንዘብ ኖቶች መያዛቸው ተገለፀ።ገንዘቡ በቁጥጥር ስር የዋለው ትላንት መስከረም 6/2013 ዓ/ም ሲሆን ከህበረተሰቡ በተሰጠ ጥቆማ መሰረት ባደረገ ክትልል መሆኑን ድሬ ፖሊስ አስታውቋል።ከጉዳዩ ጋር ግንኙነት አላቸው ተብለው የተጠረጠሩ 4 ግለሰቦች በቁጥጥር ስር ውለው ጉዳያቸው በህግ መታየት መጀመሩም ተገልፃል።በቁጥጥር ስር ከዋሉት የብር ኖቶች ውስጥ በዋነኝነት፦ ዘጠኝ መቶ አርባ አርት ሺ አንድ መቶ አስር (944,110) የኢትዮጽያ ብርአንድ ሺ ሁለት መቶ ሀምሳ (1250) የአሜሪካን ዶላርአንድ መቶ ስልሳ አምስት (165) የሳውዲ ሪያልሰባት መቶ አርባ አምስት (745) ዩሮ ሲሆኑ ከእነዚህ ጋር አብሮም ከዘጠኝ በላይ የሚሆኑ … [Read more...] about በድሬዳዋ፤ ደቡብ ኦሞና ጌዴኦ ሃሰተኛና ሕገወጥ የብር ኖቶች ተያዙ
Middle Column
በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ከ2.3 ሚሊዮን ብር በላይ ህገ-ወጥ ገንዘብ በቁጥጥር ሥር ዋለ
በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል በህገ-ወጥ መንገድ ሲዘዋወር የነበረ ከ2 ነጥብ 3 ሚሊዮን ብር በላይ በቁጥጥር ስር መዋሉን የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን አስታወቀ፡፡ የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር አብዱልአዚም መሀመድ እንደገለጹት፣ በክልሉ በሚገኙ 4 የተለያዩ ኬላዎች በተደረገ ፍተሻ 2,370,000 ብር በቁጥጥር ሥር ውሏል፡፡ በክልሉ ኩርሙክ ወረዳ ሱዳን ድንበር አካባቢ በግለሰብ ሲዘዋወር የነበረ 600 ሺህ ብር የሚሆን ገንዘብ በቁጥጥር ስር እንደዋለ ተናግረዋል፡፡ ግለሰቡ 600 ሺህ ብር በሞተር ብስክሌት ጭኖ ሲጓዝ የጸጥታ ኃይሎች ባደረጉት ፍተሻ በቁጥጥር ስር መዋሉን አስታውቀዋል። በቁጥጥር ስር የዋለው ተጠርጣሪው ለፖሊስ በሰጠው ቃል ገንዘቡን ለወርቅ ግዥ እያንቀሳቀስኩ ነው ማለቱን ተናግረዋል። በመተከል ዞን ጉባ ወረዳ ማንኩሽ ኬላ 300 ሺህ ብር በቁጥጥር ስር መዋሉን … [Read more...] about በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ከ2.3 ሚሊዮን ብር በላይ ህገ-ወጥ ገንዘብ በቁጥጥር ሥር ዋለ
ወደ ኢትዮጵያ ሊገባ የነበረ 99 ሺህ የሚጠጋ ዶላር ተያዘ
የዛሬ ሳምንት ረቡዕ ወደ አዲስ አበባ ሊጓዝ ከነበረው መንገደኛ ላይ ዋሽንግተን በሚገኘው ደለስ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ በአሜሪካ ጉምሩክና ድንበር ተቆጣጣሪዎች የተያዘው ገንዘብ 99 ሺህ ዶላር የሚጠጋ እንደሆነ ተነግሯል። ቢቢሲ እንዳረጋገጠው ከግለሰቡ ላይ የተያዘው የገንዘብ መጠን 98,762 ዶላር ሲሆን ወደ ኢትዮጵያ ብር ሲመነዘር ከ3.6 ሚሊዮን ብር በላይ ይሆናል። የጉምሩክ መስሪያ ቤቱ የሕዝብ ግንኙነት ሠራተኛ ስቲቭ ሳፕ ለቢቢሲ በሰጡት የጽሁፍ ምላሽ ላይ እንዳመለከቱት፣ ግለሰቡ ይዞት የነበረው ዶላር የተያዘበት ተጓዦች የያዙትን የገንዘብ መጠን እንዲያሳውቁ የሚጠይቀውን የአገሪቱን ሕግ በመተለላፍ ነው። በተጨ ማሪም ቢቢሲ ባገኘው መረጃ መሰረት ግለሰቡ በዚሁ ሳቢያ ያልታሰረ ሲሆን የወንጀል ክስ ስላልተመሰረተበትም ማንነቱ እንደማይገለጽ ለማወቅ … [Read more...] about ወደ ኢትዮጵያ ሊገባ የነበረ 99 ሺህ የሚጠጋ ዶላር ተያዘ
ጭንቅላቱ የደረቀው ህወሓት ኪሱም ሊደርቅ ነው
የብር ኖቶች መቀየር በህወሓት ሠፈር መደናገጥ ፈጥሯል ኢትዮጵያ በአዳዲስ የብር ኖቶች እንደምትጠቀም ጠ/ሚ/ር ዐቢይ ይፋ ካደረጉ በኋላ መቀሌ የመሸገው ህወሓት ችግር ውስጥ መግባቱ ተሰምቷል። አዳዲሶቹ ብሮች ሙስናን እና የኮንትሮባንድን ንግድ መቀልበስ ዓላማው ማድረጉ ተነግሯል። ላለፉት ሁለት ዓመታት መቀሌ መሽጎ የሚገኘው ህወሓት የተባለው የበረኻ ወንበዴዎች ስብስብ ላለፉት እጅግ በርካታ ዓመታት ኢትዮጵያን ያለገደብ ሲዘርፍ የነበረ ቡድን መሆኑን ራሱም የሚመሰክረው ሐቅ ነው። ከሁለት ዓመት ተኩል በፊት ከምኒልክ ቤተመንግሥት ከተባረረ ወዲህ መቀሌ በየሆቴሉ መሽጎ የሽብር ተግባራትን ሲፈጽም ቆይቷል። ይህንንም ተግባሩን ለማስፈጸም እንዲረዳው በሕገወጥ የገንዘብ ዝውውር፤ ሐሰተኛ የብር ኖቶች በማተም ተግባር፤ በኮንትሮባንድ ንግድ፤ ገንዘብ ከአገር በማሸሽ፤ ወዘተ ሕገወጥ ተግባራት … [Read more...] about ጭንቅላቱ የደረቀው ህወሓት ኪሱም ሊደርቅ ነው
ዳውድ ኢብሣ ከህወሓት ጋር በማበርና በሌሎች ምክንያቶች ከሥልጣን ተወገዱ
“ሕወሓት በኦሮሞ ህዝብና ታጋዮች ላይ ላደረሰው ጉዳት ይቅርታ ካልጠየቀ ከፓርቲው ጋር ምንም ግንኙነት የለኝም” ሲል ኦነግ አስታወቀ። የኦሮሞ ነጻነት ግንባር (ኦነግ) ሥራ አስፈጻሚ ድርጅቱን ለ21 ዓመት የመሩትን አቶ ዳውድ ኢብሳን ከሊቀመንበርነት ማንሳቱን ይፋ አድርጓል። የፓርቲው የህዝብ ግንኙነት ሀላፊ አቶ ቀጄላ መርዳሳ አቶ ዳዉድ ኢብሳ በሊቀመንበርነት በቆዩባቸው 21 ዓመታት “የድርጅቱን ገንዘብና ሀብት ብቻቸውን ሲያዙበት ኖረዋል ፤ በድርጅቱ ውስጥ አድልዎ በመፍጠር የአካባቢያቸውን ሰዎችና ዘመዶች ቁልፍ የስራ መደቦች ላይ በመመደብ ጥቅማቸውን አስጠብቀዋል” ሲሉ ለአል ዐይን ኒውስ ተናግረዋል። ግንባሩ የሊቀመንበሩን መታገድ በተመለከተ መግለጫም አውጥቷል። መግለጫው አቶ ዳውድን “በዚህ መሰል ኣካሄድ ከድርጅቱ ህገ ደንብና አሰራር ውጭ የራሳቸውን አምባገነንነት በድርጅቱ ላይ … [Read more...] about ዳውድ ኢብሣ ከህወሓት ጋር በማበርና በሌሎች ምክንያቶች ከሥልጣን ተወገዱ
ሶማሌ ክልል የጦር መሣሪያ መሰብሰብ ሊጀምር ነው
የሶማሌ ክልል ልዩ ኃይል ዋና አዛዥ ጦር መሳሪያዎችን የመሰብሰብ ዘመቻ እንደሚጀመር አስታወቁ! ትላንት (እሁድ) ከሶማሌ ብዙሃን መገናኛ ድርጅት ጋር ቆይታ ያደረጉት፣ የሶማሌ ክልል ልዩ ኃይል ዋና አዛዥ ረ/ኮሚሽነር መሀመድ አህመድ በሁሉም የሶማሌ ክልል አከባቢዎች ጦር መሳሪያዎችን የመሰብሰብ ዘመቻ እንደሚጀመር እና ከአሁን በኋላ ለአንድም የሲቪል ማህበረሰብ ትጥቅ እንደማይፈቀድላቸው አስታወቀዋል። በተጨማሪ ከመንግሥት ጦር መሳሪያ ውጭ፣ ለሲቪል ግለሰቦች ታጥቆ መንቀሳቀስ የተከለከለ መሆኑንም ዋና አዛዥ መሀመድ አህመድ ገልፀዋል ። አክለውም ይህ የጦር መሳሪያ የመሰብሰብ ውሳኔው ለዜጎች ሰላም እና ደህንነት ተብሎ የታወጀ ውሳኔ እንደሆነ ኃላፊው አብራርተዋል። የክልሉ ፀጥታ አካላት በክልሉ ውስጥ ያለው የጦር መሳሪያ የመሰብሰብ ዘመቻ በቂ አቅምና ዝግጅትም አላቸው ያሉት … [Read more...] about ሶማሌ ክልል የጦር መሣሪያ መሰብሰብ ሊጀምር ነው
ይቅርታና ምህረት አድራጊው ይወገዳል! የተደረገለትም ይሞታል!
መሃል ሰፋሪ አሊያም ገለልተኛ ይመስል የነበረው የኦሮሞ አክቲቪስቶች በሙሉ የጃዋር ግልገል መሆናቸው የምታውቀው፤ ልክ እንደ አይን-አፋር ሴት እየተቅለሰለሱ፣ እንደ ሽምግሌ ምሳሌ እያበዙ ከሄዱ በኋላ በማጠቃለያው ላይ “ጃዋር መሃመድ በይቅርታ ከእስር ቢፈታ ለሀገርና ህዝብ ይጠቅማል!” ሲሉ ነው። በእርግጥ በእስር ላይ ያለ ሰው እንዲፈታ ማሰብ፣ አማላጅ መላክ ወይም Lobby ማድረግ በተለይ እንደ ኢትዮጵያ ባለ ሀገር ውስጥ የተለመደ ነው። በዚህ ረገድ በሰኔ15ቱ ግድያ ተጠርጥረው የታሰሩ ሰዎች መፈታታቸው በተደጋጋሚ እንደ ማሳያ ተጠቅሷል። ነገር ግን በሰኔ 15ቱ ግድያ የተሳተፉ አካላት በስልጣን ሽኩቻና አለመግባባት ምክንያት የተፈጠረ ነው። በዚህ ምክንያት የተጎዱ ሰዎች መኖራቸው እርግጥ ነው። ነገር ግን በአማራ ክልል የሚገኙ አማራዎችን ወይም ሙስሊሞችን ለማጥፋት ታቅዶ የተፈፀመ … [Read more...] about ይቅርታና ምህረት አድራጊው ይወገዳል! የተደረገለትም ይሞታል!
ኦነግ በኦነግ ላይ ዕርምጃ ሊወስድ ነው
የትኛው ኦነግ ስለየትኛው ኦነግ መግለጫም ይሁን ተቃውሞ እንደሚሰጥ ግራ እስኪያጋባ የደረሰው ዕድሜ ጠገቡ ኦነግ ተከፋፍሎ አላልቅ ብሎ አሁን ደግሞ አንዱ በአንዱ ላይ ዕርምጃ እወስዳለሁ እያለ ነው። ኢትዮ ኤፍ ኤም ያጠናከረው ዘገባ እንዲህ ይነበባል። ኦነግ ከፖርቲው ህግና ስርአት ባፈነገጠ መልኩ በተለያዩ መገናኛ ብዙሀን አሳሳች መግለጫዎችን ሲሰጡ በነበሩ አመራሮቹ ላይ እርምጃ እንደሚወስድ አስታወቀ። የኦነግ ቃላ አቀባይ አቶ ቀጀላ መርዳሳ ለኢትዮ ኤፍ ኤም እንዳሉት የተወሰኑ ሰዎች በተለያዩ መገናኛ ብዙሀን በመቅረብ አላስፈላጊ መግለጫዎችንና መልዕክት በማስተላለፋቸው ምክንያት በተፈጠረ ውዝግብ ላይ ብሔራዊ ምክር ቤቱ በጠቅላላ ጉባኤ በዲሲፕሊን እንዲጠየቁ የሚያስችል ውይይት ማድረጉን ተናግረዋል። በተለያዩ መገናኛ ብዙሀን በአመራሮች መካከል የርዕዮተ አለም ልዩነት እንዳለ … [Read more...] about ኦነግ በኦነግ ላይ ዕርምጃ ሊወስድ ነው
“ፍትኅ ለአዲስ አበባ” በሚል መሪ ቃል የማኅበራዊ መገናኛዎች ዘመቻ ተጀመረ
ስለ አዲስ አበባ ፍትኅ የሚጠይቅ የማኅበራዊ መገኛ ዘዴዎች ዘመቻ ዛሬ በዋናነት በትዊተር ላይ ተጀመረ። ዘመቻው ዛሬም እንደሚቀጥል አዘጋጆቹ የገለጡ ሲኾን፦ “በአዲስ አበባ የታየውን የመሬትና የኮንዶምንየም ምዝበራ በመቃወም” ፍትኅ ለመጠየቅ የተጀመረ መኾኑንም አክለዋል። በዘመቻዉ ላይ “#ፍትህለአዲስአበባ”፤ “#አዲስአበባ” እንዲሁም “#ኢትዮጵያ” የሚሉ አሰባሳቢ ቃላት (ሐሽታጎች) ጥቅም ላይ ውለዋል። የዘመቻው ተሳታፊዎች በአዲስ አበባ ከተማ “ተፈጸመ” ያሉትን አድሏዊ አሠራር እና በደል በመዘርዘር ተቃውሟቸውን እና ቅሬታቸውን ሲያስተጋቡ ተስተውለዋል። የዘመቻው አስተባባሪዎች ባሰራጩት ጽሑፍ፦ “በኢ/ር ታከለ ኡማ አስተዳደር ዘመን በአዲስ አበባ የታለያዩ አድሎአዊ አሠራሮች፤ ጥቅመኝነት፤ የህዝብን ሃብት ማባከን የመሳሰሰሉ ጥፋቶች ተስተውለዋል” ብለዋል። ግድፈቶች … [Read more...] about “ፍትኅ ለአዲስ አበባ” በሚል መሪ ቃል የማኅበራዊ መገናኛዎች ዘመቻ ተጀመረ
ወደ ዛምቢያ ከተሰደዱ 50 ኢትዮጵያውያን አንዱ ግድያ ተፈጸመበት
ኢትዮጵያዊ ስደተኛ ዛምቢያ ካቴቴ አውራጃ ውስጥ በበሀገሬው ቺቦላያ ነዋሪዎች በተፈጸመ ጥቃት መገደሉን ዛምቢያ ሪፖርትስ ትናንት በድረ-ገጹ ዘግቧል። አምሳዎቹ ኢትዮጵያውያን ስደተኞች ዛምቢያ የገቡት ምዋሚ በተሰኘው ድንበር በኩል ሲኾን፤ ወደ ደቡብ አፍሪቃ ከማቅናታቸው አስቀድሞ ካቴቴ ውስጥ በሕገወጥ ቆይተዋል ሲል የአካባቢው ፖሊስ ተናግሯል። የአካባቢው ነዋሪዎች ኢትዮጵያውያኑ ስደተኞች ባረፉበት ቦታ በሌሊት በድንገት ባደረሱት ጥቃት ከግድያው ባሻገር ዘጠኝ ኢትዮጵያውያን መጠነኛ የመቊሰል አደጋ እንደደረሰባቸው የአካባቢው ፖሊስ ኮሚሽነር ሉክሰን ሳካላ ገልጠዋል። ከኢትዮጵያውያን ስደተኞቹ መካከል 38ቱ በፖሊስ ሲያዙ ማንነታቸው ያልተገለጡ ኹለት ስደተኞች ግን ማምለጣቸውን የፖሊስ ኃላፊው አክለው ተናግረዋል። የፖሊስ አዛዡ፦ የአካባቢው ነዋሪ በሰፈራቸው ስለመጡ ሰዎች ጥርጣሬ … [Read more...] about ወደ ዛምቢያ ከተሰደዱ 50 ኢትዮጵያውያን አንዱ ግድያ ተፈጸመበት