• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ለደቡብ ሱዳን ሰላም ማጣት የስዩም መስፍን ሤራ

December 2, 2020 12:01 am by Editor Leave a Comment

5ኛው የሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት 6ኛ ዓመት የስራ ዘመን 2ኛ ልዩ ስብሰባውን ባካሄደበት ወቅት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ በሰጡት ማብራሪያ፤ ከሀዲው የህወሓት ቡድን ኢትዮጵያን በክልልና በዘር ከመከፋፈል አልፎ ጎረቤት ሀገራትን ጭምር በጎሳና በዘር ሲያባላ እንደነበር ተናግረዋል።

“ሶማሊያ ስንሄድ እኛ እኮ እናንተን አናምናችሁም፤ በክልልና በጎሳ ከፋፍላችሁ የምታባሉን እናንተ ናችሁ፤ የእናንተ መንግስት ነው ይህን የሚያደርገን፤ በጣም ነው የምንጠላችሁ” በማለት ሳይደብቁ ኢትዮጵያን ይወቅሱ ነበር ብለዋል ጠቅላይ ሚኒስትሩ።

“በተመሳሳይ ደቡብ ሱዳን ስንሄድም አሁን ላይ በሀገራችን እየተባላንበት ያለው ጉዳይ የእናንተው ውጤት ነው” በማለት ኢትዮጵያን እንደሚወቅሱ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ለምክር ቤቱ አብራርተዋል።

“በኢጋድ ውስጥ ስዩም መስፍን የሚባለውን ሰውዬ መድባችሁ ከፋፍሎን አባልቶን ሄዷል” በሚልም በግልጽ የጁንታው አባላት በጎረቤት አገራት ላይ የሰሩትን የከፋፋይነት ሴራ ለመንግስት እንደሚናገሩ ነው ጠቅላይ ሚኒስትሩ ያስታወቁት።

ዶ/ር ዐቢይ ይህንን በተናገሩ ማግስት ከሃዲው የህውሃት ቡድን ለደቡብ ሱዳን ህዝቦች ሰላም ማጣት እጁ እንደለበት በኢትዮጵያ የደቡብ ሱዳን አምባሳደር ገልጸዋል።

አምባሳደር ጄምስ ፒታ ሞርጋን ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደገለጹት፤ የደቡብ ሱዳን ሰላም ስምምነት ድርድር በከሃዲው የህውሃት ከፍተኛ አመራር አማካኝነት በመደረጉ ለሱዳን ህዝብ አንዳችም ውጤት አላስገኘም።

የደቡብ ሱዳን የሰላም ድርድር ሂደትን በከሃዲው የህውሃት ቡድን አባል በሆኑት አቶ ስዩም መስፍን አሸማጋይነት ድርድሩ ቢደረግም፤ በተቃዋሚ ፓርቲዎች መካከል ባለው የህወሃት የተዛባ አስተሳሰብና አድሏዊ አቋም ከውጤት መድረስ አለመቻሉንም አምባሳደሩ አብራርተዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አህመድ በደቡብ ሱዳን የሰላም ድርድር ሂደት ላይ የከሃዲውን የህወሃት አፍራሽ ሴራን ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ባደረጉት ንግግር መግለጻቸውን አስታውሰው፣ እ ኤ አ በ2015 በሱዳን ተደራዳሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች መካካል በአዲስ አበባ የሰላም ስምምነት ቢፈረምም፣ በአደራዳሪው የጁንታው መሪ ስዩም መስፍን በወሰደው ግልፅ አድልዎ እውን እንዳልሆነ ገልጸዋል።

በወቅቱ የተፈረመው የሰላም ስምምነት ለግጭቱ የታሰበውን መፍትሄ አላመጣም ብለዋል አምባሳደሩ።

የጠቅላይ ሚኒስትሩ ማብራሪያ እንዳስደሰታቸው በመግለጽ ለደቡብ ሱዳን መንግሥት ከለላ መሆኑን ያብራሩት አምባሳደሩ ሁለቱ ሀገራት ለረጅም ጊዜ የቆየውን መልካም ግንኑነት ይበልጥ ለማጠናከር የህወሓትን መጥፎ ፍላጎት ማጋለጥና ከሕዝብ እንዲነጠል ማድረግ አስፈላጊ ነው ብለዋል።

“ደቡብ ሱዳን በአንድ አመራር ታምናለች፣ እሱም የአብይ አህመድ መንግስትና አመራር ነው” ያሉት አምባሳደር ሞርጋን ኢትዮጵያ በአፍሪካ አህጉር አንጋፋ ነፃ ሀገር እንደመሆኗ ውስጣዊ ችግሮቿን በሰላማዊ መንገድ የመያዝና የመፍታት ልምድና እውቀት ያላት ሀገር ናት ብለዋል።

አምባሳደሩ አያይዘውም የሁለቱ አገራት ግንኙነት በፖለቲካ፣ በኢኮኖሚና በህዝብ ለህዝብ ድንበር ከፍተኛ ደረጃ ላይ መድረሱን ጠቅሰው አህጉራዊ ና ዓለም አቀፍ ጉዳዮች ላይ የጋራ አቋም መያዛቸውን ገልፀዋል።

ደቡብ ሱዳን ኢትዮጵያ አሁን ያለችበትን ተግዳሮት እንደምታልፍ እና የልማት ፕሮጀክቶ በተረጋጋና በተቀላጠፈ ሁኔታ እንደምትቀጥል ጠንካራ እምነት እንዳላቸው ተናግረዋል። (ኢ.ፕ.ድ)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Middle Column, Politics

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule