• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ለደቡብ ሱዳን ሰላም ማጣት የስዩም መስፍን ሤራ

December 2, 2020 12:01 am by Editor Leave a Comment

5ኛው የሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት 6ኛ ዓመት የስራ ዘመን 2ኛ ልዩ ስብሰባውን ባካሄደበት ወቅት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ በሰጡት ማብራሪያ፤ ከሀዲው የህወሓት ቡድን ኢትዮጵያን በክልልና በዘር ከመከፋፈል አልፎ ጎረቤት ሀገራትን ጭምር በጎሳና በዘር ሲያባላ እንደነበር ተናግረዋል።

“ሶማሊያ ስንሄድ እኛ እኮ እናንተን አናምናችሁም፤ በክልልና በጎሳ ከፋፍላችሁ የምታባሉን እናንተ ናችሁ፤ የእናንተ መንግስት ነው ይህን የሚያደርገን፤ በጣም ነው የምንጠላችሁ” በማለት ሳይደብቁ ኢትዮጵያን ይወቅሱ ነበር ብለዋል ጠቅላይ ሚኒስትሩ።

“በተመሳሳይ ደቡብ ሱዳን ስንሄድም አሁን ላይ በሀገራችን እየተባላንበት ያለው ጉዳይ የእናንተው ውጤት ነው” በማለት ኢትዮጵያን እንደሚወቅሱ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ለምክር ቤቱ አብራርተዋል።

“በኢጋድ ውስጥ ስዩም መስፍን የሚባለውን ሰውዬ መድባችሁ ከፋፍሎን አባልቶን ሄዷል” በሚልም በግልጽ የጁንታው አባላት በጎረቤት አገራት ላይ የሰሩትን የከፋፋይነት ሴራ ለመንግስት እንደሚናገሩ ነው ጠቅላይ ሚኒስትሩ ያስታወቁት።

ዶ/ር ዐቢይ ይህንን በተናገሩ ማግስት ከሃዲው የህውሃት ቡድን ለደቡብ ሱዳን ህዝቦች ሰላም ማጣት እጁ እንደለበት በኢትዮጵያ የደቡብ ሱዳን አምባሳደር ገልጸዋል።

አምባሳደር ጄምስ ፒታ ሞርጋን ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደገለጹት፤ የደቡብ ሱዳን ሰላም ስምምነት ድርድር በከሃዲው የህውሃት ከፍተኛ አመራር አማካኝነት በመደረጉ ለሱዳን ህዝብ አንዳችም ውጤት አላስገኘም።

የደቡብ ሱዳን የሰላም ድርድር ሂደትን በከሃዲው የህውሃት ቡድን አባል በሆኑት አቶ ስዩም መስፍን አሸማጋይነት ድርድሩ ቢደረግም፤ በተቃዋሚ ፓርቲዎች መካከል ባለው የህወሃት የተዛባ አስተሳሰብና አድሏዊ አቋም ከውጤት መድረስ አለመቻሉንም አምባሳደሩ አብራርተዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አህመድ በደቡብ ሱዳን የሰላም ድርድር ሂደት ላይ የከሃዲውን የህወሃት አፍራሽ ሴራን ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ባደረጉት ንግግር መግለጻቸውን አስታውሰው፣ እ ኤ አ በ2015 በሱዳን ተደራዳሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች መካካል በአዲስ አበባ የሰላም ስምምነት ቢፈረምም፣ በአደራዳሪው የጁንታው መሪ ስዩም መስፍን በወሰደው ግልፅ አድልዎ እውን እንዳልሆነ ገልጸዋል።

በወቅቱ የተፈረመው የሰላም ስምምነት ለግጭቱ የታሰበውን መፍትሄ አላመጣም ብለዋል አምባሳደሩ።

የጠቅላይ ሚኒስትሩ ማብራሪያ እንዳስደሰታቸው በመግለጽ ለደቡብ ሱዳን መንግሥት ከለላ መሆኑን ያብራሩት አምባሳደሩ ሁለቱ ሀገራት ለረጅም ጊዜ የቆየውን መልካም ግንኑነት ይበልጥ ለማጠናከር የህወሓትን መጥፎ ፍላጎት ማጋለጥና ከሕዝብ እንዲነጠል ማድረግ አስፈላጊ ነው ብለዋል።

“ደቡብ ሱዳን በአንድ አመራር ታምናለች፣ እሱም የአብይ አህመድ መንግስትና አመራር ነው” ያሉት አምባሳደር ሞርጋን ኢትዮጵያ በአፍሪካ አህጉር አንጋፋ ነፃ ሀገር እንደመሆኗ ውስጣዊ ችግሮቿን በሰላማዊ መንገድ የመያዝና የመፍታት ልምድና እውቀት ያላት ሀገር ናት ብለዋል።

አምባሳደሩ አያይዘውም የሁለቱ አገራት ግንኙነት በፖለቲካ፣ በኢኮኖሚና በህዝብ ለህዝብ ድንበር ከፍተኛ ደረጃ ላይ መድረሱን ጠቅሰው አህጉራዊ ና ዓለም አቀፍ ጉዳዮች ላይ የጋራ አቋም መያዛቸውን ገልፀዋል።

ደቡብ ሱዳን ኢትዮጵያ አሁን ያለችበትን ተግዳሮት እንደምታልፍ እና የልማት ፕሮጀክቶ በተረጋጋና በተቀላጠፈ ሁኔታ እንደምትቀጥል ጠንካራ እምነት እንዳላቸው ተናግረዋል። (ኢ.ፕ.ድ)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Middle Column, Politics

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am
  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule