• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ነቀርሳው ህወሓት ተነቀለ!

November 29, 2020 04:00 am by Editor 4 Comments

በትግራይ ክልል ከጥቅምት 24 ቀን 2013 ዓ.ም. ምሽት ጀምሮ ለ25 ቀናት በሕዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ሕወሓት) ቡድንና በመከላከያ ሠራዊቱ መካከል ሲደረግ የሰነበተው ውጊያ፣ ቅዳሜ ኅዳር 19 ቀን  ከሰዓት በኋላ  የመከላከያ ሠራዊቱ  የክልሉ ዋና ከተማ  መቀሌን ሙሉ በሙሉ በመቆጣጠር መጠናቀቁን ጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ አህመድ(ዶ/ር) እና የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኤታማዦር ሹም ጄኔራል ብርሃኑ ጁላ አረጋግጠዋል።

መከላከያ ሠራዊቱ ባካሄደው ዘመቻ ንጹኃን ዜጎች ዒላማ ሳይሆኑና ቅርሶች ሳይጎዱ መቀሌ ለመግባት መቻሉን ጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ  አስታውቀዋል።

ሠራዊቱ የመቀሌ ከተማ ነዋሪ ላይ ጉዳት ሳይደርስ እንዴት ከተማዋን መቆጣጠር ይቻላል በሚለው ላይ ኅዳር 18 ቀን ዝግጅት ሲያደርግ መቆየቱን በመግለጫቸው ያስታወሱት የጦር ኃይሎች ጠቅላይ  ኤታማዦር ሹም ጄኔራል ብርሃኑ፣ በዕቅዱ መሠረት ከተማዋን መቆጣጠር መቻሉን ገልጸዋል።

የመከላከያ ሠራዊቱ  በደረሰባቸው አካባቢዎች ሁሉ የትግራይ ሕዝብ ለአገሩ ያለውን ፍቅርና ለመከላከያ ሠራዊቱ ያለውን ክብር ማሳየቱንም ጠቅላይ ሚኒስትሩ ሳይገልጹ አላለፉም።

“የሕወሓት ቡድን ካስታጠቃቸው ጥቂት የክፋት ኃይሎች ውጭ ያለው የትግራይ ሕዝብ መቐለ እስኪገባ ድረስ ለመከላከያ ሠራዊቱ የሚጠበቅበትን ድጋፍ ሁሉ በማድረጉ የሠራዊቱን ድልና የቡድኑን ሽንፈት አፋጥኖታል፤” ብለዋል።

“ቡድኑ በየትኛውም መመዘኛ ለትግራይ ሕዝብ አይመጥነውም” ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣

ለድጋፉ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።

“የሕወሓት ቡድን በሸሸበት ከተማና አካባቢ ሁሉ የጤና ተቋማትን፣ ትምህርት ቤቶችን፣ ድልድዮችን፣ መንገዶችን፣ መሥሪያ ቤቶችን አውድሞ ሄዷል፤” ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ ያፈረሳቸውን መሠረተ ልማቶች በፍጥነት በመገንባት  ሕዝቡ ወደ ሰላማዊ ኑሮው እንዲመለስ ለማድረግ የተቻለው ሁሉ እንደሚደረግ ቃል ገብተዋል።

በተያያዘ ዜና የመከላከያ ሠራዊት ኅብረት ሥልጠና ዋና መምሪያ ኃላፊ ሌተና ጄኔራል ሀሰን ኢብራሂም ዓርብ ኅዳር 18 ቀን 2018 ዓ.ም ምሽት በሰጡት መግለጫ፣ የመከላከያ ሰራዊት ሀውዜን፣ አልነጃሺ፣ አዲቀየህ፣ ማይመሳኖንና ውቅሮን ከሕወሓት ታጣቂ ኃይል ሙሉ በሙሉ ነፃ ማድረጉን አረጋግጠዋል።

የሕግ ማስከበር ዘመቻው በውጤታማነት መከናወኑን ያስታወቁት ጄኔራል መኮንኑ በዓድዋ ግንባር የተንቀሳቀሰው ሠራዊት ሀውዜንን፣ አብርሃ ወአፅብሃንና ውቅሮን የተቆጣጠረ መሆኑን፣ አጉላን ደግሞ በግማሽ ቀን መያዙን ገልጸዋል። በሁለተኛው ግንባር ማለትም በአዲግራት በኩል ሠራዊቱ ሰንቀጣንና አል ነጃሺን በመቆጣጠር ውቅሮን መያዙን በመግለጫው አስረድተዋል።

በሦስተኛው የራያ ግንባር የሚገኘው ሠራዊት አዲቀይህን ከያዘ በኋላ ሔዋነን በመቆጣጠር የትግራይ ልዩ ኃይልን ሁሉንም ምሽጎች ደርምሶ ወደፊት መገስገሱን አስታውቀዋል። በአጉላን በኩል መንገድ ለመዝጋት ቢሞክርም እንዳልተሳካለትና ወደኋላ ማፈግፈጉን ጠቁመው፣ አሁን ግን መቀሌ ከተማ ብቻ መቅረቱንና በጥቂት ቀናት ወስጥ ዘመቻው እንደሚጠናቀቅ ገልጸዋል።

የሦስተኛው ምዕራፍ ዘመቻ ዓላማ የሕወሓት አመራሮችን በቁጥጥር ሥር አውሎ ለሕግ ማቅረብ መሆኑን ያስታወሱት ሌተና ጄኔራል ሀሰን፣ ሠራዊቱ ነፃ ባወጣባቸው ሥፍራዎች ሁሉ የትግራይ ሕዝብ በሠራዊቱ ላይ አልተኮሰም ብለዋል። ይህም የሕወሓት አመራሮችና ሕዝቡ አንድ አለመሆናቸውን ማረጋገጫ ነው ሲሉ አክለው፣ ሕዝቡ እንዲያውም ለሠራዊቱ ወገንተኝነት አሳይቷል ሲሉ ሁኔታውን አስረድተዋል።

የሕወሓት አመራሮችና ቡድናቸው በፕሮፓጋንዳ ጭምር እያፈገፈጉ መሄዳቸው ሽንፈታቸውን እያረጋገጠ እንደሆነም ጄኔራል ሀሰን ጠቁመዋል።

የደቡብ ግንባር የበላይ አዛዥ ሌተና ጄኔራል ባጫ ደበሌ ከሥፍራው በሰጡት ሌላ መግለጫ፣ ከባድ ምት ያረፈበት የትግራይ ልዩ ወደ አዲጉደም እንደሸሸ አስረድተዋል። ሠራዊቱ አካባቢውን በተቆጣጠረበት ወቅት ልዩ ኃይሉ ይጠቀምባቸው የነበሩ ስድስት ታንኮች፣ ሁለት ዙ23 የአየር መቃወሚያዎችና በርካታ መሣሪያዎች መደምሰሳቸውን አስታውቀዋል። ሠራዊቱ አስቸጋሪ መልክዓ ምድር በብቃት በማለፍ ከፊቱ የቆመውን ኃይል መደምሰሱን አስረድተዋል። (ሪፖርተር)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Middle Column, Politics Tagged With: operation dismantle tplf

Reader Interactions

Comments

  1. ታዛቢ says

    November 29, 2020 04:40 am at 4:40 am

    ጉልጉሎች እናመስግናለን
    እንኳን ደስ አላችሁ!
    ወያኔ ከሻገተ አስተሳሰቡና ከሰይጣናዊ ተንኮሉ ጋር ወደ እንጦርጦስ ወርዷል!
    ኢትዮጵያ አንድ የጨለማ ዘመን ታሪክ ዘግታለች

    Reply
  2. Tesfa says

    November 29, 2020 08:47 am at 8:47 am

    ቀደም ብለን የወያኔ አወዳደቅ የሮም አወዳደቅ ይሆናል ስንል ከርኩስ ተግባራቸው ተነስተን ሁሉም ቀን ጠብቆ እንደሚፍረከረክ በታሪክ ስለተረዳን ነበር እንጂ እንደ ዘመኑ ነብያት ውሸትን ተቃምሰን አልነበረም። የሚሰማና የሚያይ አይን ይዘው መስማትና ማየት የተሳናቸው የእነዚህ የሃገር ኩርንችቶች መጨረሻ እንዲህ መሆኑ አምነው ለተደገፉባቸውና ዘርፈው ላዛረፏቸው ሁሉ ኦሮማይ ያሰኛል። በመሰረቱ ወያኔ ዲያብሎስ ነው። ገና ብዙ ጉድ እንሰማለን። ወያኔ ከ 40 በላይ በዘለቁ አመታት በትግራይ ህዝብና በመላው የሃገሪቱ ህዝብ ላይ የፈጸመው በደል ናዚ ጀርመኒ በአይሁዶች ላይ ከፈጸመው ይልቃል። አሁን በማይካድራ አማራዎችን መጨፍጨፉ ከግፉ በጭልፋ የሚያሳይ እኩይ ተግባር እንጂ የተንኮል መጽሃፉ ገና አልተከፈተም። በዙ ጉድ እናያለን እንሰማለን ገና!
    የዛሬን አያድርገውና ሃገራችን የሰላም አየር ተንፍሳ፤ ሰው በሰውነቱ በሚሰላበት ዘመን የተዘፈነ አንድ የዘፈን ግጥም ትዝ አለኝ። ዘፋኙ እውቁ ጥላሁን ገሰሰ ሲሆን ገጣሚውና ግጥሙን ከዜማው ጋር ያዋሃደው ሰው ትዝ አይለኝም። የዘፈኑ ስንኝ እንዲህ ይላል።
    “ግማሽ ጎኔ በሳቅ ግማሽ ጎኔ በሃዘን ተጨንቋል መንፈሴ ልሳቅ ወይስ ልዘን”። እንዲያ ነው የሚሰማኝ አሁን በሰሜን ሰራዊት ላይ የሆነውንና በወያኔ መቃብር ላይ ሰዎች አበባ ሲያስቀምጡ ስመለከት መጭውን የሃገሬን እድል ፈንታ ሳስብ ጭንቅ ጭንቅ ይለኛል። መሳቅም ማልቀስም ይቃጣኛል። መቼ ይሆን ያዘው ጥለፈው በለውና በያት የሚለው ቀርቶ በሰው መስፈሪያ ወገኔ ተሰፍሮ በሰላምና በጤና የሚኖረው? ያ ቀን ይመጣ ይሆን? ወይስ እንዲሁ እንደተናቆርን ከጊዜ ጋር እንሻገራለን?
    አሁን ወደ ሱዳን የኮበለሉት የወያኔ ወመኔዎች ስደተኞች አይደሉም። የወያኔ የኋላ የክፉ ጊዜ ደጀን ሃይሎች እንጂ። ወያኔ እነዚህ ሰዎች የማይካድራን ሰዎች ጭፍጭፈው ወደ ሱዳን እንዲሻገሩ ያደረጋቸውም ለራሱ የወደፊት እኩይ ተግባር በማሰብ ነው። መመለስ ስለማይችሉ በሰሩት ግፍ የተነሳ የወያኔ አዲስ ምልምልና ጠበንጃ ተሸካሚ በግብጽና በሱዳን እየተረድ በዚህም በዛም ትንኮሳ ማድረጋቸው አይቀሬ ነው። ወያኔ የሚያስበው በበረሃ በተገጠመለት ጭንቅላት ነው ስንል እብዶች ናቸው ማለት ነው። የሳይኮሎጂ ሳይንስ አንድን ነገር ደጋግሞ ያለምንም ለውጥ እና የረባ ውጤት ማድረግ የጭንቅላት በሽታ ነው ይለናል። እነርሱ እንዲያ ናቸው። የክፋት ኮሮጆዎች በኢትዮጵያ ታሪክ ውስጥ ታይቶ የማይታወቅ ጭራቆች ናቸው። ከእነርዝራዣቸው ግባዕተ መሬታቸው ካልተፋጠነ ለትግራይ ህዝብም ሆነ ለቀሪው የሃገራችን ህዝብ ውጋት መሆናቸው አይቀሬ ነው። መንግስት በመረጃ የተደገፈ ወንጀል ከመሰረተባቸው የትኛውም የአለም ክፍል ቢሆን አሳልፎ እንደሚሰጣቸው እርግጠኛ ነኝ። ማንም አያስጠጋቸውም። ክሳቸው ግን ሲፈለግ የሚገኝ፤ በእውነት ላይ የተመሰረተ መሆን ይኖርበታል። ጊዜው መረጃ ይሻልና። አሁን በተደጋጋሚ ወደ አስመራ መተኮሳቸው መብገናቸውን ያሳያል እንጂ አቅሙ እንኳን አሁን ድሮም የላቸውም። ግን የኤርትራው መሪ ዝምታ የበለጠ አሳሯቸዋል። እንዲህ ነው ዝምታም መልስ ነውና! እስቲ ማን ይሙት ከቅርብ ጊዜ በፊት የኤርትራ ህዝብ ህዝባችን ነው ሲሉ እንዳልነበሩ አሁን በተውሶ ሮኬት ሊገድሉት ይፈልጋሉ? ይህ ፍጽም እብደት ነው። ግን ሙት ይዞ ይሞታል አይነት ስለሆነ ከተስፋ መቁረጥ የሚመነጭ ጭካኔ ለመሆኑ ይገባናል። ወያኔ ግን አፈር ለብሷል። የሽምቅ ውጊያ፤ የከተማ ውጊያ ገለ መሌ ቢሉም የትም አይደርሱም። የወያኔ አራጊ ፈጣሪነት ተቀብሯል።
    ጠ/ሚ አብይ በሌሎቹ የሃገራችን ክፍሎች በወያኔ እየተላኩም ሆነ በራሳቸው ተነሳሽነት ወይም የግብጽ ክፍያ እየደረሳቸው በሃገራችን ህዝቦች ላይ የሚፈጸመውን በደል ለማስቆም አይቀጡ ቅጣት ሊሰጣችው ይገባል። በመሰረቱ ዋና ማሰልጠኛ ጣቢያው ሱዳን መሆኑን የአይን ምስክሮች ይናገራሉ። የተጠናከረ በውጭም በውስጥም የስለላ መረብ ሊኖር ይገባል። ድሮ በስለላ ስራ የተካኑ የንጉሱም ሆነ የደርግ ሰዎችን በአማካሪነት በማሰባሰብ አሁን ካለው ከዘመኑ የኤሌክትሮኒክስ የስለላ ስራ ጋር አጣምሮ ገዳዪችን በማፈን ለፍርድ ማቅረብ፤ ካልተቻለ ባሉበት መግደል፤ ሌሎችም ለሃገርና ለህዝብ ደህንነት ችግር የሆኑ ነገሮችን የሚያመክን ለህዝብና ለሃገር ተቆርቋሪ የሆነ የስለላ መረብ መዘርጋት አለበት፡፤ በዘሩና በሃይማኖቱ የሚያስብ ግለሰብ ለሃገራችን አይጠቅምም። ሃገራችን ገና ብዙ ውጣ ውረድ ይጠብቃታል። ሁላችንም ለሃገር አንድነትና ለህዝባችን ደህንነት ተጣምረን እንቁም። በቃኝ!

    Reply
  3. ታዛቢ says

    November 29, 2020 06:27 pm at 6:27 pm

    ባላውቅህም ተስፋ ሃሳብህንና መቆሮቆርህን እጋራለሁ::አንዳልከውም እብዶቹ የሚሰሩትን መገመት አስቸጋሪ ነውና መጠንቀቁ ተገቢ ነው::
    ግና የዛሬ ሃምሳ ዓመት የነበረ የፖለቲካ: የኢኮኖሚ: የቴክኖሎጂና የባህል መልከዕምድር ዛሬ የለምና ስጋት አይኑረን::
    በድሮ በሬ ያረሰ ወያኔ ብቻ ነው!!!!

    Reply
    • Tesfa says

      December 1, 2020 06:44 am at 6:44 am

      ወዳጄ ታዛቢ እንደ እኔ እምብዛም ሥጋት ስለማይገባህ ደስ ይለኛል፡፡ አዎን በድሮ በሬ ያረሰ የለም፡፡ ግን እየከፈሉ እያሰለጠኑ እንደ በፊቱም ባይሆን በሚቻላቸው ሁሉ ሃገር ሰላም እንዳትሆን መፍጨርጨራቸው አይቀሬ ነው፡፡ ልንረዳ የሚገባው ነገር በሃገራችን የረጅም ጊዜ ታሪክ ውስጥ እንደ ወያኔ ያለ መርዘኛና ከፋፋይ ድርጅት ተፈጠሮ አያውቅም፡፡ የሰሜኑን እዝ ጄኔራል ገና ታሞ ሄደ የሚተካውንም ጄኔራል አንቀበልም አሉ ሲሉ ለጓደኞቼ መርዝ አብልተውት ነው ስላቸው ስቀውብኛል፡፡ የሆነው እንደዛ ነው፡፡ በ 27 ኣመት የመከራ አገዛዛቸው በልዪ ልዪ ሆስፒታሎች ባሰለፏቸው ገዳይ ሃኪሞች ለህክምና ወደዚያው ያቀኑ ሰዎች መርፌ በመውጋት የተገደሉ ብዙ ናቸው፡፡ ወያኔ የወንበዴዎች ጥርቅም ነው ስንል ቀማኛና በሰው ደም ነጋጅ መሆኑን አይናችን አይቶና ኑረንበት እንጂ በስማ በለው አይደለም፡፡ በምንም ሂሳብ ወያኔና የወያኔ አፍቃሪዎች አይታመኑም፡፡ የሃገራችን ጠላቶች የውጭ ሃይሎችና በዘርና በቋንቋ የሰከሩ እብዶች ናቸው፡፡ የወደፊት የሃገሪቱን እድል ፈንታ በተመለከተ እንዳንተ/ቺ የረጋ ልብ እንዲኖረኝ እታገላለሁ፡፡ ለአሁኑ መጨኔቄ አልቀረም፡፡

      Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule