የኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ባለሥልጣናት በኦሊምፒክና በአትሌቲክስ ፌዴሬሽን ላይ ትኩረት ያደረገ የፕሮፓጋንዳ ሥራ እንዲሠራ መመሪያ መስጠታቸው ተሰማ። መመሪያው ተግባራዊ መሆኑን ተከትሎ ኢቲቪ የሚያቀርበው ዘገባ የሕግ ጥያቄ ማስደገፊያ እንዲሆን ተደርጎ ለመረጃነት እየተዘጋጀ መሆኑ ከሌሎች ወገኖች ተደምጧል። ከፓሪሱ ኦሊምፒክ መጀመር ቀደም ብሎ በማኅበራዊ ሚዲያው የተጀመረው ዘመቻ ሁለት ቡድኖች ጎራ ለይተው ውዝግብ መጀመራቸውን አመላካች እንደነበር ይታወሳል። ሻለቃ ኃይሌ ገብረሥላሴና አትሌት ገዛኸኝ አበራ ጎራ ለይተውና ተመሳሳይ አቋም ይዘው የለኮሱት ተቃውሞ ውድድሩ ከመጀመሩ ቀናት በፊት ሲሆን፣ ማኅበራዊ ሚዲያው ተቃውሟቸውን ለመግዛትና ለማሰራጨት ጊዜ አልወሰደም። ከወራት በፊት በተጠናቀቀ ምርጫ ላይ ቅሬታ በማንሳት የተጀመረው ክስ ውድድሩ ከተጀመረ በኋላም ከፓሪስ በሚወጡ ዐውዳቸውን … [Read more...] about የኢቲቪ ባለሥልጣናት ኦሊምፒክና አትሌቲክስ ላይ ያነጣጠረ ፕሮፓጋንዳ እንዲሠራ አዘዙ
Archives for August 2024
ገዱ: “የዘር ማጥፋት ወንጀለኛ ነው እንክሰስው”፤ “ባለውለታ ነው እንጠቀምበት”
ሰሞኑን ለጥገኝነት ማመልከቻቸው ደጋፊ ነው የተባለለትን ዘለግ ያለ ጽሑፍ ያቀረቡት ገዱ አንዳርጋቸው በትግራይ ማኅበረሰብ ዘንድ የተከፋፈለ ዕይታ የፈጠሩ መሆናቸው ተነገረ። ““የዘር ማጥፋት ወንጀለኛ ነው፤ እጃችን ገብቷል እንክሰሰው” ባዮች በርተተው የታዩ ቢሆንም “ባለውለታችን ነውና አሁንም እንጠቀምበት” የሚሉ በሌላ ወገን ድምጻቸውን እያሰሙ ነው። በዘመነ ትህነግ የሥርዓቱ ተላላኪና ጉዳይ ፈጻሚ የነበሩት ገዱ አንዳርጋቸው የዚያን ጊዜው አለቆቻቸውን ለማስደሰት ያልታዘዙትን፣ ያልተጠየቁትን እላፊ በመሄድ በመፈጸም አለቆቻቸውን እጅ በመንሳት ይታወቃሉ። ለዚህ ታማኝነታቸው በአማራ ሕዝብ ላይ የመጨረሻውን ሥልጣን እንዲያገኙና ሎሌነታቸውን የበለጠ በደስታ እንዲፈጽሙ አድርጓቸዋል የሚሉ ጥቂት አይደሉም። እንደማሳያም የወልቃይትን ጉዳይ ይጠቅሳሉ። ገዱ አንዳርጋቸው ከዚህ በታች ያለው … [Read more...] about ገዱ: “የዘር ማጥፋት ወንጀለኛ ነው እንክሰስው”፤ “ባለውለታ ነው እንጠቀምበት”
ዘመኑን የጠበቀ የወታደራዊ ሬዲዮ መገጣጠሚያ ፋብሪካ ተከፈተ
በመከላከያ ኢንጅነሪንግ ኢንዱስትሪ ኮርፖሬሽን የኤሌክትሮኒክስ ኢንጅነሪንግ ኢንዱስትሪ የራዲዮ መገጣጠሚያ ፋብሪካ የጦር ሀይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ ፣ የጦር ሀይሎች ምክትል ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ጄኔራል አበባው ታደሰ እና የተቋሙ ከፍተኛ ወታደራዊ አመራሮች በተገኙበት ነው ተመርቆ የተከፈተው። የመከላከያ ሰራዊታችን አገራችን በየጊዜው የገጠሟትን ፈተናዎች በሌሎች አገራት ቴክኖሎጂዎች ላይ በመመርኮዝ ግዳጅ እየተወጣ እንደዘለቀ አውስተው የተመረቀው የወታደራዊ ራዲዮ ፋብሪካ የሰራዊቱን የተልዕኮ አፈፃፀምና የግዳጅ ስምሪት የሚያቀላጥፍ እንደሆነ ተናግረዋል። "ወታደራዊ ራዲዮው በአሁኑ ጊዜ በዓለም ላይ የመጨረሻው የዲጅታል ስታንዳርድ ራዲዮ ነው።" ያሉት ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ ይህንኑ እውን በማድረግ ረገድ የቻይናው ሀይቴራ ካምፓኒ እና የመከላከያ … [Read more...] about ዘመኑን የጠበቀ የወታደራዊ ሬዲዮ መገጣጠሚያ ፋብሪካ ተከፈተ
“የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ አእምሮና የደም ዝውውር ሊኖረው ነው”
ሁሉም ባይባልም አብዛኛዎቹ የኢትዮጵያ የተቃዋሚ ፓርቲዎች ዋና የፖለቲካ ፕሮግራም ሶሻል ዴሞክራሲ ወይም ሊበራል ዴሞክራሲ ወይም ምርጫን ማዕከሉ ያደረገ ዴሞክራሲያዊ ፖሊሲ ነው። የኢኮኖሚ ፕሮግራማቸው ደግሞ ገበያ መር ኢኮኖሚ ነው። እነዚሁ ፓርቲዎች በምርጫ ክርክር ሲደረግ በዋናነት እያነሱ የሚከራከሩት መንግሥት ኢኮኖሚውን ተቆጣጥሮታል፤ የዕዝ ኢኮኖሚ ነው አገሪቱን ለችግር የዳረጋት፣ የኢኮኖሚው አካሄድ በገበያ እንጂ በመንግሥት መመራት የለበትም በሚል የከረረ ተቃውሞ በማቅረብ ሲቃወሙ ላለፉት በርካታ ዓመታት ሰምተናል። ባለፈው ሰኞ መንግሥት የአገሪቱን ዐቢይ (ማክሮ) ኢኮኖሚ ወደ ገበያ መር የሚወስድ ውሳኔ ይፋ ሲያደርግ እነዚሁ ተቃዋሚዎች “እሰይ ስለቴ ሰመረ” ባይሉም ቢያንስ ለዓመታት ሲሟገቱለት የነበረው ሃሳብ ድል አድርጎ በማየታቸው ጥንቃቄ የተሞላበት ድጋፍ ሊያሰሙ የሚጠበቅ … [Read more...] about “የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ አእምሮና የደም ዝውውር ሊኖረው ነው”
የፖሊሲ ጥሰት በፈጸሙ 44 የግል ኮሌጆች ላይ እርምጃ ተወሰደ
የ18 የግል ኮሌጆች ፍቃድ ታገደ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትምህርትና ሥልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለሥልጣን አደረግኩት ባለው ድንገተኛ የቁጥጥር ስራ የፖሊሲ ጥሰት ፈፅመዋል ያላቸውን 18 የግል ኮሌጆች ፍቃድ አግዷል፡፡ ከታገዱት በተጨማሪ መለስተኛ የፖሊሲ ጥሰት በፈፀሙ 26 የግል ኮሌጆች የፅሁፍ ማስጠንቀቂያ ተሰጥቷቸዋል፡፡ ባለሥልጣኑ በትምህርትና ስልጠና ጥራት ማረጋገጥና ምርምር ዳይሬክቶሬት በ2016 ዓ.ም ድንገተኛ ቁጥጥር የተደረገባቸው 59 የግል ኮሌጆች ሲሆኑ 18ቱ ታግደዋል፤ 26ቱ ከቀላል እስከ ከባድ የቃል ማስጠንቀቂያ ተሰጥቷቸዋል፡፡ በድምሩ 44 የግል ኮሌጆች እርምጃ ተወስዶባቸዋል ተብሏል፡፡ ተቋማቱ እንደደረሳቸው አስተዳደራዊ እርምጃ መሰረት በአስር ቀናት ውስጥ እርምትና ማስተካከያ በማድረግ በጽሁፍና በአካል በመቅረብ ሪፖርት እንዲያደርጉ ባለስልጣኑ … [Read more...] about የፖሊሲ ጥሰት በፈጸሙ 44 የግል ኮሌጆች ላይ እርምጃ ተወሰደ
ዶላር ጨምሯል በሚል የዋጋ ጭማሪ ባደረጉ 77 የንግድ ድርጅቶች ላይ እርምጃ ተወሰደ
በቅርቡ የተደረገውን የዶላር ጭማሪ ምክንያት በማድረግ የዋጋ ጭማሪ ባደረጉ 77 የንግድ ድርጅቶች ላይ እርምጃ መዉሰዱን የአዲስ አበባ ንግድ ቢሮ አስታወቀ። ቢሮዉ ሃምሌ 23 እና 24 ቀን 2016 ዓ.ም ባደረገዉ የክትትል ሥራ በአዲስ ከተማ ክ/ከተማ 11 እንዲሁም በየካ ክ/ከ 2 በድምሩ 13 የንግድ ድርጅቶች ላይ እርምጃ መወሰዱን ያስተወቀ ሲሆን ይህ ዜና እስከተጠናቀረበት ጊዜ ድረስ በሁሉም ክፍለ ከተማ በተደረገ የአሰሳ ስራ 77 ንግድ ሱቆች ላይ አስተዳደራዊ እርምጃ መወሰዱን የአዲስ አበባ ከተማ ንግድ ቢሮ ሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ሰውነት አየለ ተናግረዋል። ኃላፊው ጨምረውም አብዛኛው የተወሰዱ እርምጃዎች በማኅበረሰቡ ጠቆማ እንደሆነ ገልጸው የከተማው ነዋሪዎች አሁንም የዋጋ ጭማሪ በሚያደርጉ የንግድ ድርጅቶችና ሱቆች በአቅራቢያቸው በሚገኝ ወረዳ መጠቆም እንዳለባቸዉ … [Read more...] about ዶላር ጨምሯል በሚል የዋጋ ጭማሪ ባደረጉ 77 የንግድ ድርጅቶች ላይ እርምጃ ተወሰደ