የዋልድባ ገዳም በህዋሓት መሪዎች በዓይነ ቁራኛ የወደቀው ገና ትግሉ እንደተጀመረ ነው። የዋልድባ ገዳም የህወሓት መሪዎች እንዲወድም ሃሳብ ያቀረቡት በ1973 መጨረሻ አካባቢ ሲሆን፣ አቅማራ ተብሎ በሚጠራ ቦታ በወቅቱ የህወሓት መናኸሪያ ነበር። በተመቤን ውስጥ የሚገኘው ቦታ በፕሮፓጋንዳ ጽ/ቤት ተሰብስበው ወሰኑ፤ በስብሰባ የነበሩት አመራር ፖሊት ቢሮው በሙሉ ነበር። እነሱም፣ ስብሃት ነጋ፣ አረጋዊ በርሄ፣ ገደይ ዘርአጽዮን፣ አባይ ፀሃየ፣ ስዩም መስፍን እና መለስ ዜናዊ ነበር። በወቅቱ ማ/ኮሚቴ የነበሩ ናቸው። በዚህ ስብሰባቸው የዋልድባን ገዳም እጣ ፈንታ ወሰኑ። ዋልድባ እንዲወደም! የዋልድባ ገዳም ለብዙ መቶ ዘመናት የቅዱሳን፣ ብፁአን፣ ባህታውያን፣ ቀሳውስት፣ አባቶች፣ ደናግል፣ ዲያቆናት ወዘተ ሰፈር በመሆን በኢትዮጵያ ቅዱስና በታሪክ ትልቅ ምእራፍ የያዘ ገዳም ነው። ይህ ቅዱስ ገዳም … [Read more...] about ህዝባዊ ወያኔ ሓርነት ትግራይና ዋልድባ ገዳም
Archives for April 2017
በበዓል ዋጋ ንረት የምትታመሰው አዲስ አበባ!
ተባዕት ዶሮ ከ280 - 360 ብር እየተሸጠ ነው! በግ ከ2,200 - 3,800 ብር የሽያጭ ዋጋ ደርሷል! ድልብ በሬ ከ25,000- 37,000 እየተሸጠ ነው! በረዥም ጊዜ ሂደት እየተዋረሰ የመጣው ኃይማኖታዊ በዓል አከባበራችን ከምግብ እና መጠጥ ጋር በጽኑ የተቆራኘ ነው፡፡ የአጽዋማትን ፍች በተመለከተ ከተቀመጡ ኃይማኖታዊ መርሆች ይልቅ ተለምዷዊ ድርጊቶች ገዥ ሐሳብ ሆነው ቀርበዋል፡፡ በዓላትን የታከከ ከፍተኛ የዋጋ ንረት ደግሞ የአገሪቱ ኢኮኖሚ መገለጫ ሆኗል፡፡ መንግስታዊ ኃላፊነቱን በዘነጋ አገዛዝ ውስጥ ላለችው ኢትዮጵያ የመሠረታዊ ሸቀጦችና የቁም እንስሳት ዋጋ ንረት መታየት አዲስ ነገር አይደለም፡፡ የህዝቡ የድህነት ቁስል ላይ ለመቆም የማይሳቀቁ ስግብግብ ነጋዴዎች የዋጋ ንረቱን በማጐን ከህወሃት/ኢህአዴግ አገዛዝ ቀጥሎ ተጠያቂዎች ናቸው፡፡ ለመንግሥት ሠራተኞች … [Read more...] about በበዓል ዋጋ ንረት የምትታመሰው አዲስ አበባ!
ለዴሞክራሲ አርበኞች ተባብሮ ለመታገል የሚያስችል ቀላልና ጠቃሚ ሃሳብ
አስቀድሞ የከበረ ሰላምታ ይድረሳችሁ፤ በዚህ ማስታወሻ የቀረበውን ሃሳብ ጠቃሚ ነው የምትሉ ስለጠቀሚነቱ፤ ጎጂ ነው የምትሉም ስለጎጅነቱ የሚታያችሁን ምክንያቶች ጨምራችሁ መልስ እንድትሰጡ ትጠየቃላችሁ፤ ሌሎች ይህ ሃሳብ ከተላለፈበት ዕለት ቀደም ብሎ ተደራጅታችሁ እንቅስቃሴ የጀመራችሁና በዚህ ዝርዝር ውስጥ ያልገባችሁ ካላችሁ ተቀላቅላችሁ ድምጻችሁን ማሰማት ትችላላችሁ። በጉዳዩ ላይ ድምጽ ለማሰማት ግለሰቦችም መብታችሁ የተጠበቀ ነው። መልስ ስትሰጡ ግን አድራሻችሁን ማኖር አትርሱ። የመልሱ ውጤት ከታየ በዃላ ቀጣይ ሂደት ይኖራ ተብሎ ተስፋ ይደረጋል። ለዚህ ጽሁፍ መነሻ፤- ከወራት በፊት አቶ ዘውዴ ጉደታ የተባሉ ወንድም "የኢትዮጵያ አገራዊ ንቅናቄ እና የአገር አንድነትን "ያገቱት" ሦስት ተጻራሪ ሃይሎች" በሚል ርዕስ አንድ ሰፋ ያለ ጽሁፍ አስነብበው ነበር። ከዚያም በላይ የጸሃፍያን … [Read more...] about ለዴሞክራሲ አርበኞች ተባብሮ ለመታገል የሚያስችል ቀላልና ጠቃሚ ሃሳብ
“… ተድብድቤ በቃሬዛም ቢሆን ያምጡኝ እንጂ ካሁን በኋላ በራሴ ፈቃድ ‘ወደ ችሎት’ አልመጣም” በቀለ ገርባ
"… ተድብድቤ በቃሬዛም ቢሆን ያምጡኝ እንጂ ካሁን በኋላ በራሴ ፈቃድ አልመጣም” በፍርድ ሂደቱ ሲሉ መሰላቸታቸውን አቶ በቀለ ገርባ ተናገሩ። አቶ በቀለ ይህንን የተናገሩት ሃሙስ ባስቻለው ችሎት የመናገር እድል እንዲሰጣቸው ጠይቀው ሲፈቀድላቸው ነው። ከሁለት ቀን በፊት አቃቤ ህግ በማስረጃነት አቀርበዋለሁ ሲለው የነበረውን የድምጽ ከምስል ማስረጃ አስተርጉሞ እንዲያቀርብና የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኤጀንሲ ሃላፊ ችሎት እንዲገኙ ትዕዛዝ ሰጥቶ ነበር። ይሁን እንጂ በቀጠሮው በትዕዛዙ መሰረት ዓቃቤ ሕግ በእነ አቶ በቀለ ገርባ ላይ ያቀረበውን የድምፅ ከምስል ማስረጃ የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን ዛሬም እንዳላስተረጎመው አሳውቋል። የኤጀንሲው ሃላፊ ችሎት አለተገኙም። የክልሎች ቋንቋ ሃላፊ ጸጋ ልዑል ወልደኪዳን "ብቁ ጋዜጠኞች ስለሌሉ አልተተረጎመም” በማለት የሰጡትን ምክንያት ፍርድ … [Read more...] about “… ተድብድቤ በቃሬዛም ቢሆን ያምጡኝ እንጂ ካሁን በኋላ በራሴ ፈቃድ ‘ወደ ችሎት’ አልመጣም” በቀለ ገርባ
የበጋው መብረቅ (ሌፍተንት ጀነራል ጃጋማ ኬሎ)
. . . ጃጋማ በውጊያ ብቻ አልነበረም ብስለቱ በአስተዳደርም የተደነቀ ነበር።ለምሳሌ፤ከአምቦ መንገድ በላይ ያሉት ነዋሪዎች ጥራጥሬ እያዋጡ ቆሎ እየቆሉ ለአርበኛው ይረዳሉ፤ከአምቦ መንገድ በታች ያሉት ግን የጃገማ አርበኞች ሙጀሌ የወረሳቸው ሰለሆኑ ይህን የተሰነጣጠቀ እግራቸው ችሎ መራመድ አይችሉም፤ስለዚህ እንኳን እኛን ከኢጣሊያ ስራዊት ሊጠብቁን እና ሊከላከልሉን ቀርቶ ለራሳቸውም ሰለማይሆኑ በምንም ነገር አንረዳቸውም ማለታቸውን ጃጋማ ሰማ። ለሰራዊቱም ትእዛዝ ሰጥቶ ወደ ሃያ ሺህ ከብቶቻቸውን አስነዳባቸው፤ ህዝቡም በጣም ተደናግጦ ምነው ምላሳችንን በቆረጠው በሚል በጣም ተደናገጡ።ቀንበራቸውን ተሸክመው የጃጋማ ጦር የሰፈረበት ቦታ ድረስ በመሄድ እግዚኦ አሉ። ወጣቱ መሪ ጃጋማ እንዲህ አላቸው (እኛ ከእናንተ የወጣን የእናንተ ልጆች ነን፤ጠላት የሚንቀን አንሶ ለሐገራችንና ለእናንተ በባዶ … [Read more...] about የበጋው መብረቅ (ሌፍተንት ጀነራል ጃጋማ ኬሎ)
ማዕከላዊ፤ የዜጐች ዋይታ ማማ! የስቃይ ማዕከል!
በማዕከላዊ ስቃይ ተፀንሶ ይወለዳል፤ ጡት ጠብቶ ዳዴ ብሎ ጐልምሶ ያረጅበታል!! እንደገና አዲስ የማሰቃያ ስልት ይወለዳል!! በማዕከላዊ በንጹሐን ዜጐች ደም የጨቀዩ ገራፊዎች ይርመሰመሱበታል!! ከዝግጅት ክፍሉ፡- ማዕከላዊ አገዛዙን በወታደራዊ የበላይነትና በደህንነቱ አቅም በቁጥጥር ስሩ ያዋለው ህወሓት፤ ማዕከላዊ እስር ቤት ውስጥ እያደረሰ ያለውን ቃላት የማይገልፁት የዜጐች ስቃይ በተመለከተ ጎልጉል ድረገጽ የጥቃቱ ሰለባ የሆኑትን ዜጐችና ቤተሰቦቻቸውን በማነጋገር ይህን ዘገባ በሁለት ክፍል አጠናቅሯል። ዘገባው የጋዜጠኛነት ሙያ የሚጠይቀውን (“የሕዝብ አይንና ጆሮ በመሆን የተደበቀውን ፈልፍሎ ማውጣት!” የሚለውን) ቀዳሚ መርህ በማድረግ በዳሰሳ ጥናት ተደግፎ የተዘጋጀ መሆኑን እንገልፃለን። የኢትዮጵያዊያን የስቃይ ጎሬ በሆነው ማዕከላዊ እስርቤት በ“ምርመራ” ወቅት በዜጎች ላይ … [Read more...] about ማዕከላዊ፤ የዜጐች ዋይታ ማማ! የስቃይ ማዕከል!
የኢትዮጵያ ሐገራዊ ንቅናቄ ተስፋና ሥጋት!
ላለፉት ሁለት ዐሥርት ዓመታት በዘረኛው የትግሬ ነፃ አውጪ የአገዛዝ መዳፍ ሥር የታፈነውን ሕዝባችንን ወደ ነፃነትና የዴሞክራሲ ምዕራፍ ለማሸጋገር የጋራ ትግል ለማድረግ ሲሞከር ቆይቷል። ሆኖም በእነዚህ ዘመናት ውስጥ የተፈጠሩት የፖለቲካ ኃይሎች ትብብር፣ ቅንጅት፣ ኅብረት እና ውህደት አንዱም ከዳር ሳይደርስ እንዲሁ ሲሰበሰብና ሲበተን ከርሟል። እንደ አባባልም እንደ መታወሻም “ተባበሩ ወይ ተሰባበሩ” የሚለው የዶ/ር መረራ ጉዲና መፈክር አንዱም ገቢራዊ ሳይሆን አብዛኞቹ የፖለቲካ ተቋማት በአገዛዙ ጫናና በራሳቸው ደካማ አደረጃጀት ህልውናቸው እየጠፋ ለሐገር የሚተርፍና ትውልድ የሚረከበው አንድም አግባቢ የጋራ ማዕከል ሳይመሰረት በኪሳራ የታጀቡ ዓመታትን አሳልፈናል። ትብብር የጉልበት ምንጭ ነው።ትብብር ድልን ማቅረቢያ ዘለቄታዊና ሠላማዊ ሽግግርን ማሳለጫ መሳርያ ነው።ትብብር ከሚከሰረው … [Read more...] about የኢትዮጵያ ሐገራዊ ንቅናቄ ተስፋና ሥጋት!
ከኢሳያስ አፈወርቂ ቃለ-ምልልስ በስተጀርባ
ጠንቋይና ፖለቲከኛ የሚያመሳስላቸው አንድ ነገር አለ። ሁለቱም ተገልጋያቸውን ለማምታታት የትኩረት አቅጣጫ ማስቀየርን ተክነውበታል። ኢሳያስ አፈወርቂ በዚህኛው - የኦሮሚያ ሚዲያ ኔትወርክ - ገለጻቸው ራሳቸውን ሳይቀይሩ ሌላውን ለመቀየር የተነሱ ግብዝ ነው የሆኑት። ይህ "ቃለ-ምልልስም" አንድ አላማ አለው። አላማውን ለማወቅ ቃላቶችን መሰንጠቅም አያስፈልግም። ግልጽ ነው። 'ብዙ ስላልተሰራበት' መልዕክቱ የተጠበቀውን አላማ የመታ አይመስልም። ቃለ-ምልልሱ የተደረገበት ወቅት፣ የተመረጠበት ሰዓት የሚሰጠን ግልጽ የሆነ ግን የተለየ ትርጉም አለ። ጠያቂዎቹ በሻዕቢያ ላይ የነበራቸው የፖለቲካ አቋም ከመቅጽበት መቀየሩ በራሱ የሂደቱን ግራጫ ምስል ያሳየናል። "ሁሉን ቢናገሩ ሆድ ባዶ ይቀራል" ይላሉ አበው። እነዚህ ጉዳዮች ውስጥ ገብቶ መላ-ምቶችን መዘርዘሩ አስፈላጊ ባይሆንም (አንዱ መላ ምት … [Read more...] about ከኢሳያስ አፈወርቂ ቃለ-ምልልስ በስተጀርባ
Kidane Alemayehu, My Journey with the United Nations and Quest for the Horn of Africa’s Unity and Justice for Ethiopia
The journey which author Ato Kidane Alemayehu chronicles in his new book takes him through Lesotho, Tanzania, Uganda, United Arab Emirates and the Horn of Africa as a representative of the United Nations, and ultimately to establish an organization dedicated to confronting “Fascist Italy and the Vatican.” His book contributes valuable information to the history of East Africa, the United Arab Emirates, and to the rationale behind Ethiopia’s struggle to win recompense from Italy for crimes … [Read more...] about Kidane Alemayehu, My Journey with the United Nations and Quest for the Horn of Africa’s Unity and Justice for Ethiopia
«ችግሩን ለማስወገድ፣ ግለሰብ ወይም ቡድን መወገድ አለበት» ዐባይ ፀሐዬ
የትግራይ ሕዝብ ነፃ አውጭ ግንባር (ወያኔ) አጠቃላይ ግብ፣ ኢትዮጵያንና ኢትዮጵያዊነትን ማጥፋት ነው። የዚህ ግብ መዳረሻ ደግሞ በኢትዮጵያዊነታቸው በጽኑ የሚያምኑ ኢትዮጵያውያን እና ከሁሉም በላይ፣ የዐማራውን ነገድ ማጥፋት ሲቻል እንደሆነ በማመኑ፣ ላለፉት 43 ዓመታት የኢትዮጵያዊነት የወል ዕሴቶችን፣ ነባር ሃይማኖቶችን፣ የአገራዊነት መገለጫ የሆነችውን ሰንደቅ ዓላማችንን፣ በሕዝቡ መሀል የአንድነት መገለጫ የሆኑ ተቋሞችንና አሠራሮችን፣ ግንኙነቶችን በአዋጅ አጥፍቷል። በዐማራው ነገድ ላይ የተቀነባበረ የዘር ማጥፋትና የዘር ማጽዳት ወንጀል ፈጽሟል። የተለያዩ መረጃዎች እንደሚያመለክቱት በወያኔ ዘረኛ አገዛዝ ከአምስት ሚሊዮን በላይ ዐማሮች ከምድረ-ገጽ እንዲጠፉ ተደርጓል። የትግሬ-ወያኔ ለዚህ ኢትዮጵያን፣ ኢትዮጵያዊነትንና የዐማራውን ነገድ ለማጥፋት ላለመው ዓላማው ወደ ግቡ መዳረስ … [Read more...] about «ችግሩን ለማስወገድ፣ ግለሰብ ወይም ቡድን መወገድ አለበት» ዐባይ ፀሐዬ