“ዳግም የመኖር እድል ተሰጠኝ፤ ተማርኩበት፤ እናንተም ተማሩ” “ጥቁሩ ሰው” ኦባንግ ሜቶ በሁሉም ስፍራ፣ በየትኛውም አጋጣሚ ለሚፈልጋቸው ሁሉ “አለሁ” የሚሉ ኢትዮጵያዊ ናቸው። ዘረኝነትን፥ ዘውገኝነትን፥ ጎሠኝነትን አጥብቀው ይዋጋሉ። ይጸየፉታል። ከዘር ቆጠራና ከቂም የጸዳች ኢትዮጵያን ማየት ህልማቸውና የመጨረሻ ግባቸው ነው። ሰብዓዊነት ለአፍታም ከአንደበታቸው የማይለይ፣ በሚያውቋቸው ሰዎች ሁሉ የሚወደዱ፣ ግልጽ ተናጋሪነታቸው ልዩ የሚያደርጋቸው ኦባንግ በዚሁ ባህሪያቸው “አባ ነቅንቅ” የሚል ስም ተሰጥቷቸዋል። በስደት ለሚሰቃዩ የኢትዮጵያ ልጆች /እሳቸው ቤተሰቦቼ የሚሏቸው/ በጠሯቸው ቦታና ሁሉ በመገኘት ለሚያሳዩት ትጋት አቻ የላቸውም። ኢትዮጵያን በመወከል በከፍተኛ ቦታዎች የሚሟገቱ፣ ያዘነውን የሚጎበኙ፣ ለሴት እህቶቻችን ቀድመው የሚደርሱ እኚህ ውድ ሰው በድንገተኛ የመኪና አደጋ … [Read more...] about ኦባንግ ሜቶ ከከፋ አደጋ ተረፉ!
Archives for April 2017
“ግድያው ተገቢና ሕጋዊ ነው” የህወሃት “ሰብዓዊ” ኮሚሽን
ህወሃት/ኢህአዴግ በንፁሐን ደም ላይ ማላገጡን ቀጥሏል!! በኢትዮጵያ ለሩብ ክፍለ ዘመን የተከማቸው የግፍ አገዛዝ በምሬት የታጀበ ህዝባዊ አመጽ አስነስቷል። ህዝባዊ አመጽ ደግሞ ለኢትዮጵያ አዲስ ክስተት ባይሆንም በአገሪቱ ዉስጥ በሁለንተናዊ ዘርፍ ተጽዕኖ መፍጠር ከሚችሉት ሁለቱ ክልሎች (የኦሮሞና የአማራ፤ የደቡብ ኮንሶንና ጌዴኦን ተቃውሞዎች ሳንዘነጋ) ተከታታይነት ባለው መልኩ የአገዛዙን ማህበራዊ መሰረት በሚንድ ሁኔታ አመጽ መቀስቀሱ ይህኛዉን ክስተት የተለየ ያድርገዋል። በዚህ ህዝባዊ አመፅ ህወሃት ከበረሃ የሽምቅ ባህሪው በተሻገረ የ“መንግስት” ባህሪ የሌለው መሆኑን ለወዳጅ ጠላቶቹ ያስመሰከረበትን መንግስታዊ ፍጅት በዜጎች ላይ ፈጽሟል። በገዛ ዜጎቹ ላይ የከፈተውን ጦርነትና ጅምላ እስር ዘግይቶም ቢሆን በአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ሥም ህጋዊ ሽፋን ሲሰጠው ታይቷል። ድርጊቱንም … [Read more...] about “ግድያው ተገቢና ሕጋዊ ነው” የህወሃት “ሰብዓዊ” ኮሚሽን
ተደናቂ ለሆነ የፍትሕ አገልግሎት ስለ ተሰጠ ሽልማት
ጋዜጣዊ መግለጫ ዓለም አቀፍ ሕብረት ለፍትሕ - የኢትዮጵያ ጉዳይ ተደናቂ የሆነ የፍትሕ አገልግሎት በመፈጸማቸው ከዚህ ቀጥሎ ስማቸው ለተዘረዘሩት ሽልማት ያበረከተ መሆኑን ይገልጻል፤ ቀሲስ/ዶር. ምክረ-ሥላሴ ገብረ አማኑኤል፤በፋሺሽት ኢጣልያ የኢትዮጵያ ወረራ ዘመን ስለነበረው የቫቲካን ሚና ግንዛቤ እንዲገኝ በደረሱት መጽሐፋቸው አማካኝነት ስላበረከቱት አስተዋጽኦ፤ ሚር. ኢያን ካምፕቤል፤ ፋሺሽቶች በኢትዮጵያ ላይ ስለ ፈጸሙዋቸው የጦር ወንጀሎች በደረሱዋቸው መጽሐፎች ስላበረከቱት አስተዋጽኦ፤ ሚር. ቫሌሪዮ ቺሪያቺ፤ ፋሺሽት ኢጣልያኖች፤ በኢትዮጵያ ላይ ስለ ፈጸሙት የጦር ወንጀልና ባሁኑ ወቅት በመኪያሔድ ላይ ስላለው የፍትሕ ጥረት ግንዛቤ እንዲገኝ ፊልም በማዘጋጀት ስላበረከተቱት አስተዋጽኦ፤ አቶ ከባዱ በላቸው፤ ፋሺሽት ኢጣልያኖች፤ በቫቲካን የትብብር ድጋፍ፤ … [Read more...] about ተደናቂ ለሆነ የፍትሕ አገልግሎት ስለ ተሰጠ ሽልማት
“ጋንታይናው” ‹ጋትዬ› አሰፋ ጫቦ
እውቁ ፖለቲከኛና አንጋውፋ ምሁር አቶ አሰፋ ጫቦ አረፉ። አቶ አሰፋ በማራኪ ተናጋሪነታቸው እና አንደበተ ርቱዕነታቸው የሚታወሱ የሕግ ምሁር ነበሩ። ብዙውን እድሜያቸውን የጨረሱት በኢትዮጵያ ፖለቲካ እና በእስር ቤት ውስጥ ነው። አሜሪካ ከገቡ በኋላ በ20 ግዛቶች እየተዘዋወሩ ኖረዋል። በቅርቡ ባሳተሙት የ”ትዝታ ፈለግ” መጽሃፋቸው ለረጅም ግዜ በአንድ ቤት የተቀመጥቁት እስር ቤት ውስጥ ብቻ ነው ሲሉ አስነብበውናል። በአንድ ቤት የተቀመጥቁት እስር ቤት ውስጥ ብቻ ነው ሲሉ አስነብበውናል። እኚህ ምሁር በደረሰባቸው ህመም ዳላስ-ቴክሳስ በሚገኝ ሆስፒታል ህክምና ሲክታተሉ ቆይተው በዛሬው እለት (እሁድ) ከዚህ አለም በሞት ተለይተዋል። ጣይቱ የባህልና የትምህርት ማህከል አሰፋ ጫቦን እረፍት አስመልክቶ የሚከተለውን የሃዘን መግለጫ አውጥቷል። አቶ አሰፋ ጫቦ ከአባቱ ከጫቦ ሣዴ ሃማ ያሬና … [Read more...] about “ጋንታይናው” ‹ጋትዬ› አሰፋ ጫቦ
የኔታ መስፍን ወልደ ማርያም የዘመን ዕንቁ! የትውልድ ዋርካ!! 87ኛ ዓመት
መግባቢያ! የሀገረ-ኢትዮጵያ የእውቀት አደባባይ በአስፈሪ ዝምታ ተውጧል። ምሁራኖቻችን ከህዝባዊ ተዋፅኦ አፈግፍገዋል። የአደባባይ ምሁራን ቁጥር ከዕለት ወደ ዕለት በመናመን ላይ ባሉ ብርቅዬ የዱር እንሰሳት መመሰል ከጀመረ ዓመታት አልፈዋል። ቁጥራቸው የበዛ ምሁራን አገዛዙ በፈጠረው የጥቅመኝነት ፖለቲካ ጥላ ስር መጠለል ምርጫቸው ሆኗል። ጥቂት የማይባሉት ደግሞ የባዕድ አገር ስደትን መርጠዋል። ሕዝባዊ መድረኮቻችንን ፋይዳ ቢስ በሆኑ ርዕሰ ጉዳዮችና በተዛቡ የታሪክ ትርክቶች፤ በዘውጋዊ አጥርና አገራዊ ከፍታን መፍጠር በማይችሉ ሙግቶች ተውጠዋል። ዕድሮችና የመረዳጃ ማህበራት ሳይቀር ዘውጋዊ ቅርጽ (አጥር) ሰርተዋል። አገሪቱ ለገባችበት የፖለቲካ-ኢኮኖሚ ቅርቃርና ለማህበራዊ ችግሮቻችን መፍትሔ ይሰጣሉ ተብለው ተስፋ የተጣለባቸው የፖለቲካ ልሂቃን አገሪቱን ለአራት አስር ዓመታት ክፉኛ … [Read more...] about የኔታ መስፍን ወልደ ማርያም የዘመን ዕንቁ! የትውልድ ዋርካ!! 87ኛ ዓመት
የእግዚአብሔር መልእክት በነቢዩ ኢሳይያስ በኩል
"ኑና እንዋቀስ ይላል እግዚአብሔር፤ ኃጢአታችሁ እንደአለላ ብትሆን እንደአመዳይ ትጸዳለች እንደደምም ብትቀላ እንደባዘቶ ትጠራለች፤ እሺ ብትሉ ለእኔም ብትታዘዙ የምድርን በረከት ትበላላችሁ፤ እንቢ ብትሉ ግን ብታምጹም ሰይፍ ይበላችኋል፤ የእግዚአብሔር አፍ ይህን ተናገሮአልና፡፡" ኢሳ. 1/18. በእግዚአብሔር ለሚያምን ሰው፣ እግዚአብሔር ሁልጊዜም፣ ለዘለዓለም ሙሉና የማይወዳደሩት ኃይል እንዳለው ለሚያምን ሰው፣ ለእግዚአብሔር ትናንትም፣ ዛሬም፣ ነገም አሁን መሆኑን ለሚያምን ሰው "ኑና እንዋቀስ" (በእንግሊዝኛው "come now let us reason together") ማለት ለእግዚአብሔር ምን ያህል መውረድ እንደሆነ መገንዘብ የሚዳግት አይመስለኝም፤ የእንግሊዝኛው ትንሽ ሻል ያለ መስሎ "ኑና እንከራከር" የሚል ቢሆንም ከመጨረሻው የላይኛው ዳኛ ጋር መከራከር የሚችለው ማን ነው? እግዚአብሔር … [Read more...] about የእግዚአብሔር መልእክት በነቢዩ ኢሳይያስ በኩል
ማዕከላዊ፤ የዜጐች ዋይታ ማማ! የስቃይ ማዕከል! (ክፍል ሁለት)
የማጠቃለያው መግቢያ እስኪ አንድ ጥያቄ እንመልስ፤ እንዴት መሽቶ ይነጋል? እነዚህ ወገኖች እንዴት ቻሉት? እንዲህ ያለው ስቃይ እንዴት ሌሎችን ያስደስታል? በህይወት ያለ ሰው በኤሌክትሪክ ማቃጠል ምን ማለት ነው? ሰውን ማኮላሸት ምን የሚሉት ጭካኔ ነው? ሰውን ሰቅሎ መርሳት፣ ገልብጦ ሲደበድቡ ማደርና ማቃጠል፣ ተነግሮ፣ ተወርቶ፣ የማያልቅ ጉድ! እንዴት ነው እነዚህ ሰዎች የሚያስቡት? ሕዝብ ስሜት ያለው አይመስላቸውም? የወላድንና የህጻናትን እንባና የፈጣሪን ፍርድ ለጊዜው ወደ ጎን ቢሉትም፣ ነገሮች በዋይታ የሚዘልቁ ሆነው ስለመሰራታቸው እርግጠኞች ናቸው? የትግራይ ሕዝብስ ለምን ዝም ትላለህ? የትግራይ ምሁራን ይህ እርካታን ይሰጣችኋል? ከመጠርጠር እስከ መመርመር፣ እስከ ማሰር፣ መክሰስ፣ መፍረድና ይቅርታ ማስጠየቅ በትግራይ ህዝብ ነጻ አውጪ ግምባር (ህወሃት) እየተከናወነ፤ የአሳሪው … [Read more...] about ማዕከላዊ፤ የዜጐች ዋይታ ማማ! የስቃይ ማዕከል! (ክፍል ሁለት)
መዘጋቱ ታቅዶ የተከፈተው የአህያ ቄራ
በህወሃት ፈቃድ በቢሾፍቱ የተከፈተው አህያ ማረጃ (ቄራ) መዘጋቱ በእንግሊዝኛ የሚታተመው ፎርቹን ጋዜጣ ከሁለት ቀናት በፊት ዘግቧል፡፡ ቄራው የተከፈተ ሰሞን የኢንቨስትመንት ኮሚሽን ድጋፍ እንደነፈገው አብሮ ተዘግቧል፡፡ ቄራው የተከፈተው እንደሚዘጋ ታቅዶ ነበር፡፡ የዛሬ ሦስት ሳምንት አካባቢ በቻይናዊ ባለሃብት ከአዲስ አበባ 48ኪሜ ርቀት ላይ በምትገኘው ቢሾፍቱ (ደብረዘይት) ከተማ የአህያ ማረጃ መከፈቱ ከተሰማበት ጊዜ ጀምሮ በብዙዎች ዘንድ የመወያያ ርዕስ ሆኖ ቆይቷል፡፡ ከውይይቱም ባለፈ በርካታዎች ጉዳዩን ከህወሃት/ኢህአዴግ ባለሥልጣናት ጋር በማገናኘት የመሳለቂያ አጀንዳ አድርገውት ከርመዋል፡፡ መዘጋቱንም በተመለከተ “አንዳንድ ባለሥልጣኖችን ከሥጋት ለመታደግ ነው” በማለት የተሳለቁም አሉ፡፡ ቄራው በሥራ በቆየበት ሦስት ሳምንታት ውስጥ ሦስት መቶ አህዮችን ማረዱ ፎርቹን መረጃ … [Read more...] about መዘጋቱ ታቅዶ የተከፈተው የአህያ ቄራ
“ጠርጥሮ የሚይዝህ፤ የሚመረምርህ፤ ዓቃቤ ሕግ ሆኖ የሚከስህ፤ ዳኛ ሆኖ የሚፈርድብህ፤ ሽማግሌ ሆኖ ይቅርታ ጠይቅ የሚልህ፤ [በሙሉ] ህወሃት ነው” ሃብታሙ አያሌው
ሃብታሙ አያሌው ከአዲስ ድምጽ ጋር ያደረገው ቃለምልልስ … [Read more...] about “ጠርጥሮ የሚይዝህ፤ የሚመረምርህ፤ ዓቃቤ ሕግ ሆኖ የሚከስህ፤ ዳኛ ሆኖ የሚፈርድብህ፤ ሽማግሌ ሆኖ ይቅርታ ጠይቅ የሚልህ፤ [በሙሉ] ህወሃት ነው” ሃብታሙ አያሌው
ወንዙ እና ዛፉ
ስርሽን አየሁት ቁልቁል ተዘርግቶ፣ ረዝሞ ተባዝቶ፣ አንድ አንቺን ሊያሳድግ፣ አንድ አንቺን ሊያቀና፣ እጅግ ተበራክቶ፣ በዚህ ከቀጠለ የጉዞ ርዝመቱ፣ ውፍረት ከጨመረ፣ ካደገ ቁመቱ፣ ወንዙ አንጀቱ ታልቦ፣ መቅኒው ተመጥምጦ፣ አፅመ ወዙ ደርቆ፣ ደም ውሃው ተመጦ፣ መላ አካሉ ፈርሶ እርቃኑን ተጋልጦ፣ ባዶ መቅረቱ ነው ድንጋይ ጥርሱ ገጦ፣ ወለላዬ ከስዊድን (welelaye2@yahoo.com) … [Read more...] about ወንዙ እና ዛፉ