የያዝነውን እናጢን! ምን እያደረግን ነው? የትግሬዎቹ ገዢ ቡድን በሚያደርገው የዕለት ተዕለት አውዳሚ ተግባሩ በመቆጣት፤ ለተቃውሞ መነሳትና፤ ይህን አካል በተግባሩ ወንጅሎ፤ በደሎቹን መዘርዘሩ አንድ ነገር ነው። ይህ ተቃውሞ ነው። በመቃወምና ይህ መደረግ የለበትም ብሎ በመጮህ፤ የተወሰነ ግብን ማስገኘት ይቻላል። ተግባሩ ግን ይቀጥላል። ቢበዛ ቢበዛ፤ በተግባሩ ሂደት ላይ ትንሽ ማስተካከያ ማስከተል ይቻላል። ከዚያ በተረፈ ግን፤ ይህ በመፈጸም ያለ በደል፤ በድጋሚ እንዳይከሰት የሚያቆመው ነገር የለም። ይሄን በማድረግ የሚረካ ሊኖር ይችላል። እንደገና፤ ይህ ተቃውሞ ነው። በታቃራኒው ደግሞ፤ የተፈጸሙትና በመፈጸም ላይ ያሉት በደሎች፤“መደረግ የለባቸውም!” ብሎ መነሳት ብቻ ሳይሆን፤ “የዚህ ሁሉ ምንጩ፤ አንድ አካል ነው። ይህ አካል መንግሥታዊ ሥልጣኑን ባንድ መንገድ ወይንም በሌላ፤ በጁ … [Read more...] about ሥርዓት ለመለወጥ የሚደረግ የፖለቲካ ትግል፤ ወይንስ የተበታተነ ተቃውሞ?
Archives for April 2017
“ኢጂኣኦ” – የቻይናና አህያ ፍቅር – ቻይና በዓመት 4 ሚሊዮን የአህያ ሌጦ ትፈልጋለች
“አህያ ሲጠፋ እህል ማን ሊሸከም ነው? ሴት?!” የአህያ ሥጋና ቆዳ ንግድ እንደ ህገወጡ የአውራሪስ ቀንድ ንግድ እንዳይሆን ተሰግቷል “አህያ ልባችን ነው። አህያ ህልውናችን ነው። አህያ ቤተሰባችን ነው። አህያ ውለታውና ተግባሩ ተዘርዝሮ የሚያልቅ አይደለም። ገዢዎቻችንም ቢሆኑ የአህያን ጥቅም በአግባቡ ያውቁታል። በበረሃ ሁሉን ችሎ እዚህ ያደረሳቸው አህያ ነው። እናም ጉዳዩ ከወሬ በላይ ነውና በሰከነ መልኩ ለማሰብ ፍላጎቱ ካለ ጊዜው ገናነው” ሲሉ የቱሉ ቦሎው ነዋሪ ይናገራሉ። የጎልጉል የአዲስ አበባ ዘጋቢ ያናገራቸው የቱሉ ቦሎ ነዋሪ እህል ነጋዴ ናቸው። እንደ ምሳሌ የሚያነሱት ጉዳይ የሚደመደመው በጥያቄ ነው። እንዲህ ይላሉ “አህያ ሲመናመን ከገጠር ማን ተሸክሞ ወደ ገበያ ያመጣ? ያው የፈረደባት ሴት በወገቧ ልትሸከም?” ለወትሮው “ሴት፣ የሴቶች መብት፣ የሴቶች የህግ … [Read more...] about “ኢጂኣኦ” – የቻይናና አህያ ፍቅር – ቻይና በዓመት 4 ሚሊዮን የአህያ ሌጦ ትፈልጋለች
ተራዛሚው የኦሮሚያ ድርቅ እና ያዘለው አደጋ!
በኦሮሚያ በሦስት ዞኖች ብቻ 241 ት/ቤቶች ተዘግተዋል፤ 114,751 ተማሪዎች ትምህርታቸውን አቋርጠዋል! በቦረናና በጉጂ ዞኖች 127,010 ከብቶች በዘንድሮው ድርቅ ሞተዋል! ድርቅ ከፍ ሲልም ችጋርና ረሃብ ለኢትዮጵያ ተጠባቂ የስጋት ምንጭ ሆነው እንደቀጠሉ ዘመናት ተቆጥረዋል፡፡ በተለይም ባለፉት ሃምሳ ዓመታት ካሳለፍነው አስከፊ የርስ በርስ እና ከጐረቤት አገራት ጋር ከተደረጉ ጦርነቶች ጐን ለጐን ድርቅ፣ ችጋር፣ ረሃብ ሌላኛው የኢትዮጵያ አስከፊ የታሪክ ምዕራፍ ሆኖ ቀጥሏል፡፡ በቀደሙት ጊዜያት በየአስር ዓመታት ልዩነት ኢትዮጵያን በሰፊው ይጐበኛት የነበረው ድርቅ፤ ባለፉት ሃያ አምስት ዓመታት አገሪቱን ደጋግሞ ሲያጠቃና የከፋ ማኅበራዊ ቀውስ ሲያስከትል ታይቷል፡፡ በተራዛሚው ጦርነት ፍፃሜ ማግስት በአገሪቱ የተከሰተው የ1988 ዓም ድርቅ የአማራ፣ የሶማሌ፣ የአፋር እና … [Read more...] about ተራዛሚው የኦሮሚያ ድርቅ እና ያዘለው አደጋ!
በሁዳዴ ጾም የአህያ ልኳንዳ!
አህያን ጅብ ብቻ ሲበላው ነው የምናውቀው! "ደሳለኝ" ተብሎ ስለሚጠራው አህያ፤ በወያኔ ሚዲያ የተተረከልን ታሪክ መሳጭ ነው። እነሱ ጫካ ውስጥ በነበሩበት ወቅት፣ አስገደ ገብረስላሴ በ45 ብር ገዝቶ ለወያኔ ማጓጓዣ ይሆን ዘንድ አበረከተ። ይህ "ደሳለኝ" የሚባለው አህያ ከባድ ጭነት እየተሸከመ ያገለግላቸው ነበር። በአንድ ወቅት በጦርነት ተሸነፉና ይዘውት የነበረውን ስፍራ ለቅቀው ተበታተኑ። ከቀናት በኋላ አንዳንዶቹ ወደቀድሞ ምሽጋቸው ተመልሰው ለመምጣት እንኳን ሲቸገሩ ደሳለኝ ግን መንገዱን ሳይስት እዚያው ስፍራ ይጠብቃቸው ነበር። በመጨረሻም የአህዮች አለቃ ተባለና "ብፃይ" (ጓድ) የሚል የማዕርግ ሹመትን አገኘ። አሁን ደሳለኝ በህይወት የለም። ወያኔዎች ግን በበኩር ልጁ እየተጽናኑ እንደሆነ ይናገራሉ። አባቱ አብሮን ብዙ ተጉዟል ሲሉ፣ "ለልጁ" የጠቅላይ ሚኒስትርነትን ሹመት … [Read more...] about በሁዳዴ ጾም የአህያ ልኳንዳ!
Horrifying Testimony of Torture in TPLF Prison: Ethiopia
Note: Ethiopia is a current non-permanent member of UN security council and a member of UN human rights council VOA Interview: Part-1 (23 March 2017) + Part-2 (25 March 2017): Habtamu Ayalew: Former spokesman of Andenet Party (Ethiopia) VOA Introducer, Alula Kebede: Today’s guest for democracy in action program is Mr. Habtamu Ayalew, former spokesperson of the opposition, Andenet Party (unity party) in Ethiopia. Mr. Habtamu was subjected to two years of imprisonment, waiting for trial after … [Read more...] about Horrifying Testimony of Torture in TPLF Prison: Ethiopia
ከቆሻሻ ኑሮና ሞት ለመላቀቅ ቆሻሻውን ስርዐት ማስወገድ
ነገሩ ሁሉ ከድጡ ወደማጡ በሆነባት ሀገራችን በየጊዜው የሚፈራረቁት ሰቆቃዎች ልብን በሀዘን ካራ ማድማታቸውን እንደቀጠሉ ነው። ባለፈው አንድ ዓመት ብቻ ከደረሱብን መዓቶች ጥቂቱን ብናነሳ፤ በረኃብ አለንጋ እየተገረፉ ደጃፋቸው ላይ ድፍት ብለው የቀሩትን፣ መብታቸውን ለመጠየቅ ሲጮሁ የጥይት ራት የሆኑትን፣ የኢሬቻን በዓል ለማክበር አምረው ደምቀው እንደወጡ ገደል ሰብስቦ ያስቀራቸውን፣ እንዲሁም በቅርቡ በቆሻሻ ናዳ ታፍነው እስከወዲያኛው ያንቀላፉትን ወገኖቻችንን በቁጭትና በመሪር ሀዘን እናስባለን። እነዚህን አደጋዎች ይበልጥ አሳዛኝና አስከፊ የሚያደርጋቸው ደግሞ በሀገሪቱ የተንሰራፉት አምባገነንነት፣ ዘረኝነት፣ ምዝበራ፣ ራስወዳድነትና ግድየለሽነት ውጤት መሆናቸው ነው። በአስራዎች በመቶ እድገት ሽምጥ ስለሚጋልበው ኢኮኖሚዋ ነጋ ጠባ የሚዘመርላት የወያኔዋ ኢትዮጵያ ዘራፊዎቿ ከቪላ ቪላ … [Read more...] about ከቆሻሻ ኑሮና ሞት ለመላቀቅ ቆሻሻውን ስርዐት ማስወገድ
የብአዴን መክዳትና የ“በቀል” ፍርሃት የወለደው “የኢኮኖሚ አብዮት” በኦሮሚያ፤
“ህወሃት የፈጸመው ግፍ በየትኛውም ዘመን የሚረሳ አይሆንም” በህወሃት ገደብ የለሽ የሥልጣን ፍቅርና የቁስ ሰቀቀን ውልቅልቋ እየወጣ ያለችው ኢትዮጵያ ከፍታው ርቋት የቁልቁለቱን ጉዞ ተያይዛዋለች። ለወጣበት ዘውግ ልዕልና የሚተጋው ህወሃት ህግና ሞራል በማይዳኘው ድርጅታዊ ቀኖናው እየተመራ ኢትዮጵያን ማድማቱን ቀጥሎበታል። እስር፣ ቶርቸር፣ ስቃይ፣ ስደት፣ ሞትና የግዞት ኑሮ ከህወሃት ዘውግ ጥላ ውጪ ያሉ ኢትዮጵያውያን ሁሉ እድል ፈንታ ሆኗል። ከነዚህ በመከራ ከሚዳክረው የኢትዮጵያ ሕዝብ መካከል አንዱ የኦሮሞ ሕዝብ ነው። እውነታው ግን ሰፊና ለም የሆነ መሬት ላይ የሰፈረው የኦሮሞ ሕዝብ በቁመቱ ልክ የፖለቲካና ኢኮኖሚ ተጠቃሚነቱ ሊከበርለት እንዳልቻለ ወራሪው ህወሃት ራሱ ለፖለቲካ ፍጆታም ቢሆን ያመነውና ማንም ሊከደው የማይችል የአደባባይ ሃቅ ነው። በአገሪቱ የፖለቲካ ምህዳር ላይ … [Read more...] about የብአዴን መክዳትና የ“በቀል” ፍርሃት የወለደው “የኢኮኖሚ አብዮት” በኦሮሚያ፤
አደራዳሪ የሌለው ድርድር፥ ሐኪም የሌለው ሆስፒታል ነው
አገራችን ባለፈው ዓመት ካለፈችበት ህዝባዊ ተቃውሞዎች አንፃር ኢሕአዴግ ከህጋዊ አገራዊ ተፎካካሪ ፓርቲዎች ጋር ድርድር ማድረግ እንደሚፈልግ መግለፁ ለብዙዎቻችን ትንሽ የተስፋ ጭላንጭል ነበር። ሆኖም በቅድመ ድርድር ሂደቱ ወቅት ኢሕአዴግ ያሳየው አካሄድ ሚጠቁመው ከድርጅቱ አመራር ውስጥ አንዳንዶቹ አገራችን ያለችበትን አደገኛ ሁኔታና ሂደት በአግባቡ ያላጤኑ ፥ አደጋውን አለባብሰው ማለፍ የመረጡ ፥ ብቃትና አቅም የሌላቸው ፅንፈኛ ጥቂቶች የድርድር ተስፋውን እያጨለሙት መሆኑን ነው። ኢሕአዴግ ከደርግና ከአፄው ስርዓት ያልተማረው ዋና ቁምነገር ሁሉን ተቆጣጥሮ ሁልጊዜ እያለባበሱ ማለፍ እንደማይቻል ነው። እስከ መጨረሻው ሰጥቶ መቀበልን ያልፈለገው ደርግ ዛሬ የታሪክ አመድ ሆኗል። በፍጥነት ተሃድሶ ማድረግ ያልፈለገው የአፄው ስርዓት ዛሬ የሚገኘው በጥቂት አረጋውያን ትዝታ ውስጥ ብቻ … [Read more...] about አደራዳሪ የሌለው ድርድር፥ ሐኪም የሌለው ሆስፒታል ነው