• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የእግዚአብሔር መልእክት በነቢዩ ኢሳይያስ በኩል

April 21, 2017 04:01 am by Editor 4 Comments

“ኑና እንዋቀስ ይላል እግዚአብሔር፤ ኃጢአታችሁ እንደአለላ ብትሆን እንደአመዳይ ትጸዳለች እንደደምም ብትቀላ እንደባዘቶ ትጠራለች፤ እሺ ብትሉ ለእኔም ብትታዘዙ የምድርን በረከት ትበላላችሁ፤ እንቢ ብትሉ ግን ብታምጹም ሰይፍ ይበላችኋል፤ የእግዚአብሔር አፍ ይህን ተናገሮአልና፡፡” ኢሳ. 1/18.

በእግዚአብሔር ለሚያምን ሰው፣ እግዚአብሔር ሁልጊዜም፣ ለዘለዓለም ሙሉና የማይወዳደሩት ኃይል እንዳለው ለሚያምን ሰው፣ ለእግዚአብሔር ትናንትም፣ ዛሬም፣ ነገም አሁን መሆኑን ለሚያምን ሰው “ኑና እንዋቀስ” (በእንግሊዝኛው “come now let us reason together”) ማለት ለእግዚአብሔር ምን ያህል መውረድ እንደሆነ መገንዘብ የሚዳግት አይመስለኝም፤ የእንግሊዝኛው ትንሽ ሻል ያለ መስሎ “ኑና እንከራከር” የሚል ቢሆንም ከመጨረሻው የላይኛው ዳኛ ጋር መከራከር የሚችለው ማን ነው? እግዚአብሔር ነው፤ ትልቁ ነገር እሱ ፈቀደ፤ “እንዋቀስ” አለ!

መዋቀስ ዓላማ አለው፤ ለመግባባት ነው፤ ለመስማማት ነው፤ ለፍቅር ነው፤ ለሰላም ነው፤ ለመረዳዳት ነው፤ እንደመለስ ዜናዊ መንገዱን ጨርቅ ያድርግላችሁ ማለት ሲቻለው፤ ኑና እንዋቀስ የሚል ኃያል አምላክ ለእኛ ምን ያስተምረናል?

የእግዚአብሔር ቃል ኑና እንማከር በማለት አልቆመም፤ እሺ ብትሉ፣ ለእኔም ብትታዘዙ፣ የምድርን በረከት ትበላላችሁ፤ እንቢ ብትሉ ግን ብታምጹም ሰይፍ ይበላችኋል፤ የእግዚአብሔር አፍ ይህን ተናግሮአልና፡፡

እግዚአብሔር ለሰው ልጆች ትሕትናንና መወያየትን፣ መወቃቀስና መስማማትን ለማስተማር በነቢዩ በኢሳይያስ በኩል መልእክቱን አስተላለፈ፤ ዛሬ ይህ መልእክት ለእኛ ለኢትዮጵያውያን ይመስለኛል፤ ዛሬ ይህ የእግዚአብሔር መልእክት ለወያኔ ይመስለኛል፤ ዛሬ ይህ መልእክት ለወያኔና ለአጋሮቻቸው ይመስለኛል፡፡
በኢሳይያስ በኩል የመጣው መልእክት ግልጽ ነው፤ ምርጫው “የምድርን በረከት መብላት” ወይም በሰይፍ መበላት ነው፡፡

የምድር በረከትን በሙሉ ሁሉ በጄ ሁሉ በደጄ ላለ ጥጋብ ላይ ነውና ይበልጥ አይታየውም፤ በዕብሪት ላበጠም ስለሰይፍ ቢወራ አያስፈራውም፡፡

እግዚአብሔር ‹‹እንዋቀስ›› ካለ እኛ፣ ገዢዎቻችንም ለሰላም ሲሉ ለፍቅር ሲሉ፣ ለልጆቸው ሲሉ፣ ለአገር ሲሉ “እንዋቀስ” ቢሉ ያስከብራቸዋል እንጂ አያዋርዳቸውም፤ ታሪካቸውን ያሳምርላቸዋል እንጂ አያጎድፍባቸውም፤ መንፈሳዊ ወኔ ያላቸው፣ ልበ-ሙሉ ጀግኖች ያደርጋቸዋል እንጂ ፈሪ አያደርጋቸውም፤ አርቀው የሚያስተውሉ ብልሆች ያደርጋቸዋል እንጂ ጊዜያዊ ጮሌነት አይሆንባቸውም፡፡

ፕ/ር መስፍን ወልደ ማርያም
ግንቦት/ 2009

(ምንጭ: Mesfin Wolde-Mariam Blog)

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions, Social Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Comments

  1. Tadesse says

    April 22, 2017 12:57 pm at 12:57 pm

    Great professor.God bless You,talak sew.

    Reply
  2. Dereje says

    April 25, 2017 10:42 pm at 10:42 pm

    Hey Anta Mesfin,
    Nayi balina mist tseb meselika hagerina?

    Reply
  3. Eunetu Yeneger says

    May 4, 2017 03:01 am at 3:01 am

    ፕሮፌሰር!!!

    ለምን ከኦርቶዶክስ፣ ከካቶሊክ፣ ከፕሮቴስታንት፣ ከሙስሊምና ከቤተ እስራኤል ቤተ እምነቶች በተውጣጡ ሀገር ወዳድ ሽማግሌ የሃይማኖት መሪዎች በኩል ከኢሕአዴግና ተቃዋሚች ጋር ከልብ መወቃቀሱ አይጀመርም????

    በዚህ የምንስማማ ከሆነ እነዚህ የተባሉትን ሰዎች መጠቆሙን እንጀምር ከዚያም ለስብሰባው የሚሆነውን በኢሜል እየተነጋገርን እናዘጋጅ???
    የእኔ ኢሜል: eunethiowt@gmail.com ነውና እስቲ ፕሮፌሰር የነቢዩ ኢሳያስን መጽሐፍ ጠቅሰው ኑ እንዋቀስ ያሉትን ተግባራዊ ለማድረግ ሁላችንም ለምን ድርሻችንን ለመወጣት አንሞክርም?ረጅሙ ጉዞ በአንድ ርምጃ አይደል የሚጀመረው?

    እግዜር ያስበን
    ለሥራም ያነሳሳን

    እውነቱ ይነገር ነኝ
    ካለሁበት

    Reply
  4. John says

    June 14, 2022 01:28 am at 1:28 am

    ኢየሱስ ጌታ ነዉ።ኢየሱስ ያድናል ሲባል አታምንም።እንኪያስ ጴንጤዎች! በማለት ትንቃለህ።ዘዳግም 5፤ ዘዳግም 28:1-65።ትንቢተ ኢሳያስ 1:18 የዮሃንስ ራእይ 6:4።18: የተፃፈዉ ዛሬ ላይ በአለም የሚኖረዉ ህዝብ ሁሉ ሀጢአተኛ በመሆኑ ንስሃ ገብት ከመቅሰፍት እንዲድን እንጂ ለኢትዮጵያዉያን ብቻ የተነገረ የንስሃ አዋጅ አይደለም።የመልእክቱ ምክርና ማስጠንቀቂያ ከሲኦልና ከገሃነም እሳት ከታላቁ ሰይፍ እንድንድን ነዉ።ልክ የፍልስፍና/ቆላስይስ 2:8/ መታለል መድረክ መቆጠር የለበትም።የኢየሱስ ወንጌል በመንግስታት ሰይፍና በፈረሰኞች ብዛት አይመካም።በሰይፍ የሚነሱ በሰይፍ ይጠፋሉና ሰይፍህን ወደሰገባህ መልስ ብሎ ኢየሱስ ለጴጥሮስ የተናገረዉን መመሪያ አስታዉስ።ሰማይንና ምድርን ፍጥረትን ሁሉ በቃል ብቻ ፈጥሯል።የሰዉ ልጅን/አዳምን/የመጀመሪያዉ የህያዋን አባት ከአፈር ፈጥሯል።ከአፈር የተፈጠሩት ከአዳም አጥንት የፈጠራት የህያዋን እናት ሄዋን ብዙ ትዉልድ ወልዳለች።ችግሩ ለመናጠቅ ሲሉ ብዙዎች በቃዬን መንገድ እየሄዱ መጠፋፋታቸዉ ከክፉ ሃሳባቸዉ የተነሳ የጥፋት ባሪያዎች ሆነዋል።ገላቲያ 5

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule