• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የኢትዮጵያ ሐገራዊ ንቅናቄ ተስፋና ሥጋት!

April 12, 2017 07:26 am by Editor 1 Comment

ላለፉት ሁለት ዐሥርት ዓመታት በዘረኛው የትግሬ ነፃ አውጪ የአገዛዝ መዳፍ ሥር የታፈነውን ሕዝባችንን ወደ ነፃነትና የዴሞክራሲ ምዕራፍ ለማሸጋገር የጋራ ትግል ለማድረግ ሲሞከር ቆይቷል።

ሆኖም በእነዚህ ዘመናት ውስጥ የተፈጠሩት የፖለቲካ ኃይሎች ትብብር፣ ቅንጅት፣ ኅብረት እና ውህደት አንዱም ከዳር ሳይደርስ እንዲሁ ሲሰበሰብና ሲበተን ከርሟል። እንደ አባባልም እንደ መታወሻም “ተባበሩ ወይ ተሰባበሩ” የሚለው የዶ/ር መረራ ጉዲና መፈክር አንዱም ገቢራዊ ሳይሆን አብዛኞቹ የፖለቲካ ተቋማት በአገዛዙ ጫናና በራሳቸው ደካማ አደረጃጀት ህልውናቸው እየጠፋ ለሐገር የሚተርፍና ትውልድ የሚረከበው አንድም አግባቢ የጋራ ማዕከል ሳይመሰረት በኪሳራ የታጀቡ ዓመታትን አሳልፈናል።

ትብብር የጉልበት ምንጭ ነው።ትብብር ድልን ማቅረቢያ ዘለቄታዊና ሠላማዊ ሽግግርን ማሳለጫ መሳርያ ነው።ትብብር ከሚከሰረው የሚያተረፈው የሚበዛበት የሕዝብን አብሮነት ማጠናከርያ፣ልዩነትን ማጥበቢያና የቅራኔ ማርገቢያ ጠቃሚ ዓላማ ነው።

አበው“ድር ቢያብር አንበሣ ያስር ” እንዲሉ የተበታተነን ትግል አቀናጅቶ ለውጤት በማብቃት የትብብር አስፈላጊነት ላይ ማንም ጥያቄ ባይኖረውም ይህንን ጠቃሚ መሳርያ ተጠቅሞና ኃይልን አጠናክሮ ጠላትን ለመርታት የሚያስፈልገውን ሰጥቶ የመቀበል፣የመቻቻልና የሰለጠነ ፖለቲካዊ ባህል ባለመኖሩ በተደጋጋሚ በሕዝብ ተነሳሽነት የተገኙ ወሳኝ ድሎች የተባበረ አመራር በመጥፋቱ ለቅልበሳ ሲዳረጉ ቆይተዋል።

ባለፈው ሰሞን የተለያዩ ወገኖች በተለያየ ጽንፍ ቆመው በአወዳሽነትና በነቃፊነት በየመገናኛ ዘዴዎቹ ሲናጩ የከረሙበት የአድዋ ድል በዓል ከአሸናፊነት የስነ ልቦና ውርስነቱና ፤ የክብር ልዕልናው ባሻገር ለዓለም ጭቁን ሕዝቦች ተምሣሌት የሆነ የመተባበር ውጤታማነት ማሳያ መሆኑን “ የራስ ወርቅ አያደምቅ” እንዲሉ እኛ ባለቤቶቹ ልንጠቀምበት ባንችልም በደቡብ አፍሪካ ፀረ-አፓርታይድ ትግል እና በሠሜን አሜሪካ የቆዳ ቀለም {ጭቆናን} ለመሰባበር ያስቻለ ተምሣሌት ለመሆኑ የትግሉ ባለቤቶች የመሰከሩትን ማየት ብቻ በቂ ይሆን ነበር።

ይህን የመሰለ ታሪክ አባቶቻችን ዘር፣ ቀለም፣ፆታና የብሔር ማንነት ሳይገድባቸው በሐገር ውስጥ የነበራቸውን ልዩነት አቻችለው በተባበረ ኃይል የአውሮፓ ወራሪን አሳፍረው በመመለስ ያቆዩልንን ሐገርና ዝንተ ዓለም በዓለም ጭቁን ሕዝቦች ታሪክ እንዳበራ የሚኖረውን ታሪክ ልንመራበት ቀርቶ ልንማርበት አለመቻላችን እጅጉን ያሳዝናል።

ከዚህ የተነሳ ሊያቀራርበን የሚችለውን ትተን ዘመን የሻረው አሮጌ ታሪክ ላይ ተቸክሎ፤ ማላዘን ተቋማዊና ሕብረተሰባዊ ባህል ወደ መሆን የደረሰ እስኪመስል ድረስ በሺህ ዘመናት ውስጥ ተገንብተው የኖሩ በጎና ተወራራሽ የጋራም የተናጥልም፤ የድል፣ የአብሮነትና የመቻቻል ታሪካችን ላይ ትኩረት ሰጥተን ያንን እንደማዳበር ከመቶ አምስት ዕጅ በማይሞላው የንትርክ አጀንዳ ላይ ኃይላችንን በማዋላችን ለሕዝባዊ ውድቀትና ለሃገራዊ ኋላ ቀርነት ተዳርገን ቆይተናል።

ሕወሃት ባሰማራቸው ቅጥረኞ፤ ባዶ ዝና ያናወዛቸው ዋልጌዎ፤ በጽንፈኛ ብሄረተኞች አቀጣጣይነት በሶሻል ሚዲያው በኩል የሚራገበው አሳፋሪ፤ አደገኛና ሗላቀር የጥላቻ ቅስቀሳ ተጠናክሮ ከቀጠለ ሕብረት መፍጠር አይደለም የሰላም ተስፋም እይኖርም። ከዚህም በላይ በሃገር ውስጥ ከእለት ወደ እለት እየተባባሰ የመጣው ድህነትና የአገዛዝ ጫና ሕዝባችንን ተስፋ ቆርጦ ወደ ለየለት አመጽ ገብቶ ሁኔታው ከቁጥጥር ውጭ ከሆነ በሗላ ለሕዝቡም ሆነ ለሃገሪቷ ልንደርስ የምንችልበት እድል በቀላሉ ስለማይኖር፤ ቀኑ ሳይመሽ ባለን እድል መጠቀሙ ለሁሉም የሚበጅ ይሆናል (ሙሉውን ጽሁፍ ለማንበብ እዚህ ላይ ይጫኑ)

 

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Comments

  1. Biruk says

    April 14, 2017 01:14 pm at 1:14 pm

    እኔን ግን ከሁሉ ከሁሉ የገረመኝ አቶ ኃይለገብርኤል አያሌው ይህችን ፎቶ የለጣፋት ምን መልዕክት ለማስተላለፍ ፈልጎ እንደሆ ነው። ትልቅ ሰው ነኝ ለማለት ነው? ትልቅ ስለሆንኩ የኔ ውሎ ከፕ/ሮች ጋር ነው ለማለት ነው? በጣም የሚገርም ብቻ ነው።

    ለማንኛም ኮሜንት ልሰጥ ወደተነሳሁበት ዋናው ቁም ነግር ልግባ።

    አቶ ኃይለገብርኤል አያሌው አንተ ተስፋ የምትለው “የኢትዮጵያ ሐገራዊ ንቅናቄ ” የሚባለውና ግንቦት 7 በበላይነት ሞተር ሆኖ የሚያሽከረከረው ንቅናቄ ለአማራው ምን እንደሆነ አማራው ጠንቅቆ ያውቃል። አንት ግን ስልጣንና በየመድርኩ እየተገኘህ ስምህንና ፎቶ መንሳትን ብቻ ስለምትወድና ስለተሸፈነብህ ግንቦት 7 ስለ አማራው ያለውን አመለካከት አታውቅም። ብታውቀም ስለተሸፈነብህ አይታይህም።

    አንት አማራው ተሎ ተደራጅቶ አንተ ተስፋ የምትለውን “የኢትዮጵያ ሐገራዊ ንቅናቄ” እንዲቀላቀል ትላላል። ግንቦት 7 ግን አማራው ተሎ ተደራጅቶ እንኳን ድርጅቱን እንዲቀላልቀል ቀርቶ እራሱን ብቻውን ቆም እንዲታግል አይፈልጉም። ለዚህ ማስረጃ የሚሆነው የሚከተለውን የከንቦት 7 ከፍተኛ አመራ የሆነው አቶ አበበ ቦጋ የተናገረውን ማዳመጥ ብቻ በቂ ነው። ሙሉን ማዳመጥ ጥሩ ነው። እኔ ግን እንድታዳምጠው የምፈልገውና አንተ ለጻፍከው የአማራ መደርጃት ለሚለው ጽሁፍ ግንቦት 7 ያለውን መለካከት ብቻ እጠቅሳለሁ።

    https://www.youtube.com/watch?v=eI7ZkWy3gyo

    ከቪድዮው ከ1:21፡00 (ከ1 ሰዓት 21 ደቂቃ ጀምሮ አዳምጥ)

    የኢትዮትዮብ ጠያቂ ጋዜጠኛ ዮሴፍ፤ ግን እኮ ሻለቃ ዳዊት ወልደጊዮርጊስ በስብሰባው ላይ ተጠይቀው በአሁን ሰዓት በአማራ ስም የተደራጁ ብዝህ ድርጅቶች ስላሉ ሁሉንም መጥራት ስላቻልን ወደፊት ለብቻ ሰርተን አንደ የተጠናከረ የአማራ ድርጅት ወደ “ሐገራዊ ንቅናቄ” እናመጣለን ብለው መስልስ ሰጥተዋል። ብሎ ሲጥይቀው

    መልስ የሚሰጠው የግንቦት 7 ከፍተኛ አመራር አቶ አበበ ቦጋለ፤ እኔ ሻለቃ ዳዊትን ብሆን ኖሮ ይህ አይነት ነገር ትክክል አይደለም ብየ ነበር የምናገረ። {አማራ ተደራጅቶ ወደ ንቅናቄ ይምጣ የሚለውን ነገር አልደግፍም ማለቱ ነው። ገባህ???}

    ስለዚህ አቶ ኃይለገብርኤል አያሌው ባጭሩ አንተ አማራው ተደርጅቶ ብትፈልግም የድርጅቱ አለቃና ሞተር ግንቦት 7 አይፈቅድም ማለት ነው።

    ከዚህ ላይ ግልጽ ላደርግልህ የምፈልገው ግን አማራው ተደራጅቶ የራሱ ስራ እየሰራ ነው። የተደራጀው ግን ከማንም ጋር ተቀላቅየ ስራ እስራለሁ ብሎ ሳይሆን በወያኔ እየደርሰበት ያለውን ጥቃት ለመመክት መደራጀት ስላለበትና መመከትም ስለምችል ነው። አማራ ከሆንህ አማራ ምን ማድረግ እንደሚችል ታውቃለህ።

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am
  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm
  • የተመሠረተው የፋኖ አደረጃጀት ዋነኛ ዓላማው ድርድር መሆኑ ተነገረ May 14, 2025 11:07 pm
  • ከፍተኛ የፋኖ አመራሮች መገደላቸው ተነገረ May 6, 2025 10:40 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule