ከጅብ ከበሮ የተሰራ አታሞ ዘወትር እንብላው፤ እንብላው ይላል የሚል ተረት ሰምቻለሁ ልበል? አዎ፤ ሳልሰማ አልቀርም። ሀሳቡም ግን ጅብ ቆዳ ሆኖ እንኳን (ቆዳ ሆኖ ብቻ አይደለም አታሞ ተለጉሞበትም) ያው የተፈጥሮ እንብላ ባይ ባህሪውን አይተውም ማለት ይመስለኛል። ያው ቢሞትም ቆዳው የጅብ ነዋ። ይህን ምሳሌ ያስታወሰኝ የሰሞኑ የአምስት የዖሮሞ ድርጅቶች ያወጡት ጠብ ያለሽ በዳቦ አይነት መግለጫ ነው። በእርግጥ የኢትዮጵያ የፖለቲካ ድርጅቶች አይነተኛ ተግባር ምናልባትም ቋሚ ስራ መግለጫ ማውጣት ስለሆነ ድርጅቶቹ ያው እንደለመደው ሰብሰብ ብለው እስቲ መግለጫ እናውጣ ቢሉ ያባት ይባል ነበር። የነዚህኞቹ ግን የዘር አዋጅ እንጂ መግለጫ የሚባል ስላልሆነ በእውነቱ በጥብቅ የሚያነጋግርም የሚያስተዛዝብም ምናልባትም ደግሞ ህግ ካለም በህግ የሚያስጠይቅ ግዴለም አቅልለን እንመልከተው ካልን ደግሞ … [Read more...] about የጠብ ሱስ
Opinions
የኔ ሃሳብ
የክልሎች የመሬት ቅርምት እና ትውልድ አምካኝ የትምህርት ፓሊሲ
1) መነሻ እውነታዎች፤ በዚህ ቋንቋን መሰረት ባደረ የጎሳ ፌዴራል ስርዓት፦ (ሀ) ጊዜ ያነሳቸው ባለጉልበቶች በጎሳና በቋንቋ ተቧድነው የኢትዮጵያን ህዝብ የጋራ መሬትና የተፈጥሮ ሃብትን ኢፍትሃዊ በሆነ መንገድ አግበስብሰው በመያዝ ከዚህ መስመር አትለፍ፣ ይህ የኔ ክልል ነው አንተን አይመለከትህም፣ መጤዎች ከክልላችንን ለቃችሁ ውጡ፣ መሬቱን እንፈልገዋለን ወደ ሃገራችሁ ሂዱ እያሉ የሃገሪቷን ዜጎች ተወልደው ካደጉበት፣ አድገው ከተዳሩበት፣ ወልደው ከከበዱበት ከሃገራቸው ላይ እንደ ዋዛ ቤተስብ በሚያፈርሱበትና በሚያፈናቅሉበት፣ በተለይም አንዱ የሃገር ባለቤትና አፈናቃይ ሌላው በሃገሩ ላይ ባዳና ሁለተኛ ዜጋ በሆነበት ሁኔታ፣ (ለ) ጥቂቶች የሃገርን ሃብትን ዘርፈውና የንፁሃንን ደም አፍሰው፣ በየእስር ቤቱ ዜጎችን ቶርቸር እያደረጉና እያሰቃዩ ከህግ በላይ ሆነው ሰውንም እግዚአብሔርን … [Read more...] about የክልሎች የመሬት ቅርምት እና ትውልድ አምካኝ የትምህርት ፓሊሲ
“በመንግስት አመራር ውስጥ ‘እኔ አውቅላችኋለሁ’ የሚል ደዌ ተጠናውቶን ቆይቷል” አቶ ገዱ አንዳርጋቸው
ገዱ አንዳርጋቸው በምሁራን መድረክ ያድረጉት የመክፈቻ ንግግር ክቡር አቶ ደመቀ መኮንን የኢፌድሪ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር የተከበራችሁ ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች! እንኳን ወደ አማራ ክልል መዲና ውቢቷ ባህርዳር ከተማ በሠላም መጣችሁ! ከነገሬ ሁሉ በማስቀደም የአማራ ክልል መንግስት እና ህዝብ የጐደለውን ትሞሉለት ዘንድ ምክራችሁን እና የሙያ ድጋፋችሁን በመሻት ለልጆቹ ያደረገውን ይህን ታሪካዊ ጥሪ ያለምንም ማቅማማት ተቀብላችሁ እዚህ በመካከላችን በመገኘታችሁ ከልብ የመነጨ ምስጋና አቀርባለሁ። በረጅሙ የሃገራችን ኢትዮጵያ ታሪክ ውስጥ የአማራ ህዝብ በስልጣኔ፣ በተለይም በመንግስት አስተዳደር፣ በታሪክ፣ በኪነ-ጥበብ፣ በስነ-ፅሁፍ፣ በአርበኝነት ተጋድሎ እንዲሁም በኢኮኖሚ ዕድገት ለሃገር ያበረከተው ድርሻ ትልቅና አይረሴ ቢሆንም ያለፈው ግማሽ ምዕተ-ዓመት … [Read more...] about “በመንግስት አመራር ውስጥ ‘እኔ አውቅላችኋለሁ’ የሚል ደዌ ተጠናውቶን ቆይቷል” አቶ ገዱ አንዳርጋቸው
Abiy lamented about the country’s lack of project management competency in his first press release
I've not yet watched the Press Release (PR) Abiy gave this morning. However, I was given a short clip taken from the PR where he was talking about why mega projects are failing in Ethiopia. He is right on the money. He pinpointed the culprit - the country's lack of capacity to implement the principles of Project Management. This is not the first time he was lamenting about it. A couple of months ago, I remember Abiy talking to the business community where he emphasized the need to build the … [Read more...] about Abiy lamented about the country’s lack of project management competency in his first press release
“ብአዴን ራሱን የማጥራት እንቅስቃሴውን አጠናክሮ ይቀጥላል” የብአዴን ማዕከላዊ ኮሚቴ
የብሄረ አማራ ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ (ብአዴን) ማዕከላዊ ኮሚቴ ነሃሴ 17 እና 18 ቀን 2010 ዓ.ም ለሁለት ቀናት ባካሄደው መደበኛ ስብሰባ በብአዴን 12ኛ መደበኛ ድርጅታዊ ጉባኤ ረቂቅ ሪፖርትና ለጉባዔው በሚቀርቡ ሌሎች ወቅታዊና መደበኛ ጉዳዮች ላይ ተወያቶ የተለያዩ ውሳኔዎችን አሳልፏል፡፡ የብአዴን 12ኛ ድርጅታዊ ጉባኤ በህዝቡ ሁለንተናዊ ተሳትፎና ባለቤትነት በሀገር ደረጃና ብአዴን በሚመራው የአማራ ክልል የተጀመረውን የለውጥ ጉዞ አጠናክሮ ለማስቀጠል ወሳኝና ታሪካዊ ጊዜ ላይ የሚካሄድ መሆኑን ታሳቢ በማድረግ ድርጅቱ የመሪነት ሚናውን ከምንጊዜውም በላይ አጠናክሮ ለማስቀጠል የሚያስችሉ አቅጣጫዎችና ውሳኔዎች ለጉባኤው እንዲቀርቡ ጥልቀት ያለው ውይይት ካካሄደ በኋላ በጉባዔ አጀንዳዎችና በሌሎች ጉዳዮች ስምምነት ላይ በመድረስ የሚከተሉትን ውሳኔዎች አስተላልፏል፡፡ በመቀጣጠል … [Read more...] about “ብአዴን ራሱን የማጥራት እንቅስቃሴውን አጠናክሮ ይቀጥላል” የብአዴን ማዕከላዊ ኮሚቴ
ኢትዮጵያ ድምፅ ሬድዮ 25ኛ አመት
ከስዊድን ሃገር የሚሰራጨዉ የኢትዮጵያ ድምፅ ሬድዮ የተመሰረትበትን 25ኛ አመት ካድማጭ ወዳጆቹ ጋር ለማክበር ዝግጂቱን በሰፊዉ እያከናወነ ይገኛል። ሁላችሁም ታድማችኋል። “ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ። ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው። … [Read more...] about ኢትዮጵያ ድምፅ ሬድዮ 25ኛ አመት
ተአምረ ኦሮሞ ወአማራ
ፍቅሬ ቶሎሳ ራሱን ከማናቸውም የጎሣ ቆዳ ገሽልጦ ወጥቶ፤ መጨረሻውን በቅጡ ሳያውቅ ከሀረር ተነሥቶ በአሜሪካ ዞሮ ኢትዮጵያ ገባ፤ በሁለት እጆቹ ኦሮሞንና አማራን በጋማቸው ይዞ አዛመዳቸው፤ የፍቅሬ ቶሎሳ ሀሳብ፣ እምነት፣ ሕልም (አንዳንዶች ቅዠት ይሉታል፤) ገና ባልታወቀ መለኮታዊ መንገድ ዞሮ ዞሮ ለማና ዓቢይ የሚባሉ ሰዎችን ያፈራ የኢትዮጵያ መሬት ላይ አረፈ፤ የኢትዮጵያን መሬት ከሰሜን እስከደቡብ፣ ከምሥራቅ እስከምዕራብ ነዘረው፤ ለማና ዓቢይ የሚባሉትን ሁለት ኢትዮጵያውያን ከአንድ መቶ ሚልዮን ሕዝብ መሀል ነቅሶ አውጥቶ አንቀረቀባቸው፤ ለማንና ዓቢይን አንቀርቅቦ አወጣና አንድ አደረጋቸው! ዘር፣ ፖሊቲካ፣ ጥቅም፣ ሥልጣን፣ ጉልበት ወይም ሀብት አይደለም፤ እግዚአብሔር በረቂቅ ጥበቡ ፍቅሬን ከአሜሪካ ለማንና ዓቢይን እነሱ በማያውቁት መንገድ አገናኝቶ፣ እነሱ ባልገባቸው መንገድ አስማምቶ … [Read more...] about ተአምረ ኦሮሞ ወአማራ
አብርሃ ደስታ ስለ ህወሓቶች፤ “አሳልፈን አንሰጣቸውም”
"አብርሃ ደስታ ሆይ!" ጃዋር በኦነግ የፊደል መማርያ ማደጉን እና አንተም በወያኔ የጥላቻ መማርያ ደብተር ማደግህን ለዛሬ የተበረዘ አስተሳሰባችሁ አስተዋጽኦ ቦኖረውም (ለዛወም ይሆናል “ኢትዮጵያ አውት ኦፍ ኦሮሚያ” ብሎ ጃዋር ሲል ፖለቲካው ይመቸኛል ያልከው) ትንሽ ስታድግ አክራሪ ብሔረተኛነትክን ትንሽም ቢሆን ማሻሻል ነበረብህ። ሆኖም ፈቀቅ አላልክም። አፈር በል! በፖለቲካው እየሸበትክ ስትመጣ “ሰከን ስትል” የኋለ ኋላ የምትናገራቸው ነገሮች መልሰው ይከነክኑሃል። አብርሃ ደስታ ዞሮ ዞሮ የወያኔ ጀሌ ነው እያልን ስንናገር፤ ብዙ ሰዎች አላመኑም ነበር። ጀሌ ማለት የግድ አባል መሆን ማለት አይደለም። ድሮ የተከናነበበትን ማጃጃያ ነጠላውን ጥሎ ዛሬ በግልጽ ስለወያኔዎች ወንጀለኞች ጥብቅና ቆሞ እየተከራከረ ነው። ድሮም ዛሬም ከወያኔ የተደመረ እንጂ ከወያኔ የተለየ ሰው አልነበረም … [Read more...] about አብርሃ ደስታ ስለ ህወሓቶች፤ “አሳልፈን አንሰጣቸውም”
አሸንዳ/ሻደይ ከሰሜን ኢትዮጵያ እስከ ደቡብ ኤርትራ የሚከበር “የጋራ ጸጋና ህዝባዊ በረከት እንጂ የምንጣላበት፣ እንደ አላቂ ሃብት በድርሻ-ድርሻ የምንካፈለው አይደለም” ጠ/ሚ/ር ዐቢይ
አሸንዳ/ሻደይ/አሸንድየ የሰሜን ኢትዮጵያ ህዝቦች የአንድነትና የወንድማማችነት ህያው ማስረጃ! በሁሉም አቅጣጫ ያሉትን የሃገራችንን ህዝቦች እንዳይበታተኑ ያስተሳሰሩ፤ እንዳይለያዩ ያጣመሩ፣ እንዳይፈርሱ ያማገሩ በርካታና ጠንካራ ማጎች በሀገራችን ሁሉም ጫፎች በክብር እና በፍቅር እዚም እዚያም አሉ። ህዝቦቻችን በጋብቻ ተዛምደው፣ በማንነት ተዋህደው የኖሩ፣ ያሉና የሚኖሩ ህዝቦች ናቸው። ልክ እንደ ምስራቁ፣ ደቡቡና ምእራቡ ህዝባችን ሁሉ የሰሜን የሃገራቸን ህዝቦችም በባህል፣ በቋንቋ፣ በዘር፤ በሃይማኖት ወዘተ ተሰናስልው፤ ተዋደውና ተዋህደው የኖሩ፣ ያሉና የሚኖሩ ስለመሆናቸው በርካታ የታሪክ፣ የባህል፤ የእምነት እና የቋንቋ ማስረጃዎች ማቅረብ የሚያስፈልገው ሁነት ሳይሆን በህይወታቸው ውስጥ ከተረበረቡ እልፍ መገለጫዎቻቸው የሚስተዋል ግሩም እውነት ነው። የዚህ አንድነትና የጋራ ማንነት- … [Read more...] about አሸንዳ/ሻደይ ከሰሜን ኢትዮጵያ እስከ ደቡብ ኤርትራ የሚከበር “የጋራ ጸጋና ህዝባዊ በረከት እንጂ የምንጣላበት፣ እንደ አላቂ ሃብት በድርሻ-ድርሻ የምንካፈለው አይደለም” ጠ/ሚ/ር ዐቢይ
የመንጋ ፍትሕ እና የጠቅላይ ሚኒስትሩ መግለጫ
የመንጋ ፖለቲካ እና የመንጋ ፍትሕ የትም ሃገር ሊከሰት የሚችል ነገር ነው። ተከስቶም ያውቃል። የዘርፉ ባለሙያዎች ዋነኛ ምክንያቱ "በተቋማት እና በመንግሥት የተቆጣ ሕዝብ፣ ከምሬት እና ከቁጭት የተነሳ ለውጥ ፈላጊ ሕዝብ በሥሜት የሚወስደው በቀል አዘል "የፍትሕ ጥያቄ" ነው" ይሉታል። በዚያ መልኩ ስንረዳው መፍትሔው ቀላል ይሆናል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ የመንጋ ፖለቲካውን እና የመንጋ ፍትሕን በዋነኛነት በሕዝብን ይሁኝታ (ለመልካም እሴት በመገዛት) እና የጸጥታ ኃይሉ በሚወስደው እርምጃ ብቻ ለመቆጣጠር ማሰባቸው ግን ሙሉ አይመስለኝም። ነፃነትል መሸከም አለመቻል አድርጎ መሳላቸውም አልተመቸኝም። ብዙ ትክክለኛ ጥያቄዎች "በመንጋው" ተነስተዋልና። ይልቁንስ ሕዝቡ በለውጡ ላይ ከፍተኛ ተስፋን በመጣሉ ዝቅተኛው ካድሬ እና የአስተዳደር አካል ሕዝቡ የሚፈልገውን ለማድረግ አለመቻሉ ነው። … [Read more...] about የመንጋ ፍትሕ እና የጠቅላይ ሚኒስትሩ መግለጫ










