• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የመንጋ ፍትሕ እና የጠቅላይ ሚኒስትሩ መግለጫ

August 20, 2018 05:25 am by Editor Leave a Comment

የመንጋ ፖለቲካ እና የመንጋ ፍትሕ የትም ሃገር ሊከሰት የሚችል ነገር ነው። ተከስቶም ያውቃል።  የዘርፉ ባለሙያዎች ዋነኛ ምክንያቱ “በተቋማት እና በመንግሥት የተቆጣ ሕዝብ፣ ከምሬት እና ከቁጭት የተነሳ ለውጥ ፈላጊ ሕዝብ በሥሜት የሚወስደው በቀል አዘል “የፍትሕ ጥያቄ” ነው” ይሉታል።
በዚያ መልኩ ስንረዳው መፍትሔው ቀላል ይሆናል።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ የመንጋ ፖለቲካውን እና የመንጋ ፍትሕን በዋነኛነት በሕዝብን ይሁኝታ (ለመልካም እሴት በመገዛት) እና የጸጥታ ኃይሉ በሚወስደው እርምጃ ብቻ ለመቆጣጠር ማሰባቸው ግን ሙሉ አይመስለኝም። 

ነፃነትል መሸከም አለመቻል አድርጎ መሳላቸውም አልተመቸኝም። ብዙ ትክክለኛ ጥያቄዎች “በመንጋው” ተነስተዋልና። ይልቁንስ ሕዝቡ በለውጡ ላይ ከፍተኛ ተስፋን በመጣሉ ዝቅተኛው ካድሬ እና የአስተዳደር አካል ሕዝቡ የሚፈልገውን ለማድረግ አለመቻሉ ነው። በዚህ ረገድም የፍትሕ ሥርዓቱ መሉ በሙሉ የፍትሕ ሥራን ሠርቶ ሕዝብን አገልግሏል ለማለት አያስደፍረም።

የመንጋ ፍትሕ ሌላ ምክንያቱ የዳሸቀ የፍትሕ አካላት ቅቡልነት እና ተዓማኒነት እንደሆነ ይገለፃል። (ሌላ ምክንያት ሊኖረው እንደሚችል ቢታወቅም)

ለረጅም አመታት የፖለቲካ ድርጅት ጠበቃ የነበረው የፍትሕ ዘርፉ አሁንም አንድም የተጠያቂነት አሠራርን ሳያሰፍን (ቢያንስ የፖለቲካ እስረኞችን ሙሉ በሙሉ ሳይፈታ፣ የማጎሪያ ቤት አሰቃይ የነበሩ ባለሥልጣናት ላይ ምንም ምርምራ ሳያደርግ) እንዴት ቅቡል እና ተዓማኒ ይሆናል፤ ሕዝቡስ እንዴት “የኔ ፍትሕ ሰጪ” ብሎ ይወሰደው?

Securitization and appealing to unbridled and unprincipled “forgiveness” will be inadequate. Appropriately recognizeing popular demand and making more delivery accordingly is a necessity. 

በሌላ በኩል የመንጋ ፍትሕ ተጨባጭ ምንክያት ዝቅተኛው ካድሬ አለመታደሱ (“አለመደመር”) ነው። ሙሰኛ ዞን እየቀተቀየረለት መሾሙ ነው። ከፍተኛው የሙስና አባቶችም “አለመደመር” ነው። ….…መደመር ማለቴ መቀነስ።

በሌላ በኩል ግን ጥሩ መልዕክት ነው…ሁለት ነጥቦችን ልጨምር.

፩. የጥንት የመልካም እሴቶች እና ሥነ መንግሥት እንደነበሩን ገልጸው ነበር። እጅግ በጣም ጥሩ ነው። ግን እነዚህ እሴቶች እና ሃገር በቀል የሆኑ የመንግሥት ሥርዓቶችን አንኮታኩተው ያደከሙት እና አንዴ ፊውዳል ሌላ ጊዜ ኮሚዩኒኒዝም፣ ሶሻሊዝም እና ካፒታሊዝም (ዴሞክራቲክ ዴቬሎፕመንታል ስቴት LOL) እያሉ ሀገሩን ወደ “STATE” ማሳደግ እንኳን ያቃታቸው ይዚሁ ሃገር ፖለቲከኞች ናቸው (ኢሕአዴግን ጨምሮ)።

፪. “አንድ የፖለቲካ እና የኢኮኖሚንማኅበረሰብን መፍጠር” ያሉትን ሰማሁት። ይህ ሐረግ በሕገ መንግሥቱ መቅድም ላይ የሚገኝ ሲሆን ኢትዮጵያ የብሔር ብሔረሰቦች እና ሕዝቦች የቡድን እና የግል መብት ተከብረውላቸው፣ የጋራ ጥቅም ተከብረውላቸው፣ ሠላም እና ዴሞክራሲ የሠፈነበት ሀገርን በጋራ መመሥረትን እንዲህ ብሎ ይገልፃል
” .….መጪው የጋራ ዕድላችን መመስረት ያለበት ከታሪካችን የወረስነውን የተዛባ ግንኙነት በማረምና የጋራ ጥቅማችንን በማሳደግ ላይ መሆኑን በመቀበል…. ”
የሕገ መንግሥት ባለሙያ ስላልሆንኩ ብዙም አስተያየት ባልችልም ግን ባለፉት 27 ዓመታት በዚህ ረገድ ምንል እንዳልተሠራ ለመናገር አሁን ያለንበት እርስበርስ ያለን ጥላቻ፣ መነቋቆር፣ መገዳደል ማየቱ በቂ ነው።

ምን ለማለት ፈልጌ ነው?

“አንድ የፖለቲካ እና የኢኮኖሚ ማኅበረሰብ”…ወይም በቀላሉ STATE ለመገንባት ብዙ ርቀት ይቀረናል…የጠቅላይ ሚኒስትሩም ትልቅ ፈተና እንደሚሆን አስባለሁ። 

Tactical Alliances (ካለ LOL)  ወደ strategic integration ይደጉ፤ እንትግሬሽንም አቃፊ ይሁን፣ ኢኮኖሚው ይነቃቃ፣ የሥራ ዕድል ይፈጠር፣ ያኔ መንጋ በሥራ ይጠመዳል (የፌስቡክ መንጋንም ጨምሮ)።
ግን ግን ቆይ የሕዝባዊ አመጹ ዋነኛ ጥያቄ ምን ነበር?

(እኔ ራሴው እንዳልረሳው ለማስታወስ ያህል ነው እንጅ እርስዎ “ጊዜ” ብለዋል)።

ከምንም በላይ ግን ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ሆይ  ኢሕአዴግን ማስተዳደር፣ መለወጥ ይቅናዎት። ካልሆነም እሱ ግትር ሆኖ አልቃና ብሎ ሲሰበር ኢትዮጵያን አደራ።

መንግሥቱ አሰፋ ነኝ

መልካም ቆይታ

(ፎቶ፤ የመንጋ ፍትሕ በታንዛኒያ ለማሳያ የቀረበ)


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ። ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው።

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የሲኖዶሱ ውዝግብ አካሄድና መጪው የአፍሪካ ኅብረት ጉባዔ February 6, 2023 02:03 am
  • የእሁዱ ሰላማዊ ሰልፍ ተራዘመ፤ ተጠባቂው ዕርቅ ፍንጭ እያሳየ ነው February 3, 2023 05:17 pm
  • የብላቴ: የውጊያ ማርሽ ቀያሪ ሠራዊት መፍለቂያ ማዕከል February 3, 2023 10:06 am
  • በኢትዮጵያ 27 በመቶ የሚሆነው የአእምሮ በሽተኛ ነው ተባለ February 3, 2023 09:47 am
  • “አስደንጋጭ”! 1 ሚሊዮን ከሚጠጋ ተፈታኝ ተማሪ ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገባው 30 ሺህ (3.3%) ብቻ ነው  January 27, 2023 09:11 am
  • የማይዘነጋዉ የኢትዮጵያዊያኖች የጀግንነት ተጋድሎ ታሪክ፡- ኮሎኔል ባጫ ሁንዴ (ታጠቅ) January 27, 2023 06:12 am
  • ጎርጎራ – የመጻዒው ዘመን ሙሽራ! የዉበት ፈርጥ! January 17, 2023 04:18 pm
  • ሁለተኛው መስቀል አደባባይ January 17, 2023 04:13 pm
  • በአቡዳቢ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን January 17, 2023 04:08 pm
  • በንፋስ ስልክ ላፍቶ ስምንት የመሬት ሌቦች ተያዙ January 16, 2023 11:36 am
  • ሺሻ ሲያስጨሱ በተገኙ ሆቴሎችና የምሽት ጭፈራ ቤቶች ላይ እርምጃ ተወሰደ January 16, 2023 08:50 am
  • በሐሰተኛ መታወቂያ የደኅንነት አባል ነን ብለው ሲያጭበረብሩ የነበሩ ተያዙ January 13, 2023 02:03 pm
  • ተሽከርካሪ ወንበር ለትግራይ – “ናይ ኣካል ጉዱኣት ተሽከርካሪ ዘለዎ ወንበር” January 12, 2023 07:17 pm
  • የአማራው ኩራት፣ የኢትዮጵያ ዘብ፣ የትህነግን ቅስም ሰባሪ! January 12, 2023 04:00 pm
  • በኢትዮጵያ ላይ የተጣሉ ማዕቀብ እና ሌሎች አስገዳጅ ሕጎች ሙሉ ለሙሉ ተሰረዙ January 12, 2023 01:52 pm
  • የቻይና ዕዳ ስረዛ “Payday Loan Diplomacy” ወይስ ኢትዮጵያን ያዳነ ተግባር? January 12, 2023 11:00 am
  • የአዲስ አበባ አስተዳደር ከቋንቋ ጋር በተያያዘ ውሳኔ አስተላለፈ January 12, 2023 10:46 am
  • “አምባሳደሩ” የቀድሞ ጌቶቻቸውን እንዲያቋቁሙ ተሾሙ January 11, 2023 03:47 pm
  • መከላከያ ሸኔን የሚዋጉ ሚሊሻዎችን አሠልጥኖ አስመረቀ January 10, 2023 05:37 pm
  • በሰባት ተጠርጣሪዎች ላይ ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመሰረተ January 10, 2023 03:36 pm
  • የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ አቅጣጫ January 6, 2023 03:26 pm
  • “ከዕብሪቱ አስተንፍሰነዋል” – ኢሳያስ January 2, 2023 07:29 pm
  • [ኢትዮጵያን] “አስታክኮ ኤርትራን መውጋት ለሚፈልግ ኃይል አንተባበርም” January 2, 2023 07:11 pm
  • የ፰ ወር ሕጻንና ጨቅላ ወንዶች የሚደፈሩባት ትግራይ December 14, 2022 02:49 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule