• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የመንጋ ፍትሕ እና የጠቅላይ ሚኒስትሩ መግለጫ

August 20, 2018 05:25 am by Editor Leave a Comment

የመንጋ ፖለቲካ እና የመንጋ ፍትሕ የትም ሃገር ሊከሰት የሚችል ነገር ነው። ተከስቶም ያውቃል።  የዘርፉ ባለሙያዎች ዋነኛ ምክንያቱ “በተቋማት እና በመንግሥት የተቆጣ ሕዝብ፣ ከምሬት እና ከቁጭት የተነሳ ለውጥ ፈላጊ ሕዝብ በሥሜት የሚወስደው በቀል አዘል “የፍትሕ ጥያቄ” ነው” ይሉታል።
በዚያ መልኩ ስንረዳው መፍትሔው ቀላል ይሆናል።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ የመንጋ ፖለቲካውን እና የመንጋ ፍትሕን በዋነኛነት በሕዝብን ይሁኝታ (ለመልካም እሴት በመገዛት) እና የጸጥታ ኃይሉ በሚወስደው እርምጃ ብቻ ለመቆጣጠር ማሰባቸው ግን ሙሉ አይመስለኝም። 

ነፃነትል መሸከም አለመቻል አድርጎ መሳላቸውም አልተመቸኝም። ብዙ ትክክለኛ ጥያቄዎች “በመንጋው” ተነስተዋልና። ይልቁንስ ሕዝቡ በለውጡ ላይ ከፍተኛ ተስፋን በመጣሉ ዝቅተኛው ካድሬ እና የአስተዳደር አካል ሕዝቡ የሚፈልገውን ለማድረግ አለመቻሉ ነው። በዚህ ረገድም የፍትሕ ሥርዓቱ መሉ በሙሉ የፍትሕ ሥራን ሠርቶ ሕዝብን አገልግሏል ለማለት አያስደፍረም።

የመንጋ ፍትሕ ሌላ ምክንያቱ የዳሸቀ የፍትሕ አካላት ቅቡልነት እና ተዓማኒነት እንደሆነ ይገለፃል። (ሌላ ምክንያት ሊኖረው እንደሚችል ቢታወቅም)

ለረጅም አመታት የፖለቲካ ድርጅት ጠበቃ የነበረው የፍትሕ ዘርፉ አሁንም አንድም የተጠያቂነት አሠራርን ሳያሰፍን (ቢያንስ የፖለቲካ እስረኞችን ሙሉ በሙሉ ሳይፈታ፣ የማጎሪያ ቤት አሰቃይ የነበሩ ባለሥልጣናት ላይ ምንም ምርምራ ሳያደርግ) እንዴት ቅቡል እና ተዓማኒ ይሆናል፤ ሕዝቡስ እንዴት “የኔ ፍትሕ ሰጪ” ብሎ ይወሰደው?

Securitization and appealing to unbridled and unprincipled “forgiveness” will be inadequate. Appropriately recognizeing popular demand and making more delivery accordingly is a necessity. 

በሌላ በኩል የመንጋ ፍትሕ ተጨባጭ ምንክያት ዝቅተኛው ካድሬ አለመታደሱ (“አለመደመር”) ነው። ሙሰኛ ዞን እየቀተቀየረለት መሾሙ ነው። ከፍተኛው የሙስና አባቶችም “አለመደመር” ነው። ….…መደመር ማለቴ መቀነስ።

በሌላ በኩል ግን ጥሩ መልዕክት ነው…ሁለት ነጥቦችን ልጨምር.

፩. የጥንት የመልካም እሴቶች እና ሥነ መንግሥት እንደነበሩን ገልጸው ነበር። እጅግ በጣም ጥሩ ነው። ግን እነዚህ እሴቶች እና ሃገር በቀል የሆኑ የመንግሥት ሥርዓቶችን አንኮታኩተው ያደከሙት እና አንዴ ፊውዳል ሌላ ጊዜ ኮሚዩኒኒዝም፣ ሶሻሊዝም እና ካፒታሊዝም (ዴሞክራቲክ ዴቬሎፕመንታል ስቴት LOL) እያሉ ሀገሩን ወደ “STATE” ማሳደግ እንኳን ያቃታቸው ይዚሁ ሃገር ፖለቲከኞች ናቸው (ኢሕአዴግን ጨምሮ)።

፪. “አንድ የፖለቲካ እና የኢኮኖሚንማኅበረሰብን መፍጠር” ያሉትን ሰማሁት። ይህ ሐረግ በሕገ መንግሥቱ መቅድም ላይ የሚገኝ ሲሆን ኢትዮጵያ የብሔር ብሔረሰቦች እና ሕዝቦች የቡድን እና የግል መብት ተከብረውላቸው፣ የጋራ ጥቅም ተከብረውላቸው፣ ሠላም እና ዴሞክራሲ የሠፈነበት ሀገርን በጋራ መመሥረትን እንዲህ ብሎ ይገልፃል
” .….መጪው የጋራ ዕድላችን መመስረት ያለበት ከታሪካችን የወረስነውን የተዛባ ግንኙነት በማረምና የጋራ ጥቅማችንን በማሳደግ ላይ መሆኑን በመቀበል…. ”
የሕገ መንግሥት ባለሙያ ስላልሆንኩ ብዙም አስተያየት ባልችልም ግን ባለፉት 27 ዓመታት በዚህ ረገድ ምንል እንዳልተሠራ ለመናገር አሁን ያለንበት እርስበርስ ያለን ጥላቻ፣ መነቋቆር፣ መገዳደል ማየቱ በቂ ነው።

ምን ለማለት ፈልጌ ነው?

“አንድ የፖለቲካ እና የኢኮኖሚ ማኅበረሰብ”…ወይም በቀላሉ STATE ለመገንባት ብዙ ርቀት ይቀረናል…የጠቅላይ ሚኒስትሩም ትልቅ ፈተና እንደሚሆን አስባለሁ። 

Tactical Alliances (ካለ LOL)  ወደ strategic integration ይደጉ፤ እንትግሬሽንም አቃፊ ይሁን፣ ኢኮኖሚው ይነቃቃ፣ የሥራ ዕድል ይፈጠር፣ ያኔ መንጋ በሥራ ይጠመዳል (የፌስቡክ መንጋንም ጨምሮ)።
ግን ግን ቆይ የሕዝባዊ አመጹ ዋነኛ ጥያቄ ምን ነበር?

(እኔ ራሴው እንዳልረሳው ለማስታወስ ያህል ነው እንጅ እርስዎ “ጊዜ” ብለዋል)።

ከምንም በላይ ግን ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ሆይ  ኢሕአዴግን ማስተዳደር፣ መለወጥ ይቅናዎት። ካልሆነም እሱ ግትር ሆኖ አልቃና ብሎ ሲሰበር ኢትዮጵያን አደራ።

መንግሥቱ አሰፋ ነኝ

መልካም ቆይታ

(ፎቶ፤ የመንጋ ፍትሕ በታንዛኒያ ለማሳያ የቀረበ)


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ። ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው።

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Opinions Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የአየለ ጫሚሶ ቅንጅት ፈረሰ January 18, 2021 02:31 pm
  • ህወሓት ተሠረዘ!!! January 18, 2021 01:32 pm
  • ዓሲምባ፣ ሣልሳዊ ወያኔና ባይቶና ከመፍረሳቸው በፊት ማብራሪያ እንዲሰጡ ተነገራቸው January 18, 2021 01:00 pm
  • ቤተሰቦች አስከሬን መውሰድ እንደሚችሉ ተነገረ January 14, 2021 06:48 pm
  • ስብሃት፤ “ከሞትን ቆይተናል፤ … አሁን የቀብር ሥነ-ስርዓታችን” እየተፈጸመ ነው January 14, 2021 01:37 pm
  • “ተመልሰን እንነሳለን” ያሉት ህወሓቶች ተመልሰው ወደማይነሱበት ተሸኙ January 13, 2021 01:12 pm
  • አፋር ነፃ አውጪ (ኡጉጉሙን) ለመጠቀም የታቀደው የህወሃት ሤራ ከሽፏል January 13, 2021 01:10 pm
  • ህወሃትን ወደ ጅቡቲ ለማሻገር ሲሰሩ የነበሩ የአፋር ታጣቂዎች በሰላም ወደ ክልሉ ገቡ January 13, 2021 06:47 am
  • በታህሳስ ወር ብቻ ከ344 ሚሊየን ብር በላይ የኮንትሮባንድ ዕቃ ተያዘ January 13, 2021 06:10 am
  • የብልፅግና ፓርቲ ቀጣይ ፈተና ምን ሊሆን ይችላል? January 13, 2021 04:10 am
  • ለትምህርት እንዲሆነን January 11, 2021 01:20 pm
  • “ከተቀበሩበት የጃርት ጉድጓድ ነው ያወጣናቸው” መቶ አለቃ ስዩም ቱርቦ January 11, 2021 12:11 pm
  • የተደመሰሱና በቁጥጥር ሥር የዋሉ የወንበዴው አባላት ይፋ ሆነ January 7, 2021 01:16 pm
  • ዐቢይና መኮንኖቹ በመቀሌ፤ “ድሉ የመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ነው” December 13, 2020 02:36 pm
  • ወንበዴው ህወሓት ከ1.4 ትሪሊዮን ብር በላይ ዘርፎ በውጭ አገራት ባንኮች አስቀምጧል December 8, 2020 01:05 am
  • ማይካድራ – የትህነግ የዘር ማጥፋት ጥግ ቋሚ ምስክር December 8, 2020 12:57 am
  • የወልቃይት ጠገዴ እናቶች ሰቆቃ ሲታወስ December 8, 2020 12:50 am
  • የደብረጽዮን ዋሻ December 7, 2020 11:30 pm
  • ባለ ከዘራው ኮሎኔል December 7, 2020 05:15 pm
  • ሰላማዊ ሕይወት በማይጨው December 7, 2020 04:12 pm
  • ተጠርጣሪ የፌዴራልና የአዲስ አበባ ፖሊሶች የመያዣ ትዕዛዝ ወጣባቸው December 7, 2020 11:46 am
  • ከ3 ሺህ በላይ ተተኳሽ ጥይቶች በወልዲያ ጉምሩክ ሊያሳልፉ የሞከሩ 4 ግለሰቦች ተያዙ! December 7, 2020 11:18 am
  • ወንበዴዎቹ ይጠቀሙባቸው የነበሩ ተሽከርካሪዎችና የግል ሰነዶቻቸው ተያዙ December 7, 2020 10:50 am
  • ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ በሶማሌ ክልል ተመሠረተ December 7, 2020 10:31 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2021 · Goolgule