የሁሉም አለቃና የበላይ የሆነውን ሕዝብ ማስደሰት ያኮራል። የሚመሩትን ሕዝብና አገር ከልብ አክብሮ መገኘት ደግሞ ከኩራትም በላይ ነው። ይህንን በኳስ ያበደ ህዝብ፣ አገሩን ከምንም በላይ የሚያፈቀር ህዝብ መወከል ደግሞ ከበጎ ታሪክነቱ በላይ ከሽልማትና ከውዳሴ በላይ ነውና የኢትዮጵያ ልጆች ኩራታችሁ ታላቅ ይሁን። መልካም ዕድል ለአምባሳደሮቻችን!! ኢትዮጵያዊነት እንዲህ የሚጣፍጥ፣ ማንም ሊወስደውና ሊበርዘው የማይችል ሃያል በረከት መሆኑን ምክንያት ሆነው ላሳዩን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን አባላት ክብር ይሁን ለማለት እንወዳለን። መልካም እድል ለአምባሳደሮቻችን ስንል በቂ ምክንያት ስላለን በፍጹም ኩራት ነው። በእግር ኳስ ፍቅር ለሚቃጠለው የኢትዮጵያ ህዝብ የደስታ ቀን ላመጣችሁ ውድ የኢትዮጵያ ልጆች የምንመኘው መልካም ምኞት ካለፉት የሰላሳ አንድ ዓመታት ውድቀት ጋር የተቀበረውን የድል … [Read more...] about ያብለጨለጨ ሁሉ ወርቅ አይደለም!!
Left Column
ወሬ ይገድላል
በጎርጎሪያኑ የቀን መቁጠሪያ ለምትገለገሉ ሁሉ መልካም አዲስ ዓመት!! በአዲሱ ዓመት ከራስ ጋር በመታረቅ፣ ከህሊናና ከእዕምሮ ባርነት በመላቀቅ፣ ከይሉንታ ጥብቆ ውስጥ በመውጣት፣አካሄድን ለማሳመር ይቻል ዘንድ የተጠቀለለውን አሮጌ ዓመት ትምህርት ማድረግ ታላቅ ጉዳይ ነው። አዲሱ ዓመት ከባከኑት ዓመታቶች ጋር ተዳምሮ እንዳያጎብጠን፣ ተስፋችንን እንዳይበላውና ወደ ከፋ የፖለቲካ መሰላቸት ውስጥ እንዳይከተን መጠንቀቅ ደግሞ ከሁሉም በላይ ወሳኝ ይመስለናልና ከከንቱና የማያንጽ ወሬው ቆጠብ፣ ከተግባሩ ጨመር እናድርግ!! ወሬ ይገድላል እንዲሉ!! ይሉኝታን እንቅበር ባለፉት ዓመታት የይሉኝታ ፖለቲካ ጉዳት አድርሷል። በይሉኝታ በመነዳት የማይረሳ ኪሳራ ተመዝግቧል። በይሉኝታ ብቻ የደረሰብን የፖለቲካ ጠባሳ ሰምበሩ በያንዳንዳችን ሰውነት ላይ ይታያል። በተፎካካሪ ፓርቲዎችና ለለውጥ በተነሱ ፓርቲዎች … [Read more...] about ወሬ ይገድላል
ስለ “አንቀጽ 39” ማንን እናመስግን?
በዋዜማ ዝግጅቶች ሲታጀብ ከርሞ፣ ቅዳሜ የተከበረውን “የብሄር ብሄረሰቦች” ቀንን አስመልክቶ የኢትዮጵያ ሬዲዮና ቴሌቪዥን የተለያዩ አስተያየት ሰጪዎችን በማሳተፍ “አንቀጽ 39 ለዘላለም ይኑር” ብሎናል። እኛም ለዚህ ውለታ ማንን ማመስገን እንዳለብን ለመጠየቅ ተገደድን። ለመልካሙና “የህዝቦች አብሮ የመኖር አለኝታ” ስለሚባለው አንቀጽ 39! የሶማሌ ብሄር አባል ናቸው። አቶ አብዱላሂ አብዱራሂም ይባላሉ። ዘጠነኛውን “የብሄር ብሄረሰቦች” ቀን አስመልክቶ አስተያየት እንዲሰጡ ተጋብዘው በቴሌቪዥን ብቅ አሉ “… አቅማችሁ ካደገ በኋላ፣ ልጆቻችሁን አስተምራችሁ አቅም ስታዳብሩ ለአንቀጽ 39 ትደርሱበታላችሁ…” እንዳሉዋቸው አቶ መለስን ጠቅሰው ተናገሩ። ትዝታቸው መሆኑ ነው። ወዲያው አቶ መለስ በወቅቱ እንገነጠላለን ያሉትን የሶማሌ ህዝቦች ሰብስበው ሲናገሩ ታዩ።እንዲህ አሉ “አስራ ዘጠኝ ዓመት … [Read more...] about ስለ “አንቀጽ 39” ማንን እናመስግን?
አሁንም የተሃድሶ ያለህ!!!
“አንድነትን ስንመሰርት በቅንጅት ወቅት ስለሰራነው ጥፋትና የፖለቲካ ስህተት የገመገምነው ነገር የለም” ዶ/ር ያዕቆብ ሃ/ማርያም አንድነት ፓርቲን ከቅንጅት ጋር በማነጻጸር ከተናገሩት፡፡ በኢትዮጵያ የተቃዋሚ ፓርቲና ድርጅቶች መዋቅራዊ ጥንካሬና ደጋፊዎቻቸውን አስተባብረው ውጤት ማስመዝገብ ያለመቻላቸው ጉዳይ አነጋጋሪ ነው። ተቃውሞ በኢትዮጵያ በፓርቲ መሪዎችና በገዢው ኢህአዴግ መካከል የሚደረግ እሰጥ አገባ ካልሆነ በስተቀር በደጋፊዎች ተሳትፎ ገዢውን ፓርቲ የማስገደድና እጁን የመጠምዘዝ ደረጃ ላይ ደርሶ ሊታይ አልቻለም። ከቅንጅት መፈራረስና ልዕልናው መክሰም ጋር የህዝብ ስሜትም አብሮ ተዳፍኗል የሚለው አስተያየት ሚዛን የደፋ የሚሆንባቸው የበዙት ለዚሁ ነው። በድርጅት ደረጃ ችግሩን ተመልክተው ስለመታደስ የሚያስቡ ስለመኖራቸው ግን ለረዥም ጊዜ አልሰማንም። በኢትዮጵያ ህዝብን ለትግልና … [Read more...] about አሁንም የተሃድሶ ያለህ!!!
ከፖለቲካ ተሃድሶ በፊት [የእውቀት] ተሃድሶ በአስቸኳይ!!
ታዋቂው የጋና ምሁር ጆርጅ አዪቴ በተደጋጋሚ እንደሚሉት ከአምባገነናዊ ስርዓት ወደ ዴሞክራሲ በሚደረገው ሽግግር የትኛውንም ዓይነት ተሃድሶ ከማድረግ በፊት ቅድሚያ ሊሰጠው የሚገባው የእውቀት ተሃድሶ ነው፡፡ ሕዝብ እንደሚገባው በእውቀት ከነቃ የዴሞክራሲና የመብቱን ጉዳይ ጠንቅቆ ስለሚያውቅ ይህንን ተከትሎ የሚከሰተው የእውቀት ተሃድሶ ወደ ፖለቲካዊ፣ ተቋማዊ፣ ሕገመንግሥታዊ፣ ኢኮኖሚያዊ፣ … ተሃድሶ ይመራል፡፡ የእውቀት ተሃድሶ ሳይደረግ ከአምባገነናዊ ሥርዓት ወደ ዴሞክራሲ የሚደረግ ሽግግር አንዱን አምባገነን በሌላ የመተካት ሂደት እንጂ ዘላቂ ለውጥ የሚያመጣ አይደለም ይላሉ፡፡ ሕዝብ የእውቀት ተሃድሶ ካካሄደ በሥልጣን ላይ ከተቀመጠው አምባገነን ያልተሻሉትን የፖለቲካ ድርጅት መሪዎች ማንነት ጠንቅቆ ማወቅ ይችላል፡፡ በፖለቲካ ብልጣብልጥነት ሊያካሂዱበት የሚችሉትን አሻጥር አስቀድሞ ያውቃል፤ … [Read more...] about ከፖለቲካ ተሃድሶ በፊት [የእውቀት] ተሃድሶ በአስቸኳይ!!
እባካችሁ ይህንን “ኢትዮጵያዊነት” አክብሩት!!
ኢትዮጵያዊነት ከአጭበርባሪነት፣ ከሸፍጥ፣ ከሴራ፣ ከኩርፊያ፣ ከበቀል፣ ከተንኮል፣ ከደባ፣ ከድብቅ ዓላማ፣ ከአድማ፣ ከባንዳነት፣ ከአቃጣሪነት፣ ከከሃዲነት፣ ከተቀጣሪነት፣ ከማወናበድ፣ በተለይም ከማስመሰለና ከተራ የፖለቲካ ንግድ በላይ መሆኑንና ማንም ሊበርዘው ቢደክምም ሊሸረሽረው የማይችለው የልብ ማህተም መሆኑን ሰሞኑን አየን። ባለፈው ሳምንት የኢትዮጵያ ብሔራዊ እግርኳስ ቡድን ድል እውን ይሆን ዘንድ ሠንደቅ ዓላማቸውን ለብሰው ሌሊቱን ሙሉ ላገራቸው ያዜሙ፣ በየቤታቸው ሆነው በጸሎት የማለዱ፣ በመላው ዓለም በየድረገጹ የመልካም የደስታ ምኞታቸውን ሲገልጹ የነበሩ፣ በዋናው የትግል ሜዳ የአገራቸውን መለያ ለብሰው ታሪኩን ያከወኑና የትግሉን ስትራቴጂ በመንደፍ ታሪክ የሰሩ ድርና ማግ ሆነው አገራቸውን አብርተዋታል። ብንዘገይም ለመላው የኢትዮጵያ እግርኳስ ቡድን አባላት፣ ለመላው የኢትዮጵያ … [Read more...] about እባካችሁ ይህንን “ኢትዮጵያዊነት” አክብሩት!!
ከሞት በፊት እውነተኛ ክብር
“… ከሁሉ አስቀድሞ ማሸነፍ የሚኖርብን በውስጣችን ያለውን ፍርሃት ነው። ለህወሃት/ኢህአዴግ ታማኝ ሊሆኑ የሚችሉት የጦርና የፀጥታ ኃይሎቹ እንዲሁም የስለላ ተቋሙ የህዝብ ድጋፍ የሌላቸው የጥቂት ዘረኞች ስብስብ በመሆኑ የሕዝብ እምቢተኝነት ሲጠናከር በቀላሉ ይመክናሉ። አመራሮቹ አስተሳሰባቸው በጣም ጠባብ፤ ብቃታቸውም እጅግ ዝቅተኛ ነው። በመሆኑም እነዚህ ኃይሎች ሁሉንም ነገር እንደተቆጣጠሩት አድርጎ ማሰብ ራስን ማዋረድ ነው። ስለዚህም መሸሽ ሳይሆን በየጊዜው ልንፈታተናቸው፣ ልንጎነትላቸውና ልንፋለማቸው ይገባል። ስለሆነም ካሁን በኋላ ሥራው ህወሃት/ኢህአዴግን ከውስጥ ሆኖ የመበታተንና የማፍረስን ሥራ ነው። የነጻነት ኃይሎችም መዋቅራቸውን በማስፋትና በርካታ ህዋሶችን በመፍጠር በትጋት እየሠሩ ይገኛሉ። የህወሃት/ኢህአዴግን የመዋቅር ስፋት በነፃነት ኃይሎች የመዋቅር ስፋት መጋፈጥ ይቻል ዘንድ … [Read more...] about ከሞት በፊት እውነተኛ ክብር
ኃይለማርያም ደሳለኝ – እንደ ዳንኤል፤ እንደ አክሊሉ ወይስ እንደ መለስ?
አገራችን ኢትዮጵያ በታሪኳ አስር የሚሆኑ ጠቅላይ ሚኒስትሮች አስተዳድረዋታል፡፡ ከእነዚህ መካከል በተለየ ሁኔታ ከሚወሱት አንዱ ጸሐፌ ትዕዛዝ አክሊሉ ሀብተወልድ ናቸው፡፡ በጣልያን ወረራ ወቅት ጠቅላይ ሚኒስትር አክሊሉ በአውሮጳ ያደረጉት ተጋድሎ እጅግ ከፍተኛ ለመሆኑ በተለያዩ ቦታዎች ሲጠቀስ የሚሰማ ነው፡፡ አርበኞቻችን በአገር ውስጥ የሕይወት መስዋዕትነት ሲከፍሉ አክሊሉ ሃብተወልድ በአውሮጳ የከፈሉት መስዋዕትነትና ኢትዮጵያን ለማዳን የሠሩት ሥራ ተጽፎ የማያልቅ ታሪካቸው ነው፡፡ ያላንዳች ማጋነን የዲፕሎማሲውን ሥራ ያለመታከት ከግብ ያደረሱት አክሊሉ ነበሩ፡፡ በተለይ “የአክሊሉ ማስታወሻ” በተባለው የራሳቸው ታሪክ በከፊል የተወሳበት መጽሐፍ ላይ የእንግሊዙ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሆር እና የፈረንሣዩ ጠ/ሚ/ር ላቫል ከኢትዮጵያ ክፍላተሃገራት አብዛኛው የሆነው ሐረር፣ ሲዳሞና ባሌን ጨምሮ … [Read more...] about ኃይለማርያም ደሳለኝ – እንደ ዳንኤል፤ እንደ አክሊሉ ወይስ እንደ መለስ?
ከመጥበብ ቅድሚያ ለ “እምዬ ኢትዮጵያ”
የኢትዮጵያ የመከላከያ ኃይል በወገኖቹ የሚፈቀር፣ የሚከበርና አስፈላጊው ሁሉ ድጋፍ የሚደረግለት የህዝብና የአገር አለኝታ ነው። ክቡር ህይወታቸውን ሳይሳሱ ላገራቸው ሲሉ አሳልፈው የሚሰጡትን ውድ የኢትዮጵያ ልጆች የምናከብራቸውና ልንከባከባቸው የሚገባው ልክ ያይናችን ብሌን ያህል ነው። “ክቡር ለውድ ኢትዮጵያዊ ሰማዕታት” ሲባል እንዲሁ መፈክር ለማለት ሳይሆን ከልባችን፣ ከውስጣችን፣ የመስዋዕትነታቸውን ክብር ከቶውንም ልንዘነጋው የሚቻለን ባለመሆኑ ነው። ሌላ ምክንያት የለውም። በቃ!! የምንኮራበት መከላከያ እንዲኖረን አጥብቀን ስለምንመኝ ያገር ኩራት የሆነው መከላከያችን በክልል፣ በዞንና በጎጥ አንሶና የተዋረደ ስብዕና ተላብሶ እንዲዋቀር ኢትዮጵያውያን አይፈቅዱም። አገራችን ከምትገኝበት የጂኦ ፖለቲካል አቀማመጥ አንጻር ብሄራዊ ስብዕና ያለው፣ ህዝብንና አገርን የሚያስቀድም የመከላከያ … [Read more...] about ከመጥበብ ቅድሚያ ለ “እምዬ ኢትዮጵያ”
ወፌ ቆመች በሉና!!
መረጃ ለአንድ ማህበረሰብ ከምንም በላይ አስፈላጊና አንገብጋቢ አጀንዳው ነው። ይህ የሚሆነው በአግባቡ ሚዛኑን ጠብቆ ሲራመድ ብቻ ነው። ስርዓት ጠብቆና በተቻለ መጠን ሙያዊ ስነምግባሩን ተከትሎ መራመድ የሚችል ሚዲያ የወደፊቱን በማየት ህብረተሰብን ያነቃል፣ ያሳስባል፣ ያዘጋጃል፣ የተለያዩ ሃሳቦችን ገደብ ሳያደርግ ያስተናግዳል። በዚህ እሳቤ ላይ ተመስርቶ ለመስራት የተስማማው የጎልጉል ኤዲቶሪያል ቦርድ በአገራችን አዲስ ዓመት ዋዜማ ለንባብ ሲውል ቀዳሚ ጥሪው ያደረገው ለመቆም የሚውተረተር ህጻን የሚበረታታበትን “ወፌ ቆመች” የሚለውን ባህላዊ ቃል ነው። ወፌ ቆመች!! ሚዲያ እንደ ንፋስ ከነፈሰና በስማ በለው ከነጎደ ስቶ ከማሳቱ በላይ ማህበረሰብን ሚዛን በሌለውና በተራ አሉባልታ በማዥጎርጎር ቀላል የማይባል የስሜት ግሽበት ያስከትላል ብለው ከሚያምኑት ክፍሎች ተርታ ራሳችንን እንመድባለን። … [Read more...] about ወፌ ቆመች በሉና!!