• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

እባካችሁ ይህንን “ኢትዮጵያዊነት” አክብሩት!!

October 22, 2012 09:52 pm by Editor 1 Comment

ኢትዮጵያዊነት ከአጭበርባሪነት፣ ከሸፍጥ፣ ከሴራ፣ ከኩርፊያ፣ ከበቀል፣ ከተንኮል፣ ከደባ፣ ከድብቅ ዓላማ፣ ከአድማ፣ ከባንዳነት፣ ከአቃጣሪነት፣ ከከሃዲነት፣ ከተቀጣሪነት፣ ከማወናበድ፣ በተለይም ከማስመሰለና ከተራ የፖለቲካ ንግድ በላይ መሆኑንና ማንም ሊበርዘው ቢደክምም ሊሸረሽረው የማይችለው የልብ ማህተም መሆኑን ሰሞኑን አየን።

ባለፈው ሳምንት የኢትዮጵያ ብሔራዊ እግርኳስ ቡድን ድል እውን ይሆን ዘንድ ሠንደቅ ዓላማቸውን ለብሰው ሌሊቱን ሙሉ ላገራቸው ያዜሙ፣ በየቤታቸው ሆነው በጸሎት የማለዱ፣ በመላው ዓለም በየድረገጹ የመልካም የደስታ ምኞታቸውን ሲገልጹ የነበሩ፣ በዋናው የትግል ሜዳ የአገራቸውን መለያ ለብሰው ታሪኩን ያከወኑና የትግሉን ስትራቴጂ በመንደፍ ታሪክ የሰሩ ድርና ማግ ሆነው አገራቸውን አብርተዋታል።

ብንዘገይም ለመላው የኢትዮጵያ እግርኳስ ቡድን አባላት፣ ለመላው የኢትዮጵያ ህዝብና አፈጣጠሩ ጤነኛ ባይሆንም ለፌዴሬሽኑ አመራሮች እንኳን ደስ አላችሁ እንላለን። በአፍሪካ ዋንጫ ብቁ ተፎካካሪ የመሆናችን ጉዳይ እንዳለ ሆኖ፣ ከሰላሳ አንድ ዓመት በኋላ ለዚህ ታላቅ ዕድል መብቃት አዲሱ ትውልድ የረሳቸውን አህጉራዊ ታሪኮቻችንን እንዲያወቅ ረድቶታልና ደስታችን ወደር የለውም። ድሉን ተከትሎ የመንግስት ባለሥልጣናትና የስፖርት ጋዜጠኞች የግል፣ የመንግስት ሳይባሉ ሲያሰሙ የነበረው ቡራ ከረዩ ግን አሳዝኖናል። ፕሮፓጋንዳው እስኪያቅለሸልሸን ድረስ ተጠይፈነዋል። ምክንያቶቻችንን እናቅርብ።

የኢትዮጵያ ስፖርት እንቅስቃሴ ከሩጫው በስተቀር ሙሉ በሙሉ ሞቷል። ሩጫው በውስን አትሌቶች ትከሻ ላይ ተንጠልጥሎ ቆይቶ የለመድነውን የአስር ሺህ ድል ሙሉ በሙሉ ማስከበር እንኳን ተስኖናል። ቤቱ በሙስናና በህገወጥ አሰራር መጠቃቀሚያ መሆኑን ጸረ ሙስና ኮሚሽን የፈረደበት ነው። ሌሎቹ ፌዴሬሽኖችም የሚወራ ዜና የላቸውም። እግር ኳሱም አንዴ ኩዴታ፣ ሌላ ጊዜ ደግሞ ብር አለን የሚሉ የአገራችን ባንኮች ቁጥር አንድ ተበዳሪዎች ጀሌ እየኮለኮሉ የሚነዱትና የሚክቡት፣ በብልሹ አሰራር፣ በሙስናና በብክነት የተመደበ ተቋም ነው።

ብሔራዊ ኦሊምፒክ ኮሚቴን ጨምሮ በአገሪቱ ያሉት ከሃያ አንድ በላይ ፌዴሬሽኖችና የስፖርት ማኅበራት ሙሉ በሙሉ የሚመሩት ስለስፖርቱ ምንም እውቀት በሌላቸው ካድሬዎችና የመንግስት ባለስልጣናት መሆኑ የአገሪቱን ስፖርት እንደገደለው በጥናት ተረጋግጦ ሳለ አሁን የተገኘውን ድል የአገሪቱ የስፖርት ፖሊሲ ውጤት ተደርጎ ለፖለቲካ ንግድ ስራ ሲውል አገር ውስጥ ያሉትም ሆኑ ከአገር ውጪ የሚገኙ ሚዲያዎች አብረው ማጫፈራቸው ያሳዝናል። ሚዲያ አብሮ ሲያብድ ጉዳቱ የከፋ ነውና እናስተውል ለማለት እንወዳለን። ቢያንስ ቢያንስ መንግስት በየመንደሩ የነበሩ የመጫወቻ ሜዳዎችን በሊዝ ጨረታ ለወዳጆቹ እየቸበቸበ ታዳጊዎችን መጫወቻ በማሳጣት አደገኛ ቦዘኔ በማለት ለአደገኛ ሱስ መዳረጉ ያስጠይቀዋል።

ደስታን መግለጽ አንድ ነገር ሆኖ ሳለ፣ ደስታው ስፖርቱ በደረሰበት ድርሽ የማይሉት የአቶ መለስ “አርቆ አሳቢነት” ውጤት እንደ ሆነ አድርጎ ኢቲቪ ማቅረቡ ከተለመደው የኢቲቪ ፕሮፓጋንዳ የተለየ ባለመሆኑ አያስገርምም። “የባንዲራ ቀን” ለማክበር በህይወት ዘመናቸው አንድ ቀን ለዚያውም ለሰላሳ ደቂቃ ስታዲየም የተገኙትን አቶ መለስን ባልዋሉበት ቦታ መሰንቀር የሙያም ስነ ምግባር አይመስለንም። ያለ ምንም ማጋነን መለስ ለስፖርቱ ካላቸው ደንታ ቢስነት አንጻር አዲስ አበባ ስታዲየም መሰቀላቸውም አግባብ አይደለም እንላለን። በተስፋ አገርና መላውን ስፖርት ቤተሰቦችን በኦርኬስትራ የሚያታልሉት የሼኽ መሃመድ ሁሴን አላሙዲን ጨምሮ!!

ላለፉት ሃያ አንድ ዓመታት ለታዳጊ ህጻናት ፕሮጀክት ስልጠና ከፊፋ የተላከ የርዳታ ብር ተዘርፏል። ሰልጣኞች ኳስና ጫማ የሚገዛላቸው በማጣት ሲበተኑ አቶ መለስም ሆኑ የስፖርት ሚኒስትሩ የፈየዱት ነገር አልነበረም። ተጠሪነቱ ለአቶ መለስ የሆነው የጸረ ሙስና ኮሚሽን አበጥሮ ያቀረበውን የውሳኔ ሃሳብ እንዲተገበር አላደረጉም። ስታዲየም እንዲሰራ ሲጠየቁ ተዛልፈው እንደነበር አይረሳም። አሁን ስታዲየም ይሰራበታል የተባለውና ከበሮ የሚመታበት ሜዳም ድሮ በ1974 ኮሎኔል መንግስቱ ብሔራዊ ስታዲየም እንዲሰራበት በስጦታ የሰጡት ቦታ መሆኑ እየታወቀ እስአከሁን አለመሰራቱ አጀንዳ መሆን ሲገባው እንደ ታላቅ ስኬት መቅረቡ ሊዋጥልን አይችልም። የዛሬ 60ዓመት በተሠራ ስታዲየም ቡድናችን ከ31ዓመት በኋላ ለድል በቃ ሲባል ከዚህ ለድል ካልበቃንባቸው ዓመታት ውስጥ ኢህአዴግ ሃያ አንዱን ይወስዳል – 70በመቶ ማለት ነው፡፡

ሚዲያ መረጃ አቀባይ ቢሆንም ብሔራዊ ስሜትን በተመለከተ የሕዝብ አካል እንደ መሆኑ ያንን መካፈሉ ስህተት ባይኖረውም ዋናውን ጉዳይ ግን መርሳት የለበትም፡፡ ድልን ሲያበስርና ችቦ ሲለኩስ ስኬት ዓልባ የነበሩትን ዓመታት ማስታወስና መጪው ደግሞ ምንያህል ፈታኝ ሊሆን እንደሚችል በሰከነ መንገድ የማስገንዘብ ኃላፊነቱን መዘንጋት አይገባውም፡፡ በቀጣይ ጨዋታዎች ላይ ያለንን ብቃትና ተወዳዳሪነትም ሳይጠቁም በድል ብቻ የሰከረ ሚዲያ በመንግሥት ቁጥጥር ሥር ያሉት ከሚያደርጉት የፕሮፓጋንዳ ዘመቻ የተለየ አያደርገውም፡፡

በድሉ የተደሰትነውን ያህል በድሉ አማካይነት የሚፈጸመውን የታሪክ ሽሚያ አልወደድነውም።ኢህአዴግ ተራ የፖለቲካ ቁማሩን በመተው ይህንን ከባድሜ ዘመቻና መለቀቅ በኋላ የታየውን ሊደበዝዝ የማይችል ብሔራዊ ስሜት ትምህርት ይውሰድበት – መማር ከቻለ፡፡ ኢህአዴግ እንደሚለው ኢትዮጵያዊነት “በአየር ላይ” ያለ ባዶ ስሜት ሳይሆን በእያንዳንዱ ዜጋ ልብ ውስጥ የታተመ ውድ ጉዳይ ነውና ይኩራበት፤ አሁንም ድል ለኢትዮጵያ ህዝብና ለቡድናችን!! ለቀጣዩ ውድድር ልዩ ወገብ ጠበቅ!!

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Editorial Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Comments

  1. dereje melaku says

    October 25, 2012 11:33 pm at 11:33 pm

    dear the children of Ethiopia

    first and for most i would like to thank you so much for your relentless effort to give information for the Ethiopian people. having said that let me introduced my self this is … who was the member of the veteran Ethiopian teachers association ,Ethiopian free press association and i was also a columnist in tobia and lissane hezebe private news paper , currently i am a columnist in finotenessanet newspaper

    i have been a member of the Ethiopian human rights council for the last 15 years and currently i am one of the executive members of Ethiopian human rights council

    by the way i have got your web site while i was coming in Ireland for a very short period of time internship program me but when i return back to Ethiopia it is impossible to get your web site as that of Ireland so that how could have access to your web site in Ethiopia ? can you subscribe your web site to my web site to my email ? please help me to read your lovely web site as you know it all web site which focused on the poltics of Ethiopia off course which is independent one banned by the facist wouyane regime so that we do not have alternative source of information . if possible subscribe your very important web site to me and my friend

    with best regard
    your sincerely dm

    WE LOVE ETHIOPIA AND WE STAND FOR HER UNITY

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule