• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ከሞት በፊት እውነተኛ ክብር

October 10, 2012 02:14 am by Editor 1 Comment

“… ከሁሉ አስቀድሞ ማሸነፍ የሚኖርብን በውስጣችን ያለውን ፍርሃት ነው። ለህወሃት/ኢህአዴግ ታማኝ ሊሆኑ የሚችሉት የጦርና የፀጥታ ኃይሎቹ እንዲሁም የስለላ ተቋሙ የህዝብ ድጋፍ የሌላቸው የጥቂት ዘረኞች ስብስብ በመሆኑ የሕዝብ እምቢተኝነት ሲጠናከር በቀላሉ ይመክናሉ። አመራሮቹ አስተሳሰባቸው በጣም ጠባብ፤ ብቃታቸውም እጅግ ዝቅተኛ ነው። በመሆኑም እነዚህ ኃይሎች ሁሉንም ነገር እንደተቆጣጠሩት አድርጎ ማሰብ ራስን ማዋረድ ነው። ስለዚህም መሸሽ ሳይሆን በየጊዜው ልንፈታተናቸው፣ ልንጎነትላቸውና ልንፋለማቸው ይገባል። ስለሆነም ካሁን በኋላ ሥራው ህወሃት/ኢህአዴግን ከውስጥ ሆኖ የመበታተንና የማፍረስን ሥራ ነው። የነጻነት ኃይሎችም መዋቅራቸውን በማስፋትና በርካታ ህዋሶችን በመፍጠር በትጋት እየሠሩ ይገኛሉ። የህወሃት/ኢህአዴግን የመዋቅር ስፋት በነፃነት ኃይሎች የመዋቅር ስፋት መጋፈጥ ይቻል ዘንድ ትግሉ ተፋፍሟል…

“… ስለዚህ ፍትሕ፣ ሰላም፣ አንድነትና ዕርቅ የሚሰፍንባትን “አዲሲቷን ኢትዮጵያ” በጥቅም ተደልለው ወይም በፍርሃት ነፃነታቸውን አሳልፈው በሚሰጡ ሰዎች መገንባት አይቻልም። የሕዝብ እግዚኦታ፣ ለቅሶና ምሬት ወደ ተግባር ሲለወጥ የማሳሰቢያ፣ የንሰሃ ወይም የጥሪ ጊዜ አይኖርም፡፡ ከላይ እንደጠቆምነው አሁን እየቀረበ ያለው ጥሪ የኢትዮጵያ መሆኑን ልብ ይበሉ:: ይህንን ጥሪ ንቆ ነገ “እኔኮ ትዕዛዝ ፈጻሚ ነበርኩ” የሚሉ ሁሉ ይህ ጥሪ ራሱ የወንጀላቸው ማስረጃ ሆኖ እንደሚቀርብባቸው መገንዘብ አዋቂነት ነውና ይህንን እየራደ የሚገኝ ሥርዓት “እንቢ!” ያሉ ወገኖቻችን የሚኖራቸውን ሞገስና ክብር፤ ከማይቀረው የኢህአዴግ ውድቀት በኋላ ተባባሪዎቹ ላይ ከሚደርስባቸው ውርደት ጋር በማነጻጸር ዛሬ ለእውነት እንቁም፡፡ ወደ ልባችን እንመለስ!! ለጥሪውም ምላሽ እንስጥ!!”

ይህ ከላይ የተቀመጠው መልዕክት የአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ “ደወል” በሚል ርዕስ ለስርዓቱ ታዘዦች በተከታታይ ካስተላለፈው መልዕክት ሁለተኛው ቁጥር ላይ የተቀነጨበ ነው። ሃሳቡን ቀንጭበን የወሰድነው ነገር ለመድገም ፈልገን ሳይሆን የወቅቱን ሁኔታ ለማሳሰብ ያህል ነው። ስጋታችንን ለመጠቆም ነው።

ኢህአዴግ ላለፉት ሃያ አንድ ዓመታት እንዴት ኖረ? ብለን ስንጠይቅ መልሱ በስለላ፣በወታደራዊ ሃይል፣ በድርጅታዊ አቅም ግዝፈቱ ሳይሆን የተቃዋሚው ጎራ ቁልፍ ድክመትና ራዕይ አልባነት እንዳለ ሆኖ፣ በ“የነጻነት ተፋላሚዎች” የተሸናፊነት ስሜትና በውስጣቸው ባለ ፍርሃት ሳቢያ ነው። ዛሬ ኢህአዴግ ያለበትን ትክክለኛ ትኩሳት መረዳት ለሚችሉ ስርዓቱ “በስብሷል፣ ሸትቷል” በማለት ከቁጥር በላይ ማስረጃዎች ራሳቸውን መጥቀስ ይቻላል። ስጋታችን የሚነሳው ከዚሁ ከመበስበስ አደጋ ላይ ይሆናል።

ኢህአዴግ ባለስልጣናቱ በሙስና የገለሙ፣ ከድሃ ህዝብ ላይ በመዝረፍ አጥንቱን የሚግጡ፣ አገርን ከመምራት ይልቅ በተራ ዝርፊያና በረከሰ ወንጀል የተጨማለቁ፣ የስብዕናቸው እድፈት ሊደበቅ የማይችልበት ደረጃ ላይ የደረሰባቸው፣ የሸተተ ስርዓትና አመራር አገርናና ህዝብን ተቆጣጥረው እንደሚኖሩ አድርጎ ማሰብ ከላይ እንደተገለጸው ራስን የማዋረድ ያህል ቢሆንም ከሁሉም በላይ እኛን የሚጨንቀን የአገራችን የወደፊት ጉዳይ ነው።

አሁን ባለው የመቧደንና የመሰነጣጠቅ አዝማሚያ፣ ስርዓቱና ባለስልጣኑ ከደረሱበት የመሞሻለቅ አፋፍ ላይ እንደ ቆምን ይሰማናል። ባለን መረጃና በያቅጣጫው ከሚታዩት ምልክቶች አንጻር የሚፈርስ ስርዓት ስለመኖሩ መጠራጠር አቁመናል። ይህንኑ የመፈራረስ አደጋ ለማስታገስ እንደተለመደው ስታሊናዊ ርምጃዎች በቅርቡ እንደምንሰማም አይታበልም። በዚህ ሁሉ መደነባበር ውስጥ አገራችንን የሚሉ የቁርጥ ቀን ልጆች ከወዲሁ ዝግጅታቸውን ሊያደርጉ ይገባል እንላለን።

ታሪክ ሰርቶ ማለፍ በደልን ሁሉ ያስረሳልና ለአገራችን ሲባል፣ ለህዝብ ሲባል፣ ለራስ ሲባል፣ ለራስ ልጅ ልጆች ሲባል፣ ማለፍም ስላለ ኢህአዴግ በቅድሚያ አገራችንን የሚታደግ ርምጃ ቢወስድ ሁሉንም ያቀለዋልና አገርና ህዝብ ደስ እንደሚላቸው ጥርጥር ለውም። ተቃዋሚዎችም ከመቼውም ጊዜ ይልቅ ትግልንና ዓላማን ወደ መሬት ለማውረድ ሊረባረቡ የሚገባቸው ወቅት ላይ እንደ ሆኑ ቢያውቁትም ልናስታወሳቸው እንወዳለን። በየደረጃው ያለን የኢትዮጵያ ልጆች ወቅቱ የሚጠይቀውን ሁሉ በማስተዋል ልናደርግ ይገባልና አገርን ለሚጠቅም አጀንዳ ሁሉ በመነዳት ሳይሆን አስተዋይነት በተሞላው መንገድ ተባባሪነትን ማሳየት እንደሚጠበቅ እንጠቁማለን። ለማንኛውም የፖለቲካ የአየር ትንበያ ባለሙያዎች ያስፈልጉናል። ባለሙያዎቹ የንስሃን ጊዜ ሲያበጁ ከሞት በፊት ንስሃን ይፈጥን ይሆናል!! ህዝብ ይቅር ካለ አገርም ትጠቀማለች። መጪው ትውልድም ባለው ለመቀጠል ይታደላል። ግን ባስቸኳይ ይሁን!!

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Editorial Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Comments

  1. Kibba says

    October 26, 2012 10:15 am at 10:15 am

    ህወህት/ኢህአዴግ እስክሁን የቋየው በስለላ፣በወታደራዊ ሃይል፣ እና በድርጅታዊ አቅም ግዝፈቱ ሳይሆን በተቃዋሚው ጎራ ያለው ድክመትና ራዕይ አልባነት እንዳለ ሆኖ፣ በ“የነጻነት ተፋላሚዎች” የተሸናፊነት ስሜትና በ መላ ኢትዮጵያውያኖች በውስጣቸው ባለው “ፍርሃት” ሳቢያ ነው።
    ዛሬ ኢህአዴግ ያለበትን ትክክለኛ ትኩሳት መረዳት ለሚችሉ፡ ስርዓቱ “በስብሷል፣ ሸትቷል” ለዚህም ከቁጥር በላይ ማስረጃዎችን መጥቀስ እና ማቅረብ ይቻላል።
    ጥየቂችን ግን ይህን የመበስበስ ሥርዓት ለማሽነፍ የህዝበችንን “ፍርሃት” እንዴት ማሽነፍ እንችላለን ነው።

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የሲኖዶሱ ውዝግብ አካሄድና መጪው የአፍሪካ ኅብረት ጉባዔ February 6, 2023 02:03 am
  • የእሁዱ ሰላማዊ ሰልፍ ተራዘመ፤ ተጠባቂው ዕርቅ ፍንጭ እያሳየ ነው February 3, 2023 05:17 pm
  • የብላቴ: የውጊያ ማርሽ ቀያሪ ሠራዊት መፍለቂያ ማዕከል February 3, 2023 10:06 am
  • በኢትዮጵያ 27 በመቶ የሚሆነው የአእምሮ በሽተኛ ነው ተባለ February 3, 2023 09:47 am
  • “አስደንጋጭ”! 1 ሚሊዮን ከሚጠጋ ተፈታኝ ተማሪ ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገባው 30 ሺህ (3.3%) ብቻ ነው  January 27, 2023 09:11 am
  • የማይዘነጋዉ የኢትዮጵያዊያኖች የጀግንነት ተጋድሎ ታሪክ፡- ኮሎኔል ባጫ ሁንዴ (ታጠቅ) January 27, 2023 06:12 am
  • ጎርጎራ – የመጻዒው ዘመን ሙሽራ! የዉበት ፈርጥ! January 17, 2023 04:18 pm
  • ሁለተኛው መስቀል አደባባይ January 17, 2023 04:13 pm
  • በአቡዳቢ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን January 17, 2023 04:08 pm
  • በንፋስ ስልክ ላፍቶ ስምንት የመሬት ሌቦች ተያዙ January 16, 2023 11:36 am
  • ሺሻ ሲያስጨሱ በተገኙ ሆቴሎችና የምሽት ጭፈራ ቤቶች ላይ እርምጃ ተወሰደ January 16, 2023 08:50 am
  • በሐሰተኛ መታወቂያ የደኅንነት አባል ነን ብለው ሲያጭበረብሩ የነበሩ ተያዙ January 13, 2023 02:03 pm
  • ተሽከርካሪ ወንበር ለትግራይ – “ናይ ኣካል ጉዱኣት ተሽከርካሪ ዘለዎ ወንበር” January 12, 2023 07:17 pm
  • የአማራው ኩራት፣ የኢትዮጵያ ዘብ፣ የትህነግን ቅስም ሰባሪ! January 12, 2023 04:00 pm
  • በኢትዮጵያ ላይ የተጣሉ ማዕቀብ እና ሌሎች አስገዳጅ ሕጎች ሙሉ ለሙሉ ተሰረዙ January 12, 2023 01:52 pm
  • የቻይና ዕዳ ስረዛ “Payday Loan Diplomacy” ወይስ ኢትዮጵያን ያዳነ ተግባር? January 12, 2023 11:00 am
  • የአዲስ አበባ አስተዳደር ከቋንቋ ጋር በተያያዘ ውሳኔ አስተላለፈ January 12, 2023 10:46 am
  • “አምባሳደሩ” የቀድሞ ጌቶቻቸውን እንዲያቋቁሙ ተሾሙ January 11, 2023 03:47 pm
  • መከላከያ ሸኔን የሚዋጉ ሚሊሻዎችን አሠልጥኖ አስመረቀ January 10, 2023 05:37 pm
  • በሰባት ተጠርጣሪዎች ላይ ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመሰረተ January 10, 2023 03:36 pm
  • የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ አቅጣጫ January 6, 2023 03:26 pm
  • “ከዕብሪቱ አስተንፍሰነዋል” – ኢሳያስ January 2, 2023 07:29 pm
  • [ኢትዮጵያን] “አስታክኮ ኤርትራን መውጋት ለሚፈልግ ኃይል አንተባበርም” January 2, 2023 07:11 pm
  • የ፰ ወር ሕጻንና ጨቅላ ወንዶች የሚደፈሩባት ትግራይ December 14, 2022 02:49 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule