• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ከሞት በፊት እውነተኛ ክብር

October 10, 2012 02:14 am by Editor 1 Comment

“… ከሁሉ አስቀድሞ ማሸነፍ የሚኖርብን በውስጣችን ያለውን ፍርሃት ነው። ለህወሃት/ኢህአዴግ ታማኝ ሊሆኑ የሚችሉት የጦርና የፀጥታ ኃይሎቹ እንዲሁም የስለላ ተቋሙ የህዝብ ድጋፍ የሌላቸው የጥቂት ዘረኞች ስብስብ በመሆኑ የሕዝብ እምቢተኝነት ሲጠናከር በቀላሉ ይመክናሉ። አመራሮቹ አስተሳሰባቸው በጣም ጠባብ፤ ብቃታቸውም እጅግ ዝቅተኛ ነው። በመሆኑም እነዚህ ኃይሎች ሁሉንም ነገር እንደተቆጣጠሩት አድርጎ ማሰብ ራስን ማዋረድ ነው። ስለዚህም መሸሽ ሳይሆን በየጊዜው ልንፈታተናቸው፣ ልንጎነትላቸውና ልንፋለማቸው ይገባል። ስለሆነም ካሁን በኋላ ሥራው ህወሃት/ኢህአዴግን ከውስጥ ሆኖ የመበታተንና የማፍረስን ሥራ ነው። የነጻነት ኃይሎችም መዋቅራቸውን በማስፋትና በርካታ ህዋሶችን በመፍጠር በትጋት እየሠሩ ይገኛሉ። የህወሃት/ኢህአዴግን የመዋቅር ስፋት በነፃነት ኃይሎች የመዋቅር ስፋት መጋፈጥ ይቻል ዘንድ ትግሉ ተፋፍሟል…

“… ስለዚህ ፍትሕ፣ ሰላም፣ አንድነትና ዕርቅ የሚሰፍንባትን “አዲሲቷን ኢትዮጵያ” በጥቅም ተደልለው ወይም በፍርሃት ነፃነታቸውን አሳልፈው በሚሰጡ ሰዎች መገንባት አይቻልም። የሕዝብ እግዚኦታ፣ ለቅሶና ምሬት ወደ ተግባር ሲለወጥ የማሳሰቢያ፣ የንሰሃ ወይም የጥሪ ጊዜ አይኖርም፡፡ ከላይ እንደጠቆምነው አሁን እየቀረበ ያለው ጥሪ የኢትዮጵያ መሆኑን ልብ ይበሉ:: ይህንን ጥሪ ንቆ ነገ “እኔኮ ትዕዛዝ ፈጻሚ ነበርኩ” የሚሉ ሁሉ ይህ ጥሪ ራሱ የወንጀላቸው ማስረጃ ሆኖ እንደሚቀርብባቸው መገንዘብ አዋቂነት ነውና ይህንን እየራደ የሚገኝ ሥርዓት “እንቢ!” ያሉ ወገኖቻችን የሚኖራቸውን ሞገስና ክብር፤ ከማይቀረው የኢህአዴግ ውድቀት በኋላ ተባባሪዎቹ ላይ ከሚደርስባቸው ውርደት ጋር በማነጻጸር ዛሬ ለእውነት እንቁም፡፡ ወደ ልባችን እንመለስ!! ለጥሪውም ምላሽ እንስጥ!!”

ይህ ከላይ የተቀመጠው መልዕክት የአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ “ደወል” በሚል ርዕስ ለስርዓቱ ታዘዦች በተከታታይ ካስተላለፈው መልዕክት ሁለተኛው ቁጥር ላይ የተቀነጨበ ነው። ሃሳቡን ቀንጭበን የወሰድነው ነገር ለመድገም ፈልገን ሳይሆን የወቅቱን ሁኔታ ለማሳሰብ ያህል ነው። ስጋታችንን ለመጠቆም ነው።

ኢህአዴግ ላለፉት ሃያ አንድ ዓመታት እንዴት ኖረ? ብለን ስንጠይቅ መልሱ በስለላ፣በወታደራዊ ሃይል፣ በድርጅታዊ አቅም ግዝፈቱ ሳይሆን የተቃዋሚው ጎራ ቁልፍ ድክመትና ራዕይ አልባነት እንዳለ ሆኖ፣ በ“የነጻነት ተፋላሚዎች” የተሸናፊነት ስሜትና በውስጣቸው ባለ ፍርሃት ሳቢያ ነው። ዛሬ ኢህአዴግ ያለበትን ትክክለኛ ትኩሳት መረዳት ለሚችሉ ስርዓቱ “በስብሷል፣ ሸትቷል” በማለት ከቁጥር በላይ ማስረጃዎች ራሳቸውን መጥቀስ ይቻላል። ስጋታችን የሚነሳው ከዚሁ ከመበስበስ አደጋ ላይ ይሆናል።

ኢህአዴግ ባለስልጣናቱ በሙስና የገለሙ፣ ከድሃ ህዝብ ላይ በመዝረፍ አጥንቱን የሚግጡ፣ አገርን ከመምራት ይልቅ በተራ ዝርፊያና በረከሰ ወንጀል የተጨማለቁ፣ የስብዕናቸው እድፈት ሊደበቅ የማይችልበት ደረጃ ላይ የደረሰባቸው፣ የሸተተ ስርዓትና አመራር አገርናና ህዝብን ተቆጣጥረው እንደሚኖሩ አድርጎ ማሰብ ከላይ እንደተገለጸው ራስን የማዋረድ ያህል ቢሆንም ከሁሉም በላይ እኛን የሚጨንቀን የአገራችን የወደፊት ጉዳይ ነው።

አሁን ባለው የመቧደንና የመሰነጣጠቅ አዝማሚያ፣ ስርዓቱና ባለስልጣኑ ከደረሱበት የመሞሻለቅ አፋፍ ላይ እንደ ቆምን ይሰማናል። ባለን መረጃና በያቅጣጫው ከሚታዩት ምልክቶች አንጻር የሚፈርስ ስርዓት ስለመኖሩ መጠራጠር አቁመናል። ይህንኑ የመፈራረስ አደጋ ለማስታገስ እንደተለመደው ስታሊናዊ ርምጃዎች በቅርቡ እንደምንሰማም አይታበልም። በዚህ ሁሉ መደነባበር ውስጥ አገራችንን የሚሉ የቁርጥ ቀን ልጆች ከወዲሁ ዝግጅታቸውን ሊያደርጉ ይገባል እንላለን።

ታሪክ ሰርቶ ማለፍ በደልን ሁሉ ያስረሳልና ለአገራችን ሲባል፣ ለህዝብ ሲባል፣ ለራስ ሲባል፣ ለራስ ልጅ ልጆች ሲባል፣ ማለፍም ስላለ ኢህአዴግ በቅድሚያ አገራችንን የሚታደግ ርምጃ ቢወስድ ሁሉንም ያቀለዋልና አገርና ህዝብ ደስ እንደሚላቸው ጥርጥር ለውም። ተቃዋሚዎችም ከመቼውም ጊዜ ይልቅ ትግልንና ዓላማን ወደ መሬት ለማውረድ ሊረባረቡ የሚገባቸው ወቅት ላይ እንደ ሆኑ ቢያውቁትም ልናስታወሳቸው እንወዳለን። በየደረጃው ያለን የኢትዮጵያ ልጆች ወቅቱ የሚጠይቀውን ሁሉ በማስተዋል ልናደርግ ይገባልና አገርን ለሚጠቅም አጀንዳ ሁሉ በመነዳት ሳይሆን አስተዋይነት በተሞላው መንገድ ተባባሪነትን ማሳየት እንደሚጠበቅ እንጠቁማለን። ለማንኛውም የፖለቲካ የአየር ትንበያ ባለሙያዎች ያስፈልጉናል። ባለሙያዎቹ የንስሃን ጊዜ ሲያበጁ ከሞት በፊት ንስሃን ይፈጥን ይሆናል!! ህዝብ ይቅር ካለ አገርም ትጠቀማለች። መጪው ትውልድም ባለው ለመቀጠል ይታደላል። ግን ባስቸኳይ ይሁን!!

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Editorial Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Comments

  1. Kibba says

    October 26, 2012 10:15 am at 10:15 am

    ህወህት/ኢህአዴግ እስክሁን የቋየው በስለላ፣በወታደራዊ ሃይል፣ እና በድርጅታዊ አቅም ግዝፈቱ ሳይሆን በተቃዋሚው ጎራ ያለው ድክመትና ራዕይ አልባነት እንዳለ ሆኖ፣ በ“የነጻነት ተፋላሚዎች” የተሸናፊነት ስሜትና በ መላ ኢትዮጵያውያኖች በውስጣቸው ባለው “ፍርሃት” ሳቢያ ነው።
    ዛሬ ኢህአዴግ ያለበትን ትክክለኛ ትኩሳት መረዳት ለሚችሉ፡ ስርዓቱ “በስብሷል፣ ሸትቷል” ለዚህም ከቁጥር በላይ ማስረጃዎችን መጥቀስ እና ማቅረብ ይቻላል።
    ጥየቂችን ግን ይህን የመበስበስ ሥርዓት ለማሽነፍ የህዝበችንን “ፍርሃት” እንዴት ማሽነፍ እንችላለን ነው።

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am
  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule