• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ከሞት በፊት እውነተኛ ክብር

October 10, 2012 02:14 am by Editor 1 Comment

“… ከሁሉ አስቀድሞ ማሸነፍ የሚኖርብን በውስጣችን ያለውን ፍርሃት ነው። ለህወሃት/ኢህአዴግ ታማኝ ሊሆኑ የሚችሉት የጦርና የፀጥታ ኃይሎቹ እንዲሁም የስለላ ተቋሙ የህዝብ ድጋፍ የሌላቸው የጥቂት ዘረኞች ስብስብ በመሆኑ የሕዝብ እምቢተኝነት ሲጠናከር በቀላሉ ይመክናሉ። አመራሮቹ አስተሳሰባቸው በጣም ጠባብ፤ ብቃታቸውም እጅግ ዝቅተኛ ነው። በመሆኑም እነዚህ ኃይሎች ሁሉንም ነገር እንደተቆጣጠሩት አድርጎ ማሰብ ራስን ማዋረድ ነው። ስለዚህም መሸሽ ሳይሆን በየጊዜው ልንፈታተናቸው፣ ልንጎነትላቸውና ልንፋለማቸው ይገባል። ስለሆነም ካሁን በኋላ ሥራው ህወሃት/ኢህአዴግን ከውስጥ ሆኖ የመበታተንና የማፍረስን ሥራ ነው። የነጻነት ኃይሎችም መዋቅራቸውን በማስፋትና በርካታ ህዋሶችን በመፍጠር በትጋት እየሠሩ ይገኛሉ። የህወሃት/ኢህአዴግን የመዋቅር ስፋት በነፃነት ኃይሎች የመዋቅር ስፋት መጋፈጥ ይቻል ዘንድ ትግሉ ተፋፍሟል…

“… ስለዚህ ፍትሕ፣ ሰላም፣ አንድነትና ዕርቅ የሚሰፍንባትን “አዲሲቷን ኢትዮጵያ” በጥቅም ተደልለው ወይም በፍርሃት ነፃነታቸውን አሳልፈው በሚሰጡ ሰዎች መገንባት አይቻልም። የሕዝብ እግዚኦታ፣ ለቅሶና ምሬት ወደ ተግባር ሲለወጥ የማሳሰቢያ፣ የንሰሃ ወይም የጥሪ ጊዜ አይኖርም፡፡ ከላይ እንደጠቆምነው አሁን እየቀረበ ያለው ጥሪ የኢትዮጵያ መሆኑን ልብ ይበሉ:: ይህንን ጥሪ ንቆ ነገ “እኔኮ ትዕዛዝ ፈጻሚ ነበርኩ” የሚሉ ሁሉ ይህ ጥሪ ራሱ የወንጀላቸው ማስረጃ ሆኖ እንደሚቀርብባቸው መገንዘብ አዋቂነት ነውና ይህንን እየራደ የሚገኝ ሥርዓት “እንቢ!” ያሉ ወገኖቻችን የሚኖራቸውን ሞገስና ክብር፤ ከማይቀረው የኢህአዴግ ውድቀት በኋላ ተባባሪዎቹ ላይ ከሚደርስባቸው ውርደት ጋር በማነጻጸር ዛሬ ለእውነት እንቁም፡፡ ወደ ልባችን እንመለስ!! ለጥሪውም ምላሽ እንስጥ!!”

ይህ ከላይ የተቀመጠው መልዕክት የአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ “ደወል” በሚል ርዕስ ለስርዓቱ ታዘዦች በተከታታይ ካስተላለፈው መልዕክት ሁለተኛው ቁጥር ላይ የተቀነጨበ ነው። ሃሳቡን ቀንጭበን የወሰድነው ነገር ለመድገም ፈልገን ሳይሆን የወቅቱን ሁኔታ ለማሳሰብ ያህል ነው። ስጋታችንን ለመጠቆም ነው።

ኢህአዴግ ላለፉት ሃያ አንድ ዓመታት እንዴት ኖረ? ብለን ስንጠይቅ መልሱ በስለላ፣በወታደራዊ ሃይል፣ በድርጅታዊ አቅም ግዝፈቱ ሳይሆን የተቃዋሚው ጎራ ቁልፍ ድክመትና ራዕይ አልባነት እንዳለ ሆኖ፣ በ“የነጻነት ተፋላሚዎች” የተሸናፊነት ስሜትና በውስጣቸው ባለ ፍርሃት ሳቢያ ነው። ዛሬ ኢህአዴግ ያለበትን ትክክለኛ ትኩሳት መረዳት ለሚችሉ ስርዓቱ “በስብሷል፣ ሸትቷል” በማለት ከቁጥር በላይ ማስረጃዎች ራሳቸውን መጥቀስ ይቻላል። ስጋታችን የሚነሳው ከዚሁ ከመበስበስ አደጋ ላይ ይሆናል።

ኢህአዴግ ባለስልጣናቱ በሙስና የገለሙ፣ ከድሃ ህዝብ ላይ በመዝረፍ አጥንቱን የሚግጡ፣ አገርን ከመምራት ይልቅ በተራ ዝርፊያና በረከሰ ወንጀል የተጨማለቁ፣ የስብዕናቸው እድፈት ሊደበቅ የማይችልበት ደረጃ ላይ የደረሰባቸው፣ የሸተተ ስርዓትና አመራር አገርናና ህዝብን ተቆጣጥረው እንደሚኖሩ አድርጎ ማሰብ ከላይ እንደተገለጸው ራስን የማዋረድ ያህል ቢሆንም ከሁሉም በላይ እኛን የሚጨንቀን የአገራችን የወደፊት ጉዳይ ነው።

አሁን ባለው የመቧደንና የመሰነጣጠቅ አዝማሚያ፣ ስርዓቱና ባለስልጣኑ ከደረሱበት የመሞሻለቅ አፋፍ ላይ እንደ ቆምን ይሰማናል። ባለን መረጃና በያቅጣጫው ከሚታዩት ምልክቶች አንጻር የሚፈርስ ስርዓት ስለመኖሩ መጠራጠር አቁመናል። ይህንኑ የመፈራረስ አደጋ ለማስታገስ እንደተለመደው ስታሊናዊ ርምጃዎች በቅርቡ እንደምንሰማም አይታበልም። በዚህ ሁሉ መደነባበር ውስጥ አገራችንን የሚሉ የቁርጥ ቀን ልጆች ከወዲሁ ዝግጅታቸውን ሊያደርጉ ይገባል እንላለን።

ታሪክ ሰርቶ ማለፍ በደልን ሁሉ ያስረሳልና ለአገራችን ሲባል፣ ለህዝብ ሲባል፣ ለራስ ሲባል፣ ለራስ ልጅ ልጆች ሲባል፣ ማለፍም ስላለ ኢህአዴግ በቅድሚያ አገራችንን የሚታደግ ርምጃ ቢወስድ ሁሉንም ያቀለዋልና አገርና ህዝብ ደስ እንደሚላቸው ጥርጥር ለውም። ተቃዋሚዎችም ከመቼውም ጊዜ ይልቅ ትግልንና ዓላማን ወደ መሬት ለማውረድ ሊረባረቡ የሚገባቸው ወቅት ላይ እንደ ሆኑ ቢያውቁትም ልናስታወሳቸው እንወዳለን። በየደረጃው ያለን የኢትዮጵያ ልጆች ወቅቱ የሚጠይቀውን ሁሉ በማስተዋል ልናደርግ ይገባልና አገርን ለሚጠቅም አጀንዳ ሁሉ በመነዳት ሳይሆን አስተዋይነት በተሞላው መንገድ ተባባሪነትን ማሳየት እንደሚጠበቅ እንጠቁማለን። ለማንኛውም የፖለቲካ የአየር ትንበያ ባለሙያዎች ያስፈልጉናል። ባለሙያዎቹ የንስሃን ጊዜ ሲያበጁ ከሞት በፊት ንስሃን ይፈጥን ይሆናል!! ህዝብ ይቅር ካለ አገርም ትጠቀማለች። መጪው ትውልድም ባለው ለመቀጠል ይታደላል። ግን ባስቸኳይ ይሁን!!

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Editorial Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Comments

  1. Kibba says

    October 26, 2012 10:15 am at 10:15 am

    ህወህት/ኢህአዴግ እስክሁን የቋየው በስለላ፣በወታደራዊ ሃይል፣ እና በድርጅታዊ አቅም ግዝፈቱ ሳይሆን በተቃዋሚው ጎራ ያለው ድክመትና ራዕይ አልባነት እንዳለ ሆኖ፣ በ“የነጻነት ተፋላሚዎች” የተሸናፊነት ስሜትና በ መላ ኢትዮጵያውያኖች በውስጣቸው ባለው “ፍርሃት” ሳቢያ ነው።
    ዛሬ ኢህአዴግ ያለበትን ትክክለኛ ትኩሳት መረዳት ለሚችሉ፡ ስርዓቱ “በስብሷል፣ ሸትቷል” ለዚህም ከቁጥር በላይ ማስረጃዎችን መጥቀስ እና ማቅረብ ይቻላል።
    ጥየቂችን ግን ይህን የመበስበስ ሥርዓት ለማሽነፍ የህዝበችንን “ፍርሃት” እንዴት ማሽነፍ እንችላለን ነው።

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • በወልቃይት 1.1ሚሊዮን ኩንታል ሰሊጥ ለመሰብሰብ ከ1 ሚሊዮን በላይ ሠራተኛ ይፈለጋል September 27, 2023 10:42 am
  • በአማራ ክልል ሰላም ዕጦት ከ90.5 ቢሊዮን ብር በላይ ፕሮጀክቶች ቆመዋል September 27, 2023 08:41 am
  • ወርቁ አይተነው የሸሹት ከዝርፊያ፣ ውንብድናና ዕዳ ጋር በተያያዘ ነው September 21, 2023 02:38 pm
  • ወደ አማራ ክልል ሊተላለፍ የነበረ መሣሪያና ሰነድ ተያዘ September 19, 2023 04:35 pm
  • በትግራይ መርዶ በይፋ ሊታወጅ ነው September 19, 2023 04:22 pm
  • ጃርቶች ለምን ይጮኻሉ? September 19, 2023 04:37 am
  • “ዐቢይ ግድቡን ሸጦታል” ጌታቸው ረዳ September 11, 2023 10:18 am
  • አቶ አገኘሁ መረጃ አሳልፎ በመስጠት ዋጋ እንደሚከፍሉ ተሰማ September 10, 2023 06:52 pm
  • ለዋዜማ ሬዲዮ “ኢትዮጵያን ቋሚ የውሀ ባለ እዳ” ያደርጋል ያላችሁት ረቂቅ ሰነድ የታለ? September 10, 2023 01:58 am
  • ወደር የሌለው የኅብረተሰባዊት ኢትዮጵያ ጀግና! ብርጋዴር ጄኔራል ተስፋዬ ኃብተማርያም September 8, 2023 02:31 pm
  • የትግራይ መፍረስ በርዕሰ መስተዳደሩ አንደበት September 8, 2023 02:49 am
  • ከያቤሎ አዲስ አበባ የተላከ ኮንትሮባንድ ጉለሌ ተያዘ September 7, 2023 01:40 pm
  • “እንኳን ተለያይተንና እርስ በርስ ተባልተን በአንድነት ቆመንም ወጀቡን መሻገር አቅቶናል” September 7, 2023 01:31 am
  • ራሱን መሪ አልባ የሚያደርገው አማራ ክልል August 24, 2023 11:50 pm
  • ጀብደኛው August 24, 2023 10:06 am
  • ጎንደርና ባሕር ዳር ከተሞች ወደ ቀድሞ ሰላማቸው ተመልሰዋል August 13, 2023 10:55 pm
  • ኢትዮጵያ በታሪኳ የመጀመሪያውን ግዙፍ ወታደራዊ ኃይል አስመረቀች August 13, 2023 10:26 pm
  • ሪፖርተር የፓርላማ ወንበር አስልቶ የአስቸኳይ አዋጁ በፓርላማ እንዳይደገፍ አቅጣጫ አመላከተ August 13, 2023 09:11 pm
  • ወደ ኤርትራ በኮንትሮባንድ የሚሻገሩ ቆሳቁሶች እየተያዙ ነው August 11, 2023 12:52 pm
  • የአማራ ክልል ትልልቅ ከተሞች ተኩስ ዓልባ ሆነው ውለዋል August 10, 2023 04:31 pm
  • “አንድ ሰው ለመግደል ኅንፃውን ማቃጠል” የኢ-ዲሞክራሲና ጽንፈኛ ኃይሎች ቅዠት፤ (ክፍል ሁለት) August 10, 2023 09:44 am
  • “አርበኛ” መሳይ – “የድል ዜና” ሳይበርድ 50ሺህ ዶላር በጎፈንድሚ August 10, 2023 09:08 am
  • በሕዝቡ ድጋፍ ከተሞች ከዘራፊው መንጋ ሥጋት ነጻ መሆናቸው ይፋ ሆነ August 9, 2023 11:47 am
  • ትህነግ አራተኛውን ሞት ሞተ  August 8, 2023 05:47 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule