• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ወሬ ይገድላል

January 2, 2013 10:29 am by Editor Leave a Comment

በጎርጎሪያኑ የቀን መቁጠሪያ ለምትገለገሉ ሁሉ መልካም አዲስ ዓመት!! በአዲሱ ዓመት ከራስ ጋር በመታረቅ፣ ከህሊናና ከእዕምሮ ባርነት በመላቀቅ፣ ከይሉንታ ጥብቆ ውስጥ በመውጣት፣አካሄድን ለማሳመር ይቻል ዘንድ የተጠቀለለውን አሮጌ ዓመት ትምህርት ማድረግ ታላቅ ጉዳይ ነው። አዲሱ ዓመት ከባከኑት ዓመታቶች ጋር ተዳምሮ እንዳያጎብጠን፣ ተስፋችንን እንዳይበላውና ወደ ከፋ የፖለቲካ መሰላቸት ውስጥ እንዳይከተን መጠንቀቅ ደግሞ ከሁሉም በላይ ወሳኝ ይመስለናልና ከከንቱና የማያንጽ ወሬው ቆጠብ፣ ከተግባሩ ጨመር እናድርግ!! ወሬ ይገድላል እንዲሉ!!

ይሉኝታን እንቅበር

ባለፉት ዓመታት የይሉኝታ ፖለቲካ ጉዳት አድርሷል። በይሉኝታ በመነዳት የማይረሳ ኪሳራ ተመዝግቧል። በይሉኝታ ብቻ የደረሰብን የፖለቲካ ጠባሳ ሰምበሩ በያንዳንዳችን ሰውነት ላይ ይታያል። በተፎካካሪ ፓርቲዎችና ለለውጥ በተነሱ ፓርቲዎች ውስጥ ብዙ የሚሰሙ ጉዳዮች አሉ። በየጓሮ የሚሰማው የሃሜት፣ የጀግንነትና የአሉባልታ ትግል የሚቆመው ይሉኝታ ሲሰበርና ፊትለፊት መግጠም ሲቻል ነውና የይሉኝታን አርበኝነት እንቅበር!! ይህ የአዲስ ዓመት የመጀመሪያው የቤት ስራ ይሁን!! በተግባርም ይታይ!!

ራስን ማክበር

አብዛኛውን ጊዜ ስለ ህሊናና አእምሮ ባርነት ይነገራል። ሰዎች ከዚሁ ከአእምሮ ባርነት ራሳቸውን ነጻ እንዲያደርጉ ምክር ሲሰነዘር በተደጋጋሚ ይሰማል። ምክሮቹና ትምህርቶቹ ምን ያህል ተግባራዊ እንደሆኑ ባናውቅም ባጭሩ ግን የ“ባርነት” ዋናው መሰረት ራስን አለማክበር ነውና የራሳችንን ዋጋ እንወቅ። ራሳችንን አክብረን፣ ክብራችንንና ዋጋችንን ጠብቀን፣ ስንጓዝ ከባርነት እንላቀቃለንና ለራሳችን ክብር እንስጥ። በከበርን ቁጥር ከስሜትና ከግብታዊ የፖለቲካ ትግል ራሳችንን በማረቅ አካሄዳችንን የማስተካከል እድል እናገኛለን። በእንዲህ መልኩ ስንደግፍም ሆነ ስንደገፍ አንወድቅም። በዚህ ዓይነቱ መደጋገፍ ውስጥ ተግባር እንጂ ፕሮፓጋንዳ ቦታው ያንሳል። መተማመን ይሰፍናል። ዛሬ እልል ብለን ነገ ከማዘን እንድናለን።ሁላችንም ራሳችንን ስናከብር የጋራ ራዕይና የጋራ መሪ ለመሰየም አንቸገርም። የሰየምነውንም መሪ አምኖ ለመቀበል ጊዜ አናመነዥግም። ሰባኪና ደቀ መዝሙርም አያስፈልግም። እናም ራስን ማክበር ዋጋው ታላቅ ይሆናል። ከመነዳትም ያድናልና!!

ያገባኛል

ባብዛኛው የአገራችን ጉዳይ ለተወሰኑ ሰዎች የተሰጠ ይመስላል። የተወሰኑ ሰዎች ይናገራሉ።ስለወገኖቻቸውና ስለ አገራቸው ይከራከራሉ። ህዝብ አደራጅተው ለመታገል የበኩላቸውን ሲያደርጉ የሚታዩት እጅግ ጥቂቶች ናቸው። አብዛኛው ህዝብ ግን አድፋጭ ነው። አብዛኛው ምሁር ተመልካች ነው። ህወሃት/ኢህአዴግ ክፉ መንግስት እንደሆነ ከልሒቅ እስከ ደቂቅ ሁሉም ህዝብ፣ የኢህአዴግ አባላትና ደጋፊዎች ጨምሮ ያውቃሉ። ግን ዳር ቆመዋል። ባልተመጣጠነ የኢኮኖሚ ፍሰት አብዛኞች ወደ ባርነት እየተመሙ፣ ልጅ ልጆቻቸውን ለባርነት በስጦታ ለማቅረብ እየገሰገሱ ነው። ልጅ ልጆቻቸው ከተወዳዳሪነት ተለይተው የበይ ተመልካች እንዲሆኑ ሲደረግ “አያገባኝም” የሚሉ እንዴት በረከቱ? ስለ ስርዓቱ ጸያፍነትና የህዝብ ምሬት ብዙ ማለት ይቻላል። ግን አድፋጩ ለምን በዛ? የፖለቲካ መሪዎቻችን ይህንን ጥያቄ መመለስ አለባቸው።አገሪቱና ህዝቧ ያስተማሯቸው የኢትዮጵያ ልጆች ካዳፋቸው የፖለቲካ ድብታ እንዴት እንዲነቁና “ያገባኛል” በሚል መንፋስ እንዲነሱ ምን ይደረግ? “የምሁራን” መንደሮች የያዛቸው እንቅልፍና የአድርባይነት ስሜት እንዴት ይነቀል? ተወደደም ተጠላም ያገባኛል የሚል ህብረተሰብ ሊፈጠር ግድ ነውና ወገብን ጠበቅ አድርጎ መስራት ግድ ይላል።

በቃኝ

ህዝብ የተቃዋሚ ፓርቲዎችን የሚያዳምጠውና የሚከለታተለው አማራጭ ስለሚፈልግ ነው።በፉክክር ተጠቃሚ ለመሆን ነው። ህዝብ የሚጠብቀውን ማድረግ ያልቻሉ አሉ። ሰሞኑን በፓርቲዎች ክርክር ስም ቀርበው ኢህአዴግን እንሞግታለን የሚሉትን ስንሰማ አጥወልውሎናል። ህዝብ እነዚህ ናቸው ተቃዋሚ ብሎ ተስፋ እንዲቆርጥ ሆን ተብሎ የሚሰራ ስራ ቢኖርም እንዴት መናገር፣ የሚናገረውን የማያውቅ፣ ስለምን እንደሚናገር ያልተረዳ፣ እቁብና እድር እንኳን መዳኘት የማይችል ሰው ፓርቲ አቋቁሞ አገር ለመምራት ያስባል? እንዲህ ያሉ ብዙ ናቸው። የምርጫ አዳማቂዎች!! በውጪም አሉ፤ በህክምና ቋንቋ “የሼልፍ ጊዜያቸው ያበቃ” መኖራቸውም፣ መጥፋታቸውም ልዩነት የሌለው ምን አለበት “ሳናውቅ እየረበሽን ኖረናል፤ በቃን” ቢሉ? ሌላም ህይወት አለ። የሚሰሩትን ከጀርባ እየተከተሉ ጤና ከመንሳት “በቃኝ” በማለት ብቻ ለህዝብ ክብር መስጠት የሚቻል ይመስለናል።

ተግባር

ስለ ህወሃት/ኢህአዴግ ብዙ ተብሏል። እንግዳ ብንሆንም እኛን ጨምሮ በየድረገጹ ያልተነገር ነገር የለም። በተለያዩ ማህበራዊ ድሮችና ሞገዶች ዛሬን ጨምሮ ስለ ኢህአዴግ እንሰማለን።የሚሰማው ብዙ ነው። በተግባር የሚታየው ግን እጅግ በጣም፣ እጅግ ጥቂት፣ በጣም በጣም ጥቂት፣ ኢምንት ነው። ወሬው እየገዘፈ ተግባሩ ሲያንስ፣ ሲኮሰምን፣ ሲሟሟ፣ ተስፋ መቁረጥ ያስከትላልና አልሞና መትሮ መንቀሳቀስ ግድ ነው። ዛሬ የሚሰሩ ስህተቶች እስከወዲያኛው የማያገግም ጠባሳ እንዳያትምብን እንጠንቀቅ። መልካም በዓል!!

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Editorial Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm
  • የተመሠረተው የፋኖ አደረጃጀት ዋነኛ ዓላማው ድርድር መሆኑ ተነገረ May 14, 2025 11:07 pm
  • ከፍተኛ የፋኖ አመራሮች መገደላቸው ተነገረ May 6, 2025 10:40 pm
  • ሃይማኖትን ለተራ የፖለቲካ ሸቀጥ ማዋል ውርደት ነው April 24, 2025 12:43 am
  •  የኬሪያ ኢብራሒም ኑዛዜ “ብትንትናችን ወጥቷል” April 22, 2025 12:08 am
  • ለወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን አመራሮች ወታደራዊ ሥልጠና ተሰጠ April 16, 2025 11:44 pm
  • ዓቅም እንደሌለው የገመገመው ሻዕቢያ ፊቱን ከጦርነት ወደ ዲፕሎማሲ እያዞረ ነው   April 15, 2025 12:32 am
  • “አንድ የፋኖ ተቋም (የእስክንድር) ተመሥርቷል፤ ሌሎቹ ደግሞ እንዲሁ አንድ ተቋም መሥርተው ወደዚህ ይመጡ” አበበ ጢሞ April 11, 2025 12:07 am
  • መለስ (ለገሰ) ዜናዊ – ተዋርዶ ያዋረደን! April 9, 2025 10:28 pm
  • የተከዜ ዘብ: የሉዓላዊነት መጠበቂያ April 8, 2025 11:49 pm
  • አዲስ አበባ አስተዳደር የሪፖርተርን የተዛባ መረጃ ኮነነ፤ ሕጋዊ እርምጃ እወስዳለሁ አለ April 8, 2025 10:06 pm
  • ሀሰተኛውን የሪፖርተር ዘገባ ንግድ ባንክ በጽኑ ተቃወመ፤ እርማትም ጠየቀ April 8, 2025 09:48 pm
  • “ኦሮሚያ ላይ ወይም ሌላ ቦታ ላይ ስታደርገው ከነበረ ትግራይ ወስጥም የማታደርግበት ምንም ምክንያት አይኖርህም” ነው ጌታቸው ረዳ April 7, 2025 10:22 pm
  • “TPLF’s belief in a strong federal government was always tied to its own dominance in Addis Ababa” April 7, 2025 10:15 pm
  • Counter-Video by EBC Challenges EBS Broadcast, Sparks Public Outcry Over Alleged Misinformation March 31, 2025 02:36 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule