• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ወሬ ይገድላል

January 2, 2013 10:29 am by Editor Leave a Comment

በጎርጎሪያኑ የቀን መቁጠሪያ ለምትገለገሉ ሁሉ መልካም አዲስ ዓመት!! በአዲሱ ዓመት ከራስ ጋር በመታረቅ፣ ከህሊናና ከእዕምሮ ባርነት በመላቀቅ፣ ከይሉንታ ጥብቆ ውስጥ በመውጣት፣አካሄድን ለማሳመር ይቻል ዘንድ የተጠቀለለውን አሮጌ ዓመት ትምህርት ማድረግ ታላቅ ጉዳይ ነው። አዲሱ ዓመት ከባከኑት ዓመታቶች ጋር ተዳምሮ እንዳያጎብጠን፣ ተስፋችንን እንዳይበላውና ወደ ከፋ የፖለቲካ መሰላቸት ውስጥ እንዳይከተን መጠንቀቅ ደግሞ ከሁሉም በላይ ወሳኝ ይመስለናልና ከከንቱና የማያንጽ ወሬው ቆጠብ፣ ከተግባሩ ጨመር እናድርግ!! ወሬ ይገድላል እንዲሉ!!

ይሉኝታን እንቅበር

ባለፉት ዓመታት የይሉኝታ ፖለቲካ ጉዳት አድርሷል። በይሉኝታ በመነዳት የማይረሳ ኪሳራ ተመዝግቧል። በይሉኝታ ብቻ የደረሰብን የፖለቲካ ጠባሳ ሰምበሩ በያንዳንዳችን ሰውነት ላይ ይታያል። በተፎካካሪ ፓርቲዎችና ለለውጥ በተነሱ ፓርቲዎች ውስጥ ብዙ የሚሰሙ ጉዳዮች አሉ። በየጓሮ የሚሰማው የሃሜት፣ የጀግንነትና የአሉባልታ ትግል የሚቆመው ይሉኝታ ሲሰበርና ፊትለፊት መግጠም ሲቻል ነውና የይሉኝታን አርበኝነት እንቅበር!! ይህ የአዲስ ዓመት የመጀመሪያው የቤት ስራ ይሁን!! በተግባርም ይታይ!!

ራስን ማክበር

አብዛኛውን ጊዜ ስለ ህሊናና አእምሮ ባርነት ይነገራል። ሰዎች ከዚሁ ከአእምሮ ባርነት ራሳቸውን ነጻ እንዲያደርጉ ምክር ሲሰነዘር በተደጋጋሚ ይሰማል። ምክሮቹና ትምህርቶቹ ምን ያህል ተግባራዊ እንደሆኑ ባናውቅም ባጭሩ ግን የ“ባርነት” ዋናው መሰረት ራስን አለማክበር ነውና የራሳችንን ዋጋ እንወቅ። ራሳችንን አክብረን፣ ክብራችንንና ዋጋችንን ጠብቀን፣ ስንጓዝ ከባርነት እንላቀቃለንና ለራሳችን ክብር እንስጥ። በከበርን ቁጥር ከስሜትና ከግብታዊ የፖለቲካ ትግል ራሳችንን በማረቅ አካሄዳችንን የማስተካከል እድል እናገኛለን። በእንዲህ መልኩ ስንደግፍም ሆነ ስንደገፍ አንወድቅም። በዚህ ዓይነቱ መደጋገፍ ውስጥ ተግባር እንጂ ፕሮፓጋንዳ ቦታው ያንሳል። መተማመን ይሰፍናል። ዛሬ እልል ብለን ነገ ከማዘን እንድናለን።ሁላችንም ራሳችንን ስናከብር የጋራ ራዕይና የጋራ መሪ ለመሰየም አንቸገርም። የሰየምነውንም መሪ አምኖ ለመቀበል ጊዜ አናመነዥግም። ሰባኪና ደቀ መዝሙርም አያስፈልግም። እናም ራስን ማክበር ዋጋው ታላቅ ይሆናል። ከመነዳትም ያድናልና!!

ያገባኛል

ባብዛኛው የአገራችን ጉዳይ ለተወሰኑ ሰዎች የተሰጠ ይመስላል። የተወሰኑ ሰዎች ይናገራሉ።ስለወገኖቻቸውና ስለ አገራቸው ይከራከራሉ። ህዝብ አደራጅተው ለመታገል የበኩላቸውን ሲያደርጉ የሚታዩት እጅግ ጥቂቶች ናቸው። አብዛኛው ህዝብ ግን አድፋጭ ነው። አብዛኛው ምሁር ተመልካች ነው። ህወሃት/ኢህአዴግ ክፉ መንግስት እንደሆነ ከልሒቅ እስከ ደቂቅ ሁሉም ህዝብ፣ የኢህአዴግ አባላትና ደጋፊዎች ጨምሮ ያውቃሉ። ግን ዳር ቆመዋል። ባልተመጣጠነ የኢኮኖሚ ፍሰት አብዛኞች ወደ ባርነት እየተመሙ፣ ልጅ ልጆቻቸውን ለባርነት በስጦታ ለማቅረብ እየገሰገሱ ነው። ልጅ ልጆቻቸው ከተወዳዳሪነት ተለይተው የበይ ተመልካች እንዲሆኑ ሲደረግ “አያገባኝም” የሚሉ እንዴት በረከቱ? ስለ ስርዓቱ ጸያፍነትና የህዝብ ምሬት ብዙ ማለት ይቻላል። ግን አድፋጩ ለምን በዛ? የፖለቲካ መሪዎቻችን ይህንን ጥያቄ መመለስ አለባቸው።አገሪቱና ህዝቧ ያስተማሯቸው የኢትዮጵያ ልጆች ካዳፋቸው የፖለቲካ ድብታ እንዴት እንዲነቁና “ያገባኛል” በሚል መንፋስ እንዲነሱ ምን ይደረግ? “የምሁራን” መንደሮች የያዛቸው እንቅልፍና የአድርባይነት ስሜት እንዴት ይነቀል? ተወደደም ተጠላም ያገባኛል የሚል ህብረተሰብ ሊፈጠር ግድ ነውና ወገብን ጠበቅ አድርጎ መስራት ግድ ይላል።

በቃኝ

ህዝብ የተቃዋሚ ፓርቲዎችን የሚያዳምጠውና የሚከለታተለው አማራጭ ስለሚፈልግ ነው።በፉክክር ተጠቃሚ ለመሆን ነው። ህዝብ የሚጠብቀውን ማድረግ ያልቻሉ አሉ። ሰሞኑን በፓርቲዎች ክርክር ስም ቀርበው ኢህአዴግን እንሞግታለን የሚሉትን ስንሰማ አጥወልውሎናል። ህዝብ እነዚህ ናቸው ተቃዋሚ ብሎ ተስፋ እንዲቆርጥ ሆን ተብሎ የሚሰራ ስራ ቢኖርም እንዴት መናገር፣ የሚናገረውን የማያውቅ፣ ስለምን እንደሚናገር ያልተረዳ፣ እቁብና እድር እንኳን መዳኘት የማይችል ሰው ፓርቲ አቋቁሞ አገር ለመምራት ያስባል? እንዲህ ያሉ ብዙ ናቸው። የምርጫ አዳማቂዎች!! በውጪም አሉ፤ በህክምና ቋንቋ “የሼልፍ ጊዜያቸው ያበቃ” መኖራቸውም፣ መጥፋታቸውም ልዩነት የሌለው ምን አለበት “ሳናውቅ እየረበሽን ኖረናል፤ በቃን” ቢሉ? ሌላም ህይወት አለ። የሚሰሩትን ከጀርባ እየተከተሉ ጤና ከመንሳት “በቃኝ” በማለት ብቻ ለህዝብ ክብር መስጠት የሚቻል ይመስለናል።

ተግባር

ስለ ህወሃት/ኢህአዴግ ብዙ ተብሏል። እንግዳ ብንሆንም እኛን ጨምሮ በየድረገጹ ያልተነገር ነገር የለም። በተለያዩ ማህበራዊ ድሮችና ሞገዶች ዛሬን ጨምሮ ስለ ኢህአዴግ እንሰማለን።የሚሰማው ብዙ ነው። በተግባር የሚታየው ግን እጅግ በጣም፣ እጅግ ጥቂት፣ በጣም በጣም ጥቂት፣ ኢምንት ነው። ወሬው እየገዘፈ ተግባሩ ሲያንስ፣ ሲኮሰምን፣ ሲሟሟ፣ ተስፋ መቁረጥ ያስከትላልና አልሞና መትሮ መንቀሳቀስ ግድ ነው። ዛሬ የሚሰሩ ስህተቶች እስከወዲያኛው የማያገግም ጠባሳ እንዳያትምብን እንጠንቀቅ። መልካም በዓል!!

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Editorial Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • “ሚካኤል ችግኝ ነው። … ችግኝ ይተክላል” ቴዲ አፍሮ June 29, 2022 03:30 am
  • “የእኔን ልጆችና የልጅ ልጆች (22ቱንም) የቀበርኩት እኔ ነኝ” አቶ መሀመድ የሱፍ ከምዕራብ ወለጋ June 28, 2022 01:07 pm
  • የገዳ ሥርዓት እና የኦሮሞ ገዢ መደብ June 20, 2022 11:34 pm
  • “የወልቃይትን ጉዳይ ለድርድር የማናቀርበው ቀይ መስመራችን ነው” ርዕሰ መስተዳድር ይልቃል June 12, 2022 07:09 pm
  • የሰሜን ምዕራብ ዕዝና የአማራ ልዩ ኃይል ተከዜ ክፍለ ጦር ዕውቅናና ሽልማት ተሰጣቸው June 12, 2022 06:21 pm
  • ሀገር በቀል ባህላዊ የግጭት አፈታቶችን በተገቢው በመጠቀም ዘላቂ እርቅና ሰላምን ማምጣት ይቻላል June 12, 2022 05:40 pm
  • የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን በገረጂና በቀበና ያስገነባቸውን የመኖሪያ አፓርትመንቶች አስመረቀ June 12, 2022 05:35 pm
  • በኦነግ ሸኔ ፈርሶ የነበረውና ወታደራዊ ጠቀሜታ ያለው ድልድይ ተጠግኖ አገልግሎት መስጠት ጀመረ June 10, 2022 09:13 am
  • ጃዋር በዳውድ ኢብሣ ቀይ መስመር ተሰመረለት June 8, 2022 12:59 pm
  • ወልቃይት: ቢመረንም ለመዋጥና ራሳችንን ለመመልከት እንሞክር June 8, 2022 11:53 am
  • እብድ ይሻለዋል እንጂ አይድንም፤ ሐጂ ጃዋር አሁን ለምን ብቅ አለ? June 8, 2022 05:59 am
  • ሕዝብ ድምፅ የነፈጋቸው “ፓርቲዎች” የሽግግር መንግሥት ይቋቋም አሉ June 7, 2022 01:11 am
  • “አድጌ እንደናንተ መሆን እፈልጋለሁ” June 5, 2022 06:58 pm
  • በሳምንት ለ100 ያህል ሕሙማን አገልግሎት የሚሰጥ የኩላሊት ዕጥበት ማዕከል ሥራ ጀመረ May 30, 2022 02:20 am
  • የጥቁር አንበሳ ዕጩ መኮንኖች (ካዴቶች) ተመረቁ May 29, 2022 04:01 pm
  • “ኢትዮጵያን መንካት አይቻልም!!” በሚል ቁጭት ነው እየሠራን ያለነው May 29, 2022 01:04 pm
  • “ከሞፈርና ቀንበር ወደ ትራክተር” በሚል መርህ ለአማራ ገበሬዎች የግብርና ሜካናይዜሽን ተሰጠ May 29, 2022 02:02 am
  • ኢትዮ 360 “የወያኔ፣ የጁንታ ሚዲያ ነው” – ባለከዘራው ጄኔራል May 27, 2022 02:51 am
  • “እኛ የምናውቀው ነገር የለም፤ የሚያጣሉን ፖለቲከኞች ናቸው” የአማራ ወዳጃቸውን አደራ ቤት የመለሱ የቅማንት ተወላጅ May 27, 2022 01:40 am
  • ትግራይን አገር እናደርጋለን፤ “በውይይት እና በጦርነት” ሁሉንም ጉዳይ እንቋጫለን – የወንበዴው መሪ ደብረጽዮን May 26, 2022 09:18 am
  • “ሁለቱ የምዕራብ ዕዝ ተዋጊ ዶክተሮች” May 26, 2022 08:19 am
  • ወደ ትህነግ ሊተላለፍ የነበረ አምስት ሚሊዮን ብር ከ20 ተጠርጣሪዎች ጋር ተያዘ May 25, 2022 01:57 am
  • የጦርነቱ ስትራቴጂያዊ እውነታዎች May 19, 2022 09:37 am
  • በጦርነቱ የተጎዱ አካባቢዎችን ለማቋቋም የሚውል የ15 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር ድጋፍ የዓለም ባንክ May 16, 2022 10:22 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2022 · Goolgule