ሰዎች ተጠርጣሪ ወንጀለኛ ናችሁ ተብለው ሲያዙ ይደነግጣሉ፤ ከሁሉ በላይ የሚያስደነግጠው ደግሞ ፖሊስ ጣቢያ ሄደው የሚነሱት ፎቶ ነው። ሕይወታቸውን ሁሉ የሚያበላሽ፤ ዕድሜ ልካቸውን ሲከተላቸው የሚኖር ፎቶ ነው። ብዙዎች ሲነሱ ይበሳጫሉ፤ ሌላ ሰው ለመምሰል ይሞክራሉ፤ ንዴትና ቁጭር ይታይባቸዋል፤ ዓይነቱ እጅግ ብዙ ነው። ዱሮ ላይ ፎቶ ቤት ሄዶ መነሳት ብርቅ ነበር። ፎቶ አንሺ ማለት ከሐኪም በላይ ነው የሚከበረው፤ ሁኑ ያለውን ሁሉ ሆኖ መነሳት የግድ ነው። የማይሆኑ ትዕዛዞችን ሊሰጥ ይችላል፤ "የተናደደ ሳቅ ፊትህ ላይ አሳይ"፤ "ተመስጠህ ተበሳጭ"፤ ወዘተ የሚሉ። ፊንቴክን በተመለከተ ተጠርጥረው የተያዙት የተነሱት ፎቶ ትንሽ ለየት ያለ ነው። ዱሮ "ፎቶ ቤት ሄደህ ፎቶ ትነሳለህ" እንደተባለ ልጅ ፍልቅልቅ ብለው መነሳታቸው ግራ ያጋባል። አንድ ሰው ለብቻው በሺዎች የሚቆጠር ፎቶ … [Read more...] about ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ?
daniel
ኃይለማርያም ደሳለኝ – እንደ ዳንኤል፤ እንደ አክሊሉ ወይስ እንደ መለስ?
አገራችን ኢትዮጵያ በታሪኳ አስር የሚሆኑ ጠቅላይ ሚኒስትሮች አስተዳድረዋታል፡፡ ከእነዚህ መካከል በተለየ ሁኔታ ከሚወሱት አንዱ ጸሐፌ ትዕዛዝ አክሊሉ ሀብተወልድ ናቸው፡፡ በጣልያን ወረራ ወቅት ጠቅላይ ሚኒስትር አክሊሉ በአውሮጳ ያደረጉት ተጋድሎ እጅግ ከፍተኛ ለመሆኑ በተለያዩ ቦታዎች ሲጠቀስ የሚሰማ ነው፡፡ አርበኞቻችን በአገር ውስጥ የሕይወት መስዋዕትነት ሲከፍሉ አክሊሉ ሃብተወልድ በአውሮጳ የከፈሉት መስዋዕትነትና ኢትዮጵያን ለማዳን የሠሩት ሥራ ተጽፎ የማያልቅ ታሪካቸው ነው፡፡ ያላንዳች ማጋነን የዲፕሎማሲውን ሥራ ያለመታከት ከግብ ያደረሱት አክሊሉ ነበሩ፡፡ በተለይ “የአክሊሉ ማስታወሻ” በተባለው የራሳቸው ታሪክ በከፊል የተወሳበት መጽሐፍ ላይ የእንግሊዙ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሆር እና የፈረንሣዩ ጠ/ሚ/ር ላቫል ከኢትዮጵያ ክፍላተሃገራት አብዛኛው የሆነው ሐረር፣ ሲዳሞና ባሌን ጨምሮ … [Read more...] about ኃይለማርያም ደሳለኝ – እንደ ዳንኤል፤ እንደ አክሊሉ ወይስ እንደ መለስ?


