• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ያብለጨለጨ ሁሉ ወርቅ አይደለም!!

January 14, 2013 06:41 am by Editor Leave a Comment

የሁሉም አለቃና የበላይ የሆነውን ሕዝብ ማስደሰት ያኮራል። የሚመሩትን ሕዝብና አገር ከልብ አክብሮ መገኘት ደግሞ ከኩራትም በላይ ነው። ይህንን በኳስ ያበደ ህዝብ፣ አገሩን ከምንም በላይ የሚያፈቀር ህዝብ መወከል ደግሞ ከበጎ ታሪክነቱ በላይ ከሽልማትና ከውዳሴ በላይ ነውና የኢትዮጵያ ልጆች ኩራታችሁ ታላቅ ይሁን። መልካም ዕድል ለአምባሳደሮቻችን!!

ኢትዮጵያዊነት እንዲህ የሚጣፍጥ፣ ማንም ሊወስደውና ሊበርዘው የማይችል ሃያል በረከት መሆኑን ምክንያት ሆነው ላሳዩን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን አባላት ክብር ይሁን ለማለት እንወዳለን። መልካም እድል ለአምባሳደሮቻችን ስንል በቂ ምክንያት ስላለን በፍጹም ኩራት ነው። በእግር ኳስ ፍቅር ለሚቃጠለው የኢትዮጵያ ህዝብ የደስታ ቀን ላመጣችሁ ውድ የኢትዮጵያ ልጆች የምንመኘው መልካም ምኞት ካለፉት የሰላሳ አንድ ዓመታት ውድቀት ጋር የተቀበረውን የድል አድራጊነት ስሜት ስለቀሰቀሳችሁ በበጎ ታሪክ ማህደር ኢትዮጵያ አትዘነጋችሁምና ዕድለኞች ናችሁ። ለዚያውም በዛሬ ዘመን!!

አገራችንን አንቆ የያዛት የኮሙኒዝም “ሙት መንፈስ” መንግስት ያለበትን ሃላፊነት መወጣቱ፣ ዜጎች የድርሻቸውን ማበርከታቸው እንደ ታላቅ ነገር ተወስዶ “የእግር ኳሱ ውጤት የህዳሴው ስኬት አንዱ አካል” ተደርጎ መወሰዱ ፍጹም ተቀባይነት የሌለው ቢሆንም በሽኝታችሁ ወቅት ጠቅላይ ሚኒስትር ሃይለማርያም ደሳለኝን ጨምሮ በርካታ እንግዶች በተገኙበት የተደረገላችሁ አሸኛኛት የጀግና ነውና ማለፊያ የሚያሰኝ ነው።

በመሸለማችሁና በክብር ስለተደረገላችሁ አሸኛኘት የተደሰትነውን ያህል ያዘንበትም ጉዳይ አለ። በስፖርቱ ውስጥ ተመሽገው ለእውቅናቸው የሚቧቀሱ “ጋንግስተሮች” ያየነው ባለፉት ሃያ አንድ ዓመት ጊዜ ውስጥ ነው። ምንጩ በማይታወቅ ሃብት ስፖርቱን የሚረዱ መስለው ፌዴሬሽኑን የከበቡ ጉልበተኞች በአዲስ አበባ ስታዲየም ሲፈጽሙት የነበረው “ወራዳ” ተግባር የሚረሳ አይሆንም። ጋዜጠኞችን ከማስደብደብ ጀምሮ አገር እስከማስቀጣት የደረሱ “ማጅራት መቺዎች” ትልቅ ሰው መስለውና “ትልቅ ሰው” ተደርገው ስናይ በብሄራዊ ቡድናችን የምንኮራውን ያህል እንዲህ ዓይነት ዱርዬዎች የነገሱበት የክብር አሸኛኘት መደረጉ “ማፊያነትን” የማበረታታት ያህል ይሆንብናልና ህዝብ “ያብረቀረቀ ሁሉ ወርቅ ነው” ወደሚለው ድምዳሜ እንዳያመራ ልንመክር እንወዳለን። ሚዲያዎችም ከስሜት ያለፈውን ካሁኑ በማመሳከር መረጃቸውን እንዲያስተላልፉ ለማስታወስ እንወዳለን።

ሌላው ሼኽ መሐመድ ሁሴን አላሙዲ በደርባ ሲሚንቶ ፋብሪካ ስም ለመለገስ ቃል ከገቡት ሌላ “እንዳልታማ ይኸው ቼኩ” በሚል አስቀድመው እንደሚሰጡ የተናገሩትን አስር ሚለዮን ብር መድረክ ላይ መስጠታቸው ተመስገን የሚያሰኝና መጠቀስ ያለበት ነጥብ ይሆንብናል። ከባንክ ያለባቸውን እዳ በመክፈል፣ የጀመሯቸውን ፕሮጀክቶች በመጨረስ፣ አሰራዋለሁ፣ አስገነባዋለሁ በማለት ከዓመታት በፊት ከጓዳ አስከ አደባባይ የገቡትን ቃል፣ በተለይም አዲስ አበባ ስታዲየም ውስጥ “ካንድም ስምንት ስታዲየም እናስገነባለን። አፍሪካ ዋንጫን አገራችን እናዘጋጃለን” በማለት የገቡትን ተስፋና በተለያዩ ገጠሮች ክሊኒክና፣ የሙያ ትምህርት ቤት ለማስገንባት የገቡትን ውዴታ በነካ እጃቸው ለመተግበር፣ አሊያም “ትቼዋለሁ” በማለት አጀንዳውን እንዲዘጉ ለማሳሰብ እንወዳለን። ከሁሉም በላይ ለወደፊቱ ቼክ በመያዝ የፍላጎታቸውን ከማከናወን ውጪ ቃል እንዳይገቡም እንመክራለን። ሰንዳፋ አትሌቲክስ መንደር ግንባታ የዘገየው እንዲሁ ሃያ ዘጠኝ ሚሊዮን ለመስጠት በህጋዊ ቴሌቶን ላይ ቃል ገብተው ዝም በማለታቸው ነውና!!

ለጊዜው ይብቃን። ብሄራዊ ቡድናችን የስነ ምግብ ባለሙያ፣ የስነ ልቦና ባለሙያ፣ የጤና ባለሙያ፣ ወጌሻ፣ ስራ አስኪያጅ፣ የቡድን መሪ፣ አሰልጣኝ በመመደብና እንክብካቤ ተደርጎለት እዚህ ደርሷል። “የተከበራችሁ የኢትዮጵያ ህዝቦች” በማለት በጀመሩት የመሸኛ ንግግራቸው ወቅት እንደተናገሩት፣ በአንድ ወቅት ገናና ከነበርንበት ስልጣኔ ወርደን የድህነት ተምሳሌት መሆናችንን በቁጭት በማንሳት፣ በአፍሪካ በጀመርነው የእግር ኳስ ውድድር ተገፍትረን ላለፉት ሰላሳ አንድ ዓመታት ተመልካች ስለመሆናችን አውስተዋል። “ቀደም ሲል ጥሩ አጥቂ፣ ጥሩ ተከላካይ፣ ጥሩ ግብ ጠባቂ ነበረን” ሲሉም ያለፈውን የነመንግስቱ ወርቁ ዘመን አወድሰዋል። በመቀጠልም ከነሱ ዘመን በኋላ ማለታቸው ነው “መፋዘዝ ነግሶ ቆይቷል” የመፋዘዙ መነሻ ብዙ ቢሆንም፣ ዛሬ ይህ ድብታ ተሰብሯል። ይህንን የውድቀት ስሜት መስበር በራሱ ታላቅ ድል ነው!! የወደፊቱን ውጤት በጸጋ እንቀበላለን። መልካም እድል!! አቶ ሃይለማርያምም ከመሪ በሚጠበቅ ደረጃ የሚመሩትን ህዝብ ደጋግመው በመጥራት ማወደስዎ ያልተለመደና የረሳነው በመሆኑ ለርስዎም ታላቅ ጅምር ለማለት እንወዳለን። በተቋቋመ አጭር ጊዜ ውስጥ ሃያ አራት ሚሊዮን ብር ስፖንሰር ያደረገውን የሔኒከን በደሌ ስፔሻል ቢራ ማሞካሸት ከተስፋዎች ሁሉ በላይ ነውና አግባብ ይሆናል እንላለን!!

በደቡብ አፍሪካ በስደት የምትገኙ ኢትዮጵያውያኖች ቡድናችሁን ለመደገፍ በስፋት መነሳሳታችሁ ተሰምቷል፡፡ ታዋቂው አርቲስት ቴዲ አፍሮም ወደዚያው እንደሚያመራ ተናግሯል፡፡ በየአቅጣጫው የወገኖቻችሁ ድጋፍና መልካም ምኞት ብርታ እንደሚሆናችሁ እናምናለን፡፡

በድጋሚ መልካም ዕድል ለዋሊያዎች!!                                                                                               (ፎቶ: ኮንሰርቫቲቭ ባይት)

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Editorial Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የገዳ ሥርዓት እና የኦሮሞ ገዢ መደብ June 20, 2022 11:34 pm
  • “የወልቃይትን ጉዳይ ለድርድር የማናቀርበው ቀይ መስመራችን ነው” ርዕሰ መስተዳድር ይልቃል June 12, 2022 07:09 pm
  • የሰሜን ምዕራብ ዕዝና የአማራ ልዩ ኃይል ተከዜ ክፍለ ጦር ዕውቅናና ሽልማት ተሰጣቸው June 12, 2022 06:21 pm
  • ሀገር በቀል ባህላዊ የግጭት አፈታቶችን በተገቢው በመጠቀም ዘላቂ እርቅና ሰላምን ማምጣት ይቻላል June 12, 2022 05:40 pm
  • የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን በገረጂና በቀበና ያስገነባቸውን የመኖሪያ አፓርትመንቶች አስመረቀ June 12, 2022 05:35 pm
  • በኦነግ ሸኔ ፈርሶ የነበረውና ወታደራዊ ጠቀሜታ ያለው ድልድይ ተጠግኖ አገልግሎት መስጠት ጀመረ June 10, 2022 09:13 am
  • ጃዋር በዳውድ ኢብሣ ቀይ መስመር ተሰመረለት June 8, 2022 12:59 pm
  • ወልቃይት: ቢመረንም ለመዋጥና ራሳችንን ለመመልከት እንሞክር June 8, 2022 11:53 am
  • እብድ ይሻለዋል እንጂ አይድንም፤ ሐጂ ጃዋር አሁን ለምን ብቅ አለ? June 8, 2022 05:59 am
  • ሕዝብ ድምፅ የነፈጋቸው “ፓርቲዎች” የሽግግር መንግሥት ይቋቋም አሉ June 7, 2022 01:11 am
  • “አድጌ እንደናንተ መሆን እፈልጋለሁ” June 5, 2022 06:58 pm
  • በሳምንት ለ100 ያህል ሕሙማን አገልግሎት የሚሰጥ የኩላሊት ዕጥበት ማዕከል ሥራ ጀመረ May 30, 2022 02:20 am
  • የጥቁር አንበሳ ዕጩ መኮንኖች (ካዴቶች) ተመረቁ May 29, 2022 04:01 pm
  • “ኢትዮጵያን መንካት አይቻልም!!” በሚል ቁጭት ነው እየሠራን ያለነው May 29, 2022 01:04 pm
  • “ከሞፈርና ቀንበር ወደ ትራክተር” በሚል መርህ ለአማራ ገበሬዎች የግብርና ሜካናይዜሽን ተሰጠ May 29, 2022 02:02 am
  • ኢትዮ 360 “የወያኔ፣ የጁንታ ሚዲያ ነው” – ባለከዘራው ጄኔራል May 27, 2022 02:51 am
  • “እኛ የምናውቀው ነገር የለም፤ የሚያጣሉን ፖለቲከኞች ናቸው” የአማራ ወዳጃቸውን አደራ ቤት የመለሱ የቅማንት ተወላጅ May 27, 2022 01:40 am
  • ትግራይን አገር እናደርጋለን፤ “በውይይት እና በጦርነት” ሁሉንም ጉዳይ እንቋጫለን – የወንበዴው መሪ ደብረጽዮን May 26, 2022 09:18 am
  • “ሁለቱ የምዕራብ ዕዝ ተዋጊ ዶክተሮች” May 26, 2022 08:19 am
  • ወደ ትህነግ ሊተላለፍ የነበረ አምስት ሚሊዮን ብር ከ20 ተጠርጣሪዎች ጋር ተያዘ May 25, 2022 01:57 am
  • የጦርነቱ ስትራቴጂያዊ እውነታዎች May 19, 2022 09:37 am
  • በጦርነቱ የተጎዱ አካባቢዎችን ለማቋቋም የሚውል የ15 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር ድጋፍ የዓለም ባንክ May 16, 2022 10:22 am
  • በአዲስ አበባ 1 ሺህ 98 የብሬን እና 2 ሺህ 162 የክላሽ ጥይት ተያዘ May 16, 2022 10:10 am
  • በአዲስ አበባ ከተማ በግለሰብ መኖሪያ ቤት ከ5 ሺህ በላይ የአሜሪካ ዶላርና የተለያዩ አገራት ገንዘቦች ተያዙ May 16, 2022 09:53 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2022 · Goolgule