• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ከመጥበብ ቅድሚያ ለ “እምዬ ኢትዮጵያ”

September 16, 2012 02:01 pm by Editor 1 Comment

የኢትዮጵያ የመከላከያ ኃይል በወገኖቹ የሚፈቀር፣ የሚከበርና አስፈላጊው ሁሉ ድጋፍ የሚደረግለት የህዝብና የአገር አለኝታ ነው። ክቡር ህይወታቸውን ሳይሳሱ ላገራቸው ሲሉ አሳልፈው የሚሰጡትን ውድ የኢትዮጵያ ልጆች የምናከብራቸውና ልንከባከባቸው የሚገባው ልክ ያይናችን ብሌን ያህል ነው። “ክቡር ለውድ ኢትዮጵያዊ ሰማዕታት” ሲባል እንዲሁ መፈክር ለማለት ሳይሆን ከልባችን፣ ከውስጣችን፣ የመስዋዕትነታቸውን ክብር ከቶውንም ልንዘነጋው የሚቻለን ባለመሆኑ ነው። ሌላ ምክንያት የለውም። በቃ!!

የምንኮራበት መከላከያ እንዲኖረን አጥብቀን ስለምንመኝ ያገር ኩራት የሆነው መከላከያችን በክልል፣ በዞንና በጎጥ አንሶና የተዋረደ ስብዕና ተላብሶ እንዲዋቀር ኢትዮጵያውያን አይፈቅዱም። አገራችን ከምትገኝበት የጂኦ ፖለቲካል አቀማመጥ አንጻር ብሄራዊ ስብዕና ያለው፣ ህዝብንና አገርን የሚያስቀድም የመከላከያ ኃይል ሊኖረን ይገባልና፡፡ በጎጥና በዘር ፖለቲካ የተተበተበ አመለካከት ያላቸው ክፍሎች በመከላከያ ሃይላችን እንዲቀልዱበት አንፈቅድም። ክብሩንና ሞገሱን አመናምነው ወገኑን የሚወጋና የሚያፍን የማፍያ ይዘት እንዲኖረው አንፈልግም። የእስካሁኑ ይበቃል!!

ኢህአዴግ ወደ ስልጣን ሲመጣ የአገሪቱን መከላከያ እንደ ጠላት በመቁጠር በታትኖ መሳቂያ አድርጎናል። አየር ኃይላችንና ባህር ኃይላችንን አፍርሶ የወጠጤዎች መጫወቻ አድርጎናል። በዚህ አሳፋሪ ታሪክ አገር አፍሯል። ተዋርዷል። ንጹሃን ትርጉም በሌለው ጦርነት ተማግደዋል። ለአገር ሲዋደቁ የነበሩ ወገኖች እንደጠላት ታይተው እንደ እቃ መጣላቸው ለታሪክ የሚተው አቶ መለስ የፈጸሙት ታሪካዊ ግፍ እንዳለ ሆኖ፣ በባድሜ ወረራ ወቅት አቶ መለስ ያደራጁት የልምድ ጦርና አመራሩ ፍጥረቱ የተበላሸ በመሆኑ ወረራውን መመከት ሲያቅተው በዳግም ጥሪ አገሩን የታደገው ይኸው ወንጀለኛ ተደርጎና “የደርግ ሠራዊት” ተብሎ የተጣለው ወገን ነበር።

ብሄር፣ ክልል፣ ቀበሌ፣ ዘርና ቂም ሳያግደው በፈንጂ ላይ እየተረማመደ አገሩን ነጻ ያወጣ ወገን ዛሬም አይታመንም። ከደጀን ድጋፉን ሰጥቶ ለድል ያበቃ ህዝብ አሁንም ለለቅሶ እንጂ ለሃላፊነት አይታጭም። ከልምድና ከውድቀት መማር የማይችለው ኢህአዴግ ይህንን ህዝብና ወገን ማስቀየሙን ገፍቶበታል። የሰሞኑ ሹመትም የሚያጠናክረው ይህንኑ ነው። ያሳፍራል። ያሳዝናል።

በቅርቡ ኢህአዴግ ሹመት የሰጣቸው ጄኔራሎች ስልጣን የተቀበሉበት አግባብ ትክክል ሆኖ አላገኘነውም። ይህን መሰል ከፍተኛ ወታደራዊ ሹመት የሚቀርበው በአገሪቱ ጠቅላይ ሚኒስትር መሆን ሲገባው ይህ አልተደረገም። ከሁሉም በላይ ደግሞ የተሰጠው ሹመት የአንድ ብሔር (የትግራይ) አባላት የተካተቱበት፣ ፍጹም ወገንተኛ፣ ሌሎች የአገሪቱን ብሄር ብሄረሰቦች ያገለለ፣ የኢትዮጵያ ኩራትና መመኪያ የሆነውን የመከላከያ ሃይል የሚያሳንስ ሆኖ ይሰማናል።

ታላቁን የመከላከያ ሃይል በማሳነስ ከህዝብና ከአባላቱ አመኔታ የሌለው ማድረግ ዞሮ የሚጎዳው ኢህአዴግን ሳይሆን አገራችንን ነው። የመከላከያ ሃይላችን ፍጹም ህዝባዊ፣ ሚዛናዊ፣ ሁሉን አቀፍ፣ ሁሉም ባለቤት በሆነበት ደረጃ ባስቸኳይ ሊደራጅ ይገባል። አቶ መለስ የመተማመን ፖለቲካ በመዘርጋት ዜጎችን ወደ አንድ አመለካት ማሰባሰብ ሲገባቸው ብቻቸውን ለመምራት ካላቸው የኖረ ህልም ተነስተው አገሪቱን ተቋም አልባ በማድረግ የተወሳሰበ ችግር አውርሰውን እሳቸው አርፈዋል። የተቀሩት ከመለስ የስህተት ጎዳና በመውጣት የማስተካከያ ርምጃ ከመውሰድ ይልቅ “በተጀመረው ይቀጥላል” በሚል መዝሙር እያደነቆሩን ነው። ይባስ ብለው የፖለቲካውን ክፍተት ለመሙላት ህወሃት ወታደራዊና የደህንነት ተቋሞቹን እያጠናከራቸው ነው። የራሱን ሰዎች ይሾማል። የራሱን ሰዎች ያስታጥቃል። የራሱን ሰዎች በኢኮኖሚ ያበለጽጋል። የራሱን ሰዎች ከፍ ከፍ ያደርጋል። የራሱን ሰዎች ታማኝ አድርጎ አብዛኞችን ይገፋል። አሁንም እስከመቼ በዚህ መልክ ይቀጥላል?

አቋማችን አንድ ነው። ህወሃት ከብሄራዊ ክብርና ሞገስ ይልቅ ጎጥና ጎሳ ብሶበት የሚርመጠመጥበት አካሄድ ማንንም ተጠቃሚ አያደርግምና ያቁም! አገሪቱን ወደ ወታደራዊ አመራር ለመውስድ የሚያደርገውን ሩጫ ይግታ! ድርጊቱን ኢትዮጵያውያን ሁሉ በህብረት ይቃወሙት! የሁሉም ስህተቶችና የመጥበብ በሽታዎች ዞሮ የሚጎዳው አገራችንን ነውና ቅድሚያ እምዬ ኢትዮጵያን ብቻ!!

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Editorial Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Comments

  1. Yonas says

    September 17, 2012 07:20 am at 7:20 am

    Guys, keep up the good work !

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ከፍተኛ የፋኖ አመራሮች መገደላቸው ተነገረ May 6, 2025 10:40 pm
  • ሃይማኖትን ለተራ የፖለቲካ ሸቀጥ ማዋል ውርደት ነው April 24, 2025 12:43 am
  •  የኬሪያ ኢብራሒም ኑዛዜ “ብትንትናችን ወጥቷል” April 22, 2025 12:08 am
  • ለወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን አመራሮች ወታደራዊ ሥልጠና ተሰጠ April 16, 2025 11:44 pm
  • ዓቅም እንደሌለው የገመገመው ሻዕቢያ ፊቱን ከጦርነት ወደ ዲፕሎማሲ እያዞረ ነው   April 15, 2025 12:32 am
  • “አንድ የፋኖ ተቋም (የእስክንድር) ተመሥርቷል፤ ሌሎቹ ደግሞ እንዲሁ አንድ ተቋም መሥርተው ወደዚህ ይመጡ” አበበ ጢሞ April 11, 2025 12:07 am
  • መለስ (ለገሰ) ዜናዊ – ተዋርዶ ያዋረደን! April 9, 2025 10:28 pm
  • የተከዜ ዘብ: የሉዓላዊነት መጠበቂያ April 8, 2025 11:49 pm
  • አዲስ አበባ አስተዳደር የሪፖርተርን የተዛባ መረጃ ኮነነ፤ ሕጋዊ እርምጃ እወስዳለሁ አለ April 8, 2025 10:06 pm
  • ሀሰተኛውን የሪፖርተር ዘገባ ንግድ ባንክ በጽኑ ተቃወመ፤ እርማትም ጠየቀ April 8, 2025 09:48 pm
  • “ኦሮሚያ ላይ ወይም ሌላ ቦታ ላይ ስታደርገው ከነበረ ትግራይ ወስጥም የማታደርግበት ምንም ምክንያት አይኖርህም” ነው ጌታቸው ረዳ April 7, 2025 10:22 pm
  • “TPLF’s belief in a strong federal government was always tied to its own dominance in Addis Ababa” April 7, 2025 10:15 pm
  • Counter-Video by EBC Challenges EBS Broadcast, Sparks Public Outcry Over Alleged Misinformation March 31, 2025 02:36 am
  • የኤሊያስ መሠረትን ፌክ መረጃ ማን ያጋልጥ? February 19, 2025 06:00 pm
  • አዘርባጃን፡ የሻዕቢያን ሸምቀቆ ማጥበቂያ?! February 19, 2025 12:29 am
  • የአሜሪካ ድምፅ/ቪኦኤ ይዘጋ ተባለ  February 12, 2025 03:37 am
  • የብልፅግና ፓርቲ ሹመኛ ካድሬዎች February 3, 2025 11:07 am
  • ትግሉን የጎዳው የእስክንድር ነጋ አካሄድ February 3, 2025 10:29 am
  • ኤሊያስ መሠረት “ጭምብሉ ዛሬ ወለቀ”፤ ተከፋይ ነው! February 2, 2025 05:32 pm
  • የፋሲል ግንብ እድሳት እንዴት ተካሄደ? የመንጣቱ ምክንያት? January 23, 2025 03:41 pm
  • ታሪካዊዉ የፋሲል ቤተመንግሥት ለምን ነጣ? January 23, 2025 03:04 pm
  • የኢትዮጵያ አየር መንገድ በተወልደ አስተዳደር ዘመን ለተሠራ ስህተት 425ሺ ዶላር ተቀጣ December 14, 2024 01:44 am
  • በትግራይ ከሞትና ከአካላዊ ጉዳት የተረፉት ለስደት ተዳርገዋል November 27, 2024 12:09 pm
  • የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት አሠራሩን እንዲያርም ጥብቅ መመሪያ ተሰጠው November 27, 2024 11:31 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule