• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ከመጥበብ ቅድሚያ ለ “እምዬ ኢትዮጵያ”

September 16, 2012 02:01 pm by Editor 1 Comment

የኢትዮጵያ የመከላከያ ኃይል በወገኖቹ የሚፈቀር፣ የሚከበርና አስፈላጊው ሁሉ ድጋፍ የሚደረግለት የህዝብና የአገር አለኝታ ነው። ክቡር ህይወታቸውን ሳይሳሱ ላገራቸው ሲሉ አሳልፈው የሚሰጡትን ውድ የኢትዮጵያ ልጆች የምናከብራቸውና ልንከባከባቸው የሚገባው ልክ ያይናችን ብሌን ያህል ነው። “ክቡር ለውድ ኢትዮጵያዊ ሰማዕታት” ሲባል እንዲሁ መፈክር ለማለት ሳይሆን ከልባችን፣ ከውስጣችን፣ የመስዋዕትነታቸውን ክብር ከቶውንም ልንዘነጋው የሚቻለን ባለመሆኑ ነው። ሌላ ምክንያት የለውም። በቃ!!

የምንኮራበት መከላከያ እንዲኖረን አጥብቀን ስለምንመኝ ያገር ኩራት የሆነው መከላከያችን በክልል፣ በዞንና በጎጥ አንሶና የተዋረደ ስብዕና ተላብሶ እንዲዋቀር ኢትዮጵያውያን አይፈቅዱም። አገራችን ከምትገኝበት የጂኦ ፖለቲካል አቀማመጥ አንጻር ብሄራዊ ስብዕና ያለው፣ ህዝብንና አገርን የሚያስቀድም የመከላከያ ኃይል ሊኖረን ይገባልና፡፡ በጎጥና በዘር ፖለቲካ የተተበተበ አመለካከት ያላቸው ክፍሎች በመከላከያ ሃይላችን እንዲቀልዱበት አንፈቅድም። ክብሩንና ሞገሱን አመናምነው ወገኑን የሚወጋና የሚያፍን የማፍያ ይዘት እንዲኖረው አንፈልግም። የእስካሁኑ ይበቃል!!

ኢህአዴግ ወደ ስልጣን ሲመጣ የአገሪቱን መከላከያ እንደ ጠላት በመቁጠር በታትኖ መሳቂያ አድርጎናል። አየር ኃይላችንና ባህር ኃይላችንን አፍርሶ የወጠጤዎች መጫወቻ አድርጎናል። በዚህ አሳፋሪ ታሪክ አገር አፍሯል። ተዋርዷል። ንጹሃን ትርጉም በሌለው ጦርነት ተማግደዋል። ለአገር ሲዋደቁ የነበሩ ወገኖች እንደጠላት ታይተው እንደ እቃ መጣላቸው ለታሪክ የሚተው አቶ መለስ የፈጸሙት ታሪካዊ ግፍ እንዳለ ሆኖ፣ በባድሜ ወረራ ወቅት አቶ መለስ ያደራጁት የልምድ ጦርና አመራሩ ፍጥረቱ የተበላሸ በመሆኑ ወረራውን መመከት ሲያቅተው በዳግም ጥሪ አገሩን የታደገው ይኸው ወንጀለኛ ተደርጎና “የደርግ ሠራዊት” ተብሎ የተጣለው ወገን ነበር።

ብሄር፣ ክልል፣ ቀበሌ፣ ዘርና ቂም ሳያግደው በፈንጂ ላይ እየተረማመደ አገሩን ነጻ ያወጣ ወገን ዛሬም አይታመንም። ከደጀን ድጋፉን ሰጥቶ ለድል ያበቃ ህዝብ አሁንም ለለቅሶ እንጂ ለሃላፊነት አይታጭም። ከልምድና ከውድቀት መማር የማይችለው ኢህአዴግ ይህንን ህዝብና ወገን ማስቀየሙን ገፍቶበታል። የሰሞኑ ሹመትም የሚያጠናክረው ይህንኑ ነው። ያሳፍራል። ያሳዝናል።

በቅርቡ ኢህአዴግ ሹመት የሰጣቸው ጄኔራሎች ስልጣን የተቀበሉበት አግባብ ትክክል ሆኖ አላገኘነውም። ይህን መሰል ከፍተኛ ወታደራዊ ሹመት የሚቀርበው በአገሪቱ ጠቅላይ ሚኒስትር መሆን ሲገባው ይህ አልተደረገም። ከሁሉም በላይ ደግሞ የተሰጠው ሹመት የአንድ ብሔር (የትግራይ) አባላት የተካተቱበት፣ ፍጹም ወገንተኛ፣ ሌሎች የአገሪቱን ብሄር ብሄረሰቦች ያገለለ፣ የኢትዮጵያ ኩራትና መመኪያ የሆነውን የመከላከያ ሃይል የሚያሳንስ ሆኖ ይሰማናል።

ታላቁን የመከላከያ ሃይል በማሳነስ ከህዝብና ከአባላቱ አመኔታ የሌለው ማድረግ ዞሮ የሚጎዳው ኢህአዴግን ሳይሆን አገራችንን ነው። የመከላከያ ሃይላችን ፍጹም ህዝባዊ፣ ሚዛናዊ፣ ሁሉን አቀፍ፣ ሁሉም ባለቤት በሆነበት ደረጃ ባስቸኳይ ሊደራጅ ይገባል። አቶ መለስ የመተማመን ፖለቲካ በመዘርጋት ዜጎችን ወደ አንድ አመለካት ማሰባሰብ ሲገባቸው ብቻቸውን ለመምራት ካላቸው የኖረ ህልም ተነስተው አገሪቱን ተቋም አልባ በማድረግ የተወሳሰበ ችግር አውርሰውን እሳቸው አርፈዋል። የተቀሩት ከመለስ የስህተት ጎዳና በመውጣት የማስተካከያ ርምጃ ከመውሰድ ይልቅ “በተጀመረው ይቀጥላል” በሚል መዝሙር እያደነቆሩን ነው። ይባስ ብለው የፖለቲካውን ክፍተት ለመሙላት ህወሃት ወታደራዊና የደህንነት ተቋሞቹን እያጠናከራቸው ነው። የራሱን ሰዎች ይሾማል። የራሱን ሰዎች ያስታጥቃል። የራሱን ሰዎች በኢኮኖሚ ያበለጽጋል። የራሱን ሰዎች ከፍ ከፍ ያደርጋል። የራሱን ሰዎች ታማኝ አድርጎ አብዛኞችን ይገፋል። አሁንም እስከመቼ በዚህ መልክ ይቀጥላል?

አቋማችን አንድ ነው። ህወሃት ከብሄራዊ ክብርና ሞገስ ይልቅ ጎጥና ጎሳ ብሶበት የሚርመጠመጥበት አካሄድ ማንንም ተጠቃሚ አያደርግምና ያቁም! አገሪቱን ወደ ወታደራዊ አመራር ለመውስድ የሚያደርገውን ሩጫ ይግታ! ድርጊቱን ኢትዮጵያውያን ሁሉ በህብረት ይቃወሙት! የሁሉም ስህተቶችና የመጥበብ በሽታዎች ዞሮ የሚጎዳው አገራችንን ነውና ቅድሚያ እምዬ ኢትዮጵያን ብቻ!!

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Editorial Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Comments

  1. Yonas says

    September 17, 2012 07:20 am at 7:20 am

    Guys, keep up the good work !

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule