• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ከመጥበብ ቅድሚያ ለ “እምዬ ኢትዮጵያ”

September 16, 2012 02:01 pm by Editor 1 Comment

የኢትዮጵያ የመከላከያ ኃይል በወገኖቹ የሚፈቀር፣ የሚከበርና አስፈላጊው ሁሉ ድጋፍ የሚደረግለት የህዝብና የአገር አለኝታ ነው። ክቡር ህይወታቸውን ሳይሳሱ ላገራቸው ሲሉ አሳልፈው የሚሰጡትን ውድ የኢትዮጵያ ልጆች የምናከብራቸውና ልንከባከባቸው የሚገባው ልክ ያይናችን ብሌን ያህል ነው። “ክቡር ለውድ ኢትዮጵያዊ ሰማዕታት” ሲባል እንዲሁ መፈክር ለማለት ሳይሆን ከልባችን፣ ከውስጣችን፣ የመስዋዕትነታቸውን ክብር ከቶውንም ልንዘነጋው የሚቻለን ባለመሆኑ ነው። ሌላ ምክንያት የለውም። በቃ!!

የምንኮራበት መከላከያ እንዲኖረን አጥብቀን ስለምንመኝ ያገር ኩራት የሆነው መከላከያችን በክልል፣ በዞንና በጎጥ አንሶና የተዋረደ ስብዕና ተላብሶ እንዲዋቀር ኢትዮጵያውያን አይፈቅዱም። አገራችን ከምትገኝበት የጂኦ ፖለቲካል አቀማመጥ አንጻር ብሄራዊ ስብዕና ያለው፣ ህዝብንና አገርን የሚያስቀድም የመከላከያ ኃይል ሊኖረን ይገባልና፡፡ በጎጥና በዘር ፖለቲካ የተተበተበ አመለካከት ያላቸው ክፍሎች በመከላከያ ሃይላችን እንዲቀልዱበት አንፈቅድም። ክብሩንና ሞገሱን አመናምነው ወገኑን የሚወጋና የሚያፍን የማፍያ ይዘት እንዲኖረው አንፈልግም። የእስካሁኑ ይበቃል!!

ኢህአዴግ ወደ ስልጣን ሲመጣ የአገሪቱን መከላከያ እንደ ጠላት በመቁጠር በታትኖ መሳቂያ አድርጎናል። አየር ኃይላችንና ባህር ኃይላችንን አፍርሶ የወጠጤዎች መጫወቻ አድርጎናል። በዚህ አሳፋሪ ታሪክ አገር አፍሯል። ተዋርዷል። ንጹሃን ትርጉም በሌለው ጦርነት ተማግደዋል። ለአገር ሲዋደቁ የነበሩ ወገኖች እንደጠላት ታይተው እንደ እቃ መጣላቸው ለታሪክ የሚተው አቶ መለስ የፈጸሙት ታሪካዊ ግፍ እንዳለ ሆኖ፣ በባድሜ ወረራ ወቅት አቶ መለስ ያደራጁት የልምድ ጦርና አመራሩ ፍጥረቱ የተበላሸ በመሆኑ ወረራውን መመከት ሲያቅተው በዳግም ጥሪ አገሩን የታደገው ይኸው ወንጀለኛ ተደርጎና “የደርግ ሠራዊት” ተብሎ የተጣለው ወገን ነበር።

ብሄር፣ ክልል፣ ቀበሌ፣ ዘርና ቂም ሳያግደው በፈንጂ ላይ እየተረማመደ አገሩን ነጻ ያወጣ ወገን ዛሬም አይታመንም። ከደጀን ድጋፉን ሰጥቶ ለድል ያበቃ ህዝብ አሁንም ለለቅሶ እንጂ ለሃላፊነት አይታጭም። ከልምድና ከውድቀት መማር የማይችለው ኢህአዴግ ይህንን ህዝብና ወገን ማስቀየሙን ገፍቶበታል። የሰሞኑ ሹመትም የሚያጠናክረው ይህንኑ ነው። ያሳፍራል። ያሳዝናል።

በቅርቡ ኢህአዴግ ሹመት የሰጣቸው ጄኔራሎች ስልጣን የተቀበሉበት አግባብ ትክክል ሆኖ አላገኘነውም። ይህን መሰል ከፍተኛ ወታደራዊ ሹመት የሚቀርበው በአገሪቱ ጠቅላይ ሚኒስትር መሆን ሲገባው ይህ አልተደረገም። ከሁሉም በላይ ደግሞ የተሰጠው ሹመት የአንድ ብሔር (የትግራይ) አባላት የተካተቱበት፣ ፍጹም ወገንተኛ፣ ሌሎች የአገሪቱን ብሄር ብሄረሰቦች ያገለለ፣ የኢትዮጵያ ኩራትና መመኪያ የሆነውን የመከላከያ ሃይል የሚያሳንስ ሆኖ ይሰማናል።

ታላቁን የመከላከያ ሃይል በማሳነስ ከህዝብና ከአባላቱ አመኔታ የሌለው ማድረግ ዞሮ የሚጎዳው ኢህአዴግን ሳይሆን አገራችንን ነው። የመከላከያ ሃይላችን ፍጹም ህዝባዊ፣ ሚዛናዊ፣ ሁሉን አቀፍ፣ ሁሉም ባለቤት በሆነበት ደረጃ ባስቸኳይ ሊደራጅ ይገባል። አቶ መለስ የመተማመን ፖለቲካ በመዘርጋት ዜጎችን ወደ አንድ አመለካት ማሰባሰብ ሲገባቸው ብቻቸውን ለመምራት ካላቸው የኖረ ህልም ተነስተው አገሪቱን ተቋም አልባ በማድረግ የተወሳሰበ ችግር አውርሰውን እሳቸው አርፈዋል። የተቀሩት ከመለስ የስህተት ጎዳና በመውጣት የማስተካከያ ርምጃ ከመውሰድ ይልቅ “በተጀመረው ይቀጥላል” በሚል መዝሙር እያደነቆሩን ነው። ይባስ ብለው የፖለቲካውን ክፍተት ለመሙላት ህወሃት ወታደራዊና የደህንነት ተቋሞቹን እያጠናከራቸው ነው። የራሱን ሰዎች ይሾማል። የራሱን ሰዎች ያስታጥቃል። የራሱን ሰዎች በኢኮኖሚ ያበለጽጋል። የራሱን ሰዎች ከፍ ከፍ ያደርጋል። የራሱን ሰዎች ታማኝ አድርጎ አብዛኞችን ይገፋል። አሁንም እስከመቼ በዚህ መልክ ይቀጥላል?

አቋማችን አንድ ነው። ህወሃት ከብሄራዊ ክብርና ሞገስ ይልቅ ጎጥና ጎሳ ብሶበት የሚርመጠመጥበት አካሄድ ማንንም ተጠቃሚ አያደርግምና ያቁም! አገሪቱን ወደ ወታደራዊ አመራር ለመውስድ የሚያደርገውን ሩጫ ይግታ! ድርጊቱን ኢትዮጵያውያን ሁሉ በህብረት ይቃወሙት! የሁሉም ስህተቶችና የመጥበብ በሽታዎች ዞሮ የሚጎዳው አገራችንን ነውና ቅድሚያ እምዬ ኢትዮጵያን ብቻ!!

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Editorial Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Comments

  1. Yonas says

    September 17, 2012 07:20 am at 7:20 am

    Guys, keep up the good work !

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am
  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule