• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ወፌ ቆመች በሉና!!

September 13, 2012 02:06 pm by Editor 5 Comments

መረጃ ለአንድ ማህበረሰብ ከምንም በላይ አስፈላጊና አንገብጋቢ አጀንዳው ነው። ይህ የሚሆነው በአግባቡ ሚዛኑን ጠብቆ ሲራመድ ብቻ ነው። ስርዓት ጠብቆና በተቻለ መጠን ሙያዊ ስነምግባሩን ተከትሎ መራመድ የሚችል ሚዲያ የወደፊቱን በማየት ህብረተሰብን ያነቃል፣ ያሳስባል፣ ያዘጋጃል፣ የተለያዩ ሃሳቦችን ገደብ ሳያደርግ ያስተናግዳል። በዚህ እሳቤ ላይ ተመስርቶ ለመስራት የተስማማው የጎልጉል ኤዲቶሪያል ቦርድ በአገራችን አዲስ ዓመት ዋዜማ ለንባብ ሲውል ቀዳሚ ጥሪው ያደረገው ለመቆም የሚውተረተር ህጻን የሚበረታታበትን “ወፌ ቆመች” የሚለውን ባህላዊ ቃል ነው። ወፌ ቆመች!!

ሚዲያ እንደ ንፋስ ከነፈሰና በስማ በለው ከነጎደ ስቶ ከማሳቱ በላይ ማህበረሰብን ሚዛን በሌለውና በተራ አሉባልታ በማዥጎርጎር ቀላል የማይባል የስሜት ግሽበት ያስከትላል ብለው ከሚያምኑት ክፍሎች ተርታ ራሳችንን እንመድባለን። በተራ ዘለፋና ስድብ አዘል መልዕክቶች የትኛውንም ዓይነት አስተሳሰብና የትኛውም ዓይነት አቋም ያላቸውን ክፍሎች ማስተማር፣ ማረምና መገሰጽ አስቸጋሪ ነው ብለን ስለምናምን ለመቆም የምንውተረተረው ከዚህ የጸና ዓላማችን ዝንፍ ሳንል እንደሆነ ለምታቋቁሙን አስቀድመን ለማሳወቅ እንወዳለን።

ሁላችንም እንደምንረዳው በአሁኑ ወቅት በስፋት የሚስተዋለው የመሞጋገስ አካሄድ ብቻውን ወደሚፈለገው ግብ ያደርሳል ብለን ከቶውንም አናምንም። ኢትዮጵያን “አውራ ፓርቲ ነኝ” በማለት ያለ ህዝብ ይሁንታ እየመራ ያለው ኢህአዴግ ብቻ ሳይሆን የተቃዋሚው ጎራም  ሲሳሳት – ተስተካከል፣ ባለበት ሲረግጥ – ተንቀሳቀስ፣ ሲረጋና ሲጋገር – ሩጥ፣ ከህዝብ ሲርቅ – ወደ ህዝብ ተጠጋ፣ ውስጣዊ ዴሞክራሲ ሲጎድለው – ተመለስ፣ በስሜት ሲነዳ – አስተውል፣ ራዕይ አልባ ሲሆን ራዕይ ሰንቅ፣ ቅርብ አዳሪ ሲሆን ሩቅ ተጓዥ ሁን… አልሰማ ሲልና ወደ በረዶ አለትነት ተቀይሮ የለውጥ ጠረን ካጣ በቃህ፣ ለተተኪ አስረክብ… የሚል ከወተት እስከ አጥንት የጠጠረ ሂስ ሊቀርብበት ይገባል ብለን እናምናለን።

አገራችንና ህዝቧ የተቆፈረላቸው የጎሳና የዘር ጉድጓድ አፉ ሰፊ፣ ጥልቀቱ የራቀ፣ መጠኑ ትልቅ በመሆኑ ይህንን ገደል የመድፈን ስራ ከቶውንም ዕረፍት የሚሰጥ ባለመሆኑ ዜጎች ከጎሳ ይልቅ ለመፈቃቀርና ለሰብዓዊነት ቅድሚያ እንዲሰጡ ማስተማር ከየትኛውም አገር ወዳድ ዜጋ የሚጠበቅ እንደሆነ ይሰማናል። በአንድ ሰው ነፍስና የሞት ወለል ላይ የተቸነከረችው አገራችን ከሙት መንፈስ አመራርና ራዕይ ውጪ ሌላ አማራጭ እንደሌላት በተደጋጋሚ በሃዘን ድባብ ውስጥ የሰነበቱት የኢህአዴግ አመራሮች ነግረውናል። አገሪቱ በሙት መንፈስ እንደምትመራም አረጋግጠውልናል። አገር መሸጥና የአገርን ታሪክ ማጉደል፤ ከሌላው ህዝብ ላይ እየዘረፉ የራስን ቆዳ ማስዋብ፣ አገርን በዘርና በጎሳ በልቶ ማባላት፣ የባህር በሯንና መሬቷን መሸጥ፣ የሚበሉና የበይ ተመልካች የሆነ ህዝብ መፍጠር፣ የፕሬስ ነጻነትን ማሸግ፣ የመናገርና የመሰብሰብን ተፈጥሯዊ መብት መዝጋት፣ ተቃዋሚ ፖለቲከኞችን ማሳደድ፣ ጋዜጠኞችንና ንጹሃን ዜጎችን ማሰር፣ አገር ወዳዶችን መግረፍና ማሰቃየት፣ አፈናና የአፈና ተቋማትን በማደራጀት ስልጣንን በአንድ ብሄረሰብ ዙሪያና በቤተሰብ በማካለል ዜጎችን ባይተዋር ማድረግ… እንደ ታላቅ ጀብድና ዝና ተቆጥሮ “አጽምህ ይምራን” ሲባል መስማት እጅግ አስነዋሪና ከባድ አገራዊ ውድቀት ነው።

ኢህአዴግ የሚያሰራጨው ፕሮፖጋንዳ ሰለባ ያደረገው ህዝብ፣ ሰለባ ካደረገው የፕሮፖጋንዳ ባህር ይላቀቅ ዘንድ አበክሮ መስራት ካልተቻለ ሁሉንም ነገር አዳጋች ያደርገዋልና “ወፌ ቆመች” በሉን ስንል እንዲሁ ተረት ለማስታወስ አይደለም። ኢህአዴግ አማራጭ መገናኛዎች እንዳያብቡ በውስጥም ሆነ በውጭ አገር ከፍተኛ ሃብት እያፈሰሰ የሚዋጋው የሚዲያን ኃይል ስለሚረዳው ነውና ይህ እልህ እኛም ዘንድ ሊፈጠር ግድ ይላል። በተረትና በፉከራ የሚፈጠር አንድም ነገር የለምና ከወዲሁ መድረሻውንና መነሻውን ያስቀመጠ የሚዲያ አብዮት ሊቀጣጠል ይገባል። ህዝባችንን በባርነት ከያዘው የኢህአዴግ ፕሮፖጋንዳ ለማላቀቅ አስተውሎ መስራት ከወፌ ቆመች ያለፈ ታላቅ ተግባር ነውና ጎልጉልን እነሆ። ጎልጉል የዘመቻችን የመጀመሪያዋ መሳሪያ ናት። አሁንም ወፌ ቆመች!!

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Editorial Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Comments

  1. Ewnetu says

    September 11, 2012 12:32 pm at 12:32 pm

    Dear brothers and sisters of Golgul,
    we wish you a successful start and wish you strength in the bumpy road to democracy and freedom. We hope that you do not remain a site which only “copies and pastes” every cram which appeared on the internet. Ethiopians now above all need true and meaningful information that leads to a more strategic struggle.
    We also hope that you do not fall in the trap of woyanes which dissiminate misinformation labled as “sources from within”.
    We expect that the disinformed, brainwashed and blinded woyane supporters are not going to prolong the agony of ethiopian people.
    Dear Golguls Welcome to the ethiopian struggle for freedom!!

    Reply
  2. Girmu says

    September 12, 2012 10:12 am at 10:12 am

    Dear Golgul editor,I like your effort,but you are one of those guys who prolonged Melese Zenawi`s regime and still you are doing it by rejecting the oppositions unity.I do not know for how long you are going to make sweet words reiteration.Rethorics and gossple words by themselves won`t bring any change.Think about what you are doing,question yourselve what you are doing,your preach with sweet words tactic is over,now you need to practical shift or paradiam.Do not think this advise is from the enemies camp,it is from one of the Ethiopian nationalists

    Reply
  3. Kebena says

    September 12, 2012 10:38 am at 10:38 am

    Hi there,
    It is a good begining and hope you will be different from other in providing ture information that cover all parts of Ethiopia. Pls try not to concetrate on the news from capital city but try to cover the real situation of people who are living in country side as well.
    Wish you all the best.

    Reply
  4. tesfaye says

    September 13, 2012 06:50 pm at 6:50 pm

    is good place send any articles to my email address

    Reply
  5. Dereje Mengesha says

    September 19, 2012 12:35 pm at 12:35 pm

    It is a good begning and we must break the information monopoly of TPLF/EPRDF. g o go go

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • በአዲስ አበባ የተወረረው መሬት፣ ባለቤት አልባ ቤቶችና ሕንጻዎች ይፋ ሆኑ January 26, 2021 11:16 am
  • የብሔራዊ መረጃና ደህንነት አክቲቪስቶችን በሕግ ተጠያቂ አደርጋለሁ አለ January 26, 2021 10:32 am
  • የሰባት ቤት አገው የፈረሰኞች ማኅበር 81ኛ የምስረታ በዓል January 26, 2021 07:17 am
  • በጋምቤላ ህወሃትንና ኦነግ ሸኔን ትረዳላችሁ ተብለው የታሰሩ እንዲፈቱ ተጠየቀ January 25, 2021 03:07 pm
  • “…ሰብዓዊ እርዳታ እየቀረበ አይደለም የሚሉ አካላት የፖለቲካ ትርፍ ለማግኘት ነው” – ዶ/ር ሙሉ ነጋ January 25, 2021 01:02 pm
  • የሶማሌና ኦሮሚያ መሥተዳድሮች ወሰንን በተመለከተ የሰላምና የጋራ ልማት ስምምነት አደረጉ January 25, 2021 12:50 pm
  • 125ተኛውን የአድዋ ድል በዓል በድምቀት ሊከበር ነው January 25, 2021 09:34 am
  • በመቀሌ ከ350 ሚሊዮን ብር በላይ የህክምና ግብዓቶች ክምችት መኖሩ ታወቀ January 25, 2021 02:47 am
  • ዊንጉ አፍሪካ (wingu.africa) በዓይነቱ የመጀመሪያ የሆነ የመረጃ ማዕከል ሊገነባ ነው January 24, 2021 01:23 pm
  • ኢትዮጵያ ድሮኖችን ማምረት ልትጀምር ነው January 24, 2021 02:40 am
  • የአየለ ጫሚሶ ቅንጅት ፈረሰ January 18, 2021 02:31 pm
  • ህወሓት ተሠረዘ!!! January 18, 2021 01:32 pm
  • ዓሲምባ፣ ሣልሳዊ ወያኔና ባይቶና ከመፍረሳቸው በፊት ማብራሪያ እንዲሰጡ ተነገራቸው January 18, 2021 01:00 pm
  • ቤተሰቦች አስከሬን መውሰድ እንደሚችሉ ተነገረ January 14, 2021 06:48 pm
  • ስብሃት፤ “ከሞትን ቆይተናል፤ … አሁን የቀብር ሥነ-ስርዓታችን” እየተፈጸመ ነው January 14, 2021 01:37 pm
  • “ተመልሰን እንነሳለን” ያሉት ህወሓቶች ተመልሰው ወደማይነሱበት ተሸኙ January 13, 2021 01:12 pm
  • አፋር ነፃ አውጪ (ኡጉጉሙን) ለመጠቀም የታቀደው የህወሃት ሤራ ከሽፏል January 13, 2021 01:10 pm
  • ህወሃትን ወደ ጅቡቲ ለማሻገር ሲሰሩ የነበሩ የአፋር ታጣቂዎች በሰላም ወደ ክልሉ ገቡ January 13, 2021 06:47 am
  • በታህሳስ ወር ብቻ ከ344 ሚሊየን ብር በላይ የኮንትሮባንድ ዕቃ ተያዘ January 13, 2021 06:10 am
  • የብልፅግና ፓርቲ ቀጣይ ፈተና ምን ሊሆን ይችላል? January 13, 2021 04:10 am
  • ለትምህርት እንዲሆነን January 11, 2021 01:20 pm
  • “ከተቀበሩበት የጃርት ጉድጓድ ነው ያወጣናቸው” መቶ አለቃ ስዩም ቱርቦ January 11, 2021 12:11 pm
  • የተደመሰሱና በቁጥጥር ሥር የዋሉ የወንበዴው አባላት ይፋ ሆነ January 7, 2021 01:16 pm
  • ዐቢይና መኮንኖቹ በመቀሌ፤ “ድሉ የመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ነው” December 13, 2020 02:36 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2021 · Goolgule