በጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ ተስፋን-በጥንቃቄ (cautious optimism) ካነገቡት ሰዎች አንዱ ነኝ። የተስፋዬ መሠረቶች ጠቅላይ ሚኒስትሩ ወደ ሥልጣን የመጡበት መንገድ፣ የገቧቸው ቃልኪዳኖች እና አሁን የታየው መረጋጋት ናቸው። አሁን የታየው መረጋጋት ስል የቄሮዎች የአደባባይ ተቃውሞ መቆሙን ማለቴ አይደለም። ተቃዋሚዎችን እያሳደዱ መከታተል፣ ማዋከብ እና ማሰር ርቀን ሳንሔድ አምና ከነበረው አንፃር እንኳ ልዩነቱ የትየለሌ ነው። ለዚህ የራሴን ስሜት እና ተሞክሮ ነው በምሳሌነት የማቀርበው። በፊትም አሁንም ሐሳቤን በነጻነት እገልጻለሁ። ነገር ግን አምና እና ካቻምና ከያንዳንዱ ጽሑፎቼ/ንግግሮቼ ቀጥሎ እስር ይመጣል እያልኩ እየሰጋሁ ነበር የማደርገው። አሁን ምን ያክል ይዘልቃል የሚለው ቢያሰጋኝም እታሰራለሁ እያልኩ በየደቂቃው አልባትትም። በፊት ሲያስሩ፣ ሲያዋክቡ እና ሲከስሱ ከነበሩት … [Read more...] about ጠቅላይ ሚኒስትሩን ከራሳቸው ማዳን!
Archives for April 2018
ከሁሉም የፖለቲካ ሃይሎች ጋር ግልጽ ውይይትና ድርድር ሊደረግ ይገባል!
ዶ/ር አብይ የኦህዴድ ጽ/ቤት አላፊ በነበሩበት ወቅት ኦህዴድ ሁሉንም ሰላም ወዳድ ዜጋን ያስደሰተ ጥሪ በሀገር ውስጥም ሆነ በውጪ ላሉ ተቃዋሚዎች አቅርቦ ነበር። ይህ ጥሪ ያለ ምንም ቅድመ ሁኔታ የቀረበ በመሆኑ አንዳንድ በኦሮሞ ስም የሚታገሉ በውጪም በውስጥም ያሉ ተቃዋሚዎች በደስታ የተቀበሉት ነበር። ነገር ግን ይህ የኦህዴድ ጥሪ ምንም ያህል ለሀገሪቱ ሰላም ከፍተኛ አስተዋጽኦ ያለው ቢሆንም ያለ ኢህአዴግ አሺታ ሊሳካ እንደማይችል የገመቱ ነበሩ። ዶ/ር አብይ ወደ ስልጣን በመጡ የመጀመሪያዋ ቀን በፓርላማው ተገኝተው ባደረጉት ንግግር ኦህዴድ ለተቃዋሚዎች ካቀረበው ጥሪ ጋር ተመሳሳይነት ያለውን ሃሳብ ተናግረው ነበር። ጠቅላይ ሚንስተሩ በኢትዮጵያ ጉዳይ “በተለያየ መልኩ” ከሚንቀሳቀሱ የፖለቲካ ሀይሎች ጋር አብሮ ለመስራት እንደሚፈልጉ ጠቅሰው ነበር። የዲስፖራው ፖለቲካ ብዙውን … [Read more...] about ከሁሉም የፖለቲካ ሃይሎች ጋር ግልጽ ውይይትና ድርድር ሊደረግ ይገባል!
“EFFORTን” መውረስ የኢኮኖሚውን ጥገኛ ተውሳክ እንደማስወገድ ነው!
ትላንት በፌስቡክ ገፄ ላይ የትእምት (EFFORT) ድርጅቶች በመንግስት መወረስ እንዳለባቸው ለመጠቆም ሞክሬ ነበር። ለዚህ ያቀረብኳቸው ምክንያቶችና ማስረጃዎች እንዳሉ ሆነው እነዚህን ድርጅቶች መውረስና ወደ ግል እንዲዛወሩ ማድረግ ምን ፋይዳ አለው? በሀገሪቱ ፖለቲካና ኢኮኖሚ ላይ ምን ዓይነት አሉታዊ ሆነ አዎንታዊ ተፅዕኖ ሊፈጥር ይችላል? እና ሌሎች ተያያዥ ጉዳዮችን በዝርዝር መመልከት ያስፈልጋል። በቅድሚያ ግን ስለ ትእምት (EFFORT) ድርጅቶች አጠቃላይ ባህሪ የተወሰነ ግንዛቤ ሊኖረን ይገባል። ለዚህ ደግሞ ከትእምት (EFFORT) ድርጅቶች የመሰቦ ሲሚንቶ ፋብሪካን እንደ ማሳያ በመውሰድ እንመልከት። በመቐለ ዩኒቨርሲቲ በቢዝነስ አመራር ሙያ (Business Administration) የሁለተኛ ዲግሪ ትምህርት በምማርበት ወቅት “Operation Management” የሚባለውን ኮርስ … [Read more...] about “EFFORTን” መውረስ የኢኮኖሚውን ጥገኛ ተውሳክ እንደማስወገድ ነው!
EFFORTን መውረስ ለዶ/ር አብይ ቀዳሚ ተግባር ነው!!!
ዶ/ር አብይ ጠ/ሚኒስትር ሆነው የተመረጡ ዕለት ባደረጉት ንግግር የሀገሪቱን ኢኮኖሚ እድገት እና ፍትሃዊ የሃብት ክፍፍል ለማረጋገጥ፣ በተለይ አዳዲስ ባለሃብቶችን እንዲፈጠሩ ቅድሚያ ሰጥተው እንደሚሰሩ ገልፀዋል። ይህን እውን ለማድረግ የጠ/ሚኒስትሩ የመጀመሪያ ተግባር መሆን ያለበት #EFFORTን በመውረስ ወደ ግል ባለሃብቶች ማዘዋወር (privatize) ነው። ምክንያቱም፣ 1ኛ) ለሀገሪቱ የኢንዱስትሪ ልማትና እድገት፣ በተለይ አዳዲስ ባለሃብቶችን በመፍጠሩ ረገድ ዋና እንቅፋት መሆናቸው በዚህ ጥናታዊ ፅሁፍ በዝርዝር ተገልጿል። 2ኛ) #በአርከበ_ዕቁባይ መሪነት ተግባራዊ የተደረገው የሀገሪቱ ኢንዱስትሪ ፖሊስ የEFFORT ድርጅቶችን ተጠቃሚ በማድረግና የግል ቢዝነስ ተቋማትን እድገት በማቀጨጭ ላይ የተመሠረተ ስለመሆኑ ይህን ፅሁፍ ያንብቡ። 3ኛ፦ የEFFORT መነሻ ካፒታል 100ሚሊዮን … [Read more...] about EFFORTን መውረስ ለዶ/ር አብይ ቀዳሚ ተግባር ነው!!!
ይድረስ የፈጣሪን ስም ለጠሩ ዶ/ር አብይ አህመድ
በ 44 ዓመታት ጊዜ ውስጥ የኢትዮጵያ መሪ በመሆን ለመጀመሪያ ጊዜ “ፈጣሪ ኢትዮጵያንና ሕዝቦቿን ይባርክ” እያሉ ንግግርዎን ሲያሳርጉ አይቶ ሕዝበ ኢትዮጵያ በደስታ ተሞልቷል። እኔ ግን እያሉ ያሉት ይህ የማሳረጊያ ቃል በሕዝብ ፊት ብቻ ሳይሆን በአምላክ ፊት ምንና ምንን በሃላፊነት ሊያስጠይቅዎ እንደሚችል የነገሩ ክብደት እጅግ አሳስቦኛል። የፈጣሪ ስም ከተነሳ ዘንዳ፥ ይህ ፈጣሪ የሚሰጠን በረከት ምንነት ይታወቅ ዘንድ ያስፈልጋል። “ኢትዮጵያ እጆቿን ወደ እግዚአብሔር ትዘረጋለች” ሲባል ዝንተ አለም አሳልፈን ዛሬን ደረስን። እስከ ዛሬ “ትዘረጋለች” ከማለት አልፈን “ዘረጋች” ወደማለት ሳንሸጋገር ሦስት ሽህ ዓመታት ጠበቅን። በዚህ ፅሁፌ ይህ 3000 ዓመታት ያስቆጠረው ትንቢት ተፈፀመ የሚያስብለው ሁኔታ ምን እንደሆነና፤ የፈጣሪን በረከት የጠየቁት እርስዎ ስለዚህ በረከት ሊኖርዎት … [Read more...] about ይድረስ የፈጣሪን ስም ለጠሩ ዶ/ር አብይ አህመድ
“ቃል ጉልበት አለው፤ ይተክላል ይነቅላል፤ ትውልድ ይፈጥራል ትውልድ ያጠፋል፤ ፍቅር ይዘራል ጥላቻ ይዘራል”
“ቃል ካልወጣ በአእምሮ ውስጥ ቢብሰለሰል ብቻውን ሀሳብ ሊሆን አይችልም።” ጠ/ሚኒስትር አብይ አህመድ (ዶ/ር) የኮርያ ብሮድካስት ኮርፖሬሽን የደቡብ ኮርያው ፕሬዚዳንት ወደ ኢትዮጵያ ከመምጣታቸው አስቀድሞ ኢንተርቪው ሊያደርጉኝ መጥተው ከብዙ ውይይት በሁዋላ “እንዴት ስለስፔስ ታስባላችሁ? እናንተ ድሃ ሀገር ናችሁ። ህዝባችሁ አግራሪያን (አርሶ አደር) ስለሆነ ማሰብ ያለባችሁ አግሪካልቸር እንዴት መሻሻል እንዳለበት አይደለም እንዴ?” ብሎ በጣም ደፋር ወጣት ጋዜጠኛ ጠየቀኝ። የመለስኩለት መልስም እንዲህ ነበር፤- እናንተን ነፃ ለማውጣት ወደ ኮርያ ስንዘምት ጠቅላላ ጦርነቱን የመራው ሰውዬ ጄኔራል ማካርቲ ይባላል። አራት ኮከብ ማዕረግ ያለው የአሜሪካን ጄኔራል ነው። ጄኔራል ማካርቲ በሁለተኛው የዓለም ጦርነት ጃፓንን ለመውረር ጦር አዝምቶ የገባና የኮርያ የርስ በርስ ጦርነት ሲነሳ … [Read more...] about “ቃል ጉልበት አለው፤ ይተክላል ይነቅላል፤ ትውልድ ይፈጥራል ትውልድ ያጠፋል፤ ፍቅር ይዘራል ጥላቻ ይዘራል”
ቋንቋን በቋንቋ
ስለ ቋንቋ የተለያዩ እይታዎች መኖራቸው አዲስ አይደለም። የሚገርመው ይልቅ፣ ብዙዎች እንደ ሹምና አቡን ትእዛዝ ሲሰጣጡ ማየት ነው። ትእዛዙን ማን፣ እንዴት ይፈጽም? እይታዎችን ማቀራረብና መተግበርስ ይቻላል? መቸ በምን ቅደም ተከተል? ወዘተ። ይህን ያሰቡበት ቢኖሩ ድምጻቸው አልተሰማም። የራስን አጉልቶ፣ የሌላኛውን ማድበስበስ የተለመደ በመሆኑ፣ የጽሑፌ ይዘት ለያንዳንዱ ምላሽ ከመስጠት ይልቅ፣ የተዘነጉ ጥቃቅን አሳቦችን ማነጋገር ይሆናል። ቋንቋ ቢያንስ ሀ/ ድንበር ተሻጋሪ መሆን ይኖርበታል፤ አማርኛ ተናጋሪ፣ እርስ በርሱ ብቻ ከሆነ፣ ከኬላው ውጭ በምን ይግባባል? ለ/ ድንበር ተሻግረን እንግሊዝኛ፣ አማርኛ፣ ወዘተ፣ የቆነጠርን ቢያንስ አኗኗራችንን ለማሻሻል እንደ ሆነ አንርሳ ሐ/ ቋንቋ ተሻጋሪ እንዲሆን፣ ድልድይ የሚሆን ቋንቋ ይሻል። አማርኛ ድልድይ ነው። እርግጥ፣ ሁሉን ቋንቋ ማወቅ … [Read more...] about ቋንቋን በቋንቋ
ኤች አር 128 ዓለም አቀፍ ግንኙነትና የኛ ሚና
በቅርቡ አሜሪካ የሚኖሩት ወገኖቻችን በተባበረ ጥረታቸው ለብዙ ጊዜ ሲዋጉለት የነበረውንና የኢትዮጵያን መንግሥት ቢያንስ ቢያንስ ወደ ተከላካይነት ሊያወርደው ይችላል ተብሎ የታመነበት የአሜሪካ ኮንግረስ ውሳኔ በአደባባይ ለመላው ዓለም ሲታወጅ የተሰማን ደስታ ወሰን አልነበረውም። እኛ የአንጋፋው ትውልድ፣ ከሩቅ ሆነን ሲመቸን ብቻ “በርቱ” እያልን “ድጋፍ” ስንሰጣቸው የነበርነውን ይህን ያህል ያስደስተን፣ በቦታው ሆነው ሌት ተቀን ሳይታክቱ ከስቴት ወደ ስቴት እየተደዋወሉ በተወካዮቻቸው የኮንግረስ አባላት ዘንድ በመደወልና በመጻፍ ተጽዕኖ እያሳደሩ በመጨረሻ ላይ የለፉለት ግቡን ሲመታ ምንኛ እንደተደሰቱ ገምቼ እኔም በጣም ተደሰትኩላቸው። ብዙዎቹ እንደነገሩኝ ከሆነ፣ ያን ቀን በጥዋት ተነስተው ወደ ካፒቶል በማምራት፣ አሰልቺውን የጸጥታ ምርመራ በትዕግሥት አልፈው ወደ ኮንግሬስ ተወካዮቻቸው ቢሮ … [Read more...] about ኤች አር 128 ዓለም አቀፍ ግንኙነትና የኛ ሚና
የአማራ ብሔረተኝነት ለስር ነቀል ለውጥ መሰረት፣ ለኢትዮጵያም መዳኛ መድሃኒት ነው
የአማራን ህዝብ በቃላት መሸንገል የማይቻልበት ደረጃ ተደርሷል። የህዝቡ ንቃተ ህሊናው በስልጣን ላይ ከሚገኙት ከፓለቲከኞቹ ቀድሞ ሄዷል። ወጣቱ የነብር ጣቱ - እሳት ትውልድ ሆኗል። ገና ከመነሻው ወያኔ/ትህነግ በ1967 ዓ.ም ባፀደቀው በማኒፌስቶው ላይ አማራ ጠላቴ ነው በማለት የአማራ ህዝብ መቃብር ላይ የትግራይን ሪፕብሊክ እመሰርታለሁ፣ የአማራን ህዝብ ማህበራዊ ሰላም አሳጠዋለሁ ብሎ ሸፈተ። በርሃ ሳለ በአማራው ተወላጅ ላይ ከፍተኛ በደልና ወንጀል ሲፈጽም ከቅምየ በኋላ በተለት የአለም አቀፍና የሃገር ውስጥ ሁኔታዎች በደርግ መንግስት ላይ በፈጠሩት ጫና በለስ ቀንቶት የመንግስት ስልጣን ከተቆጣጠረበት ከ1983 ዓ.ም ጀምሮ በጥናትና በእቅድ በተጠናከረ ሁኔታ በአማራ ህዝብ ላይ የሙፈጽመውን በደልና ቀጠለበት። ጫካ እያለ ያፀደቀውን ፀረ አማራ ፕሮግራሙን ለማታለያነት ከካናዳና ከሌሎች … [Read more...] about የአማራ ብሔረተኝነት ለስር ነቀል ለውጥ መሰረት፣ ለኢትዮጵያም መዳኛ መድሃኒት ነው
የዶ/ር ዓቢይን “መጨረሻ ለማየት ቢያንስ ስድስት ወራት እንጠብቅ”
ዶር. ዓቢይና አቶ ለማ መገርሳ በኢትዮጵያ መድረክ ላይ መታየት ሲጀምሩ ኢትዮጵያ የተአምር አገር መሆንዋን አስታወስሁና እግዚአብሔር ፊቱን ወደኢትዮጵያ መመለሱን ተረዳሁ፤ ከዚያም በላይ ያለፈው ጠቅላይ ሚኒስትር እናቱን በመውቀስና በመመጻደቅ ጀመረ፤ አዲሱ ደግሞ እናቱን በማወደስ መጀመሩ ብቻ ሳይሆን በእግዚአብሔር ላይ ያለውን እምነት በአደባባይ ደጋግሞ በመግለጹ አከበርሁት፤ አከብረዋለሁ። ከዚህ በፊት ሦስት ጊዜ በፌስቡክ የጻፍሁትን ልድገመው፤ አንድ፤ በ1965 በወሎ ችጋር ዘመን በቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ መምህራንና ተማሪዎች እርዳታ ለማድረግ በምንሯሯጥበት ጊዜ አንዳንድ የኢሕአፓ አባሎች ለተራቡት እርዳታ መሰብሰብ አብዮቱ እንዳይመጣ ማድረግ ነው እያሉ ይቃወሙን ነበር፤ ነፍሱን ይማረውና አብርሃም ደሞዝና እኔ ተቆጥተንና አስፈራርተን አደብ እንዲገዙ አድርገናቸው ነበር፤ ዛሬ ደግሞ … [Read more...] about የዶ/ር ዓቢይን “መጨረሻ ለማየት ቢያንስ ስድስት ወራት እንጠብቅ”