• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ከሁሉም የፖለቲካ ሃይሎች ጋር ግልጽ ውይይትና ድርድር ሊደረግ ይገባል!

April 29, 2018 08:10 am by Editor Leave a Comment

ዶ/ር አብይ የኦህዴድ ጽ/ቤት አላፊ በነበሩበት ወቅት ኦህዴድ ሁሉንም ሰላም ወዳድ ዜጋን ያስደሰተ ጥሪ በሀገር ውስጥም ሆነ በውጪ ላሉ ተቃዋሚዎች አቅርቦ ነበር። ይህ ጥሪ ያለ ምንም ቅድመ ሁኔታ  የቀረበ በመሆኑ አንዳንድ በኦሮሞ ስም የሚታገሉ በውጪም  በውስጥም ያሉ ተቃዋሚዎች በደስታ የተቀበሉት ነበር። ነገር ግን ይህ የኦህዴድ ጥሪ ምንም ያህል ለሀገሪቱ ሰላም  ከፍተኛ አስተዋጽኦ ያለው ቢሆንም ያለ ኢህአዴግ አሺታ ሊሳካ እንደማይችል የገመቱ ነበሩ።

ዶ/ር አብይ ወደ ስልጣን በመጡ የመጀመሪያዋ ቀን በፓርላማው ተገኝተው ባደረጉት ንግግር ኦህዴድ ለተቃዋሚዎች ካቀረበው ጥሪ ጋር ተመሳሳይነት ያለውን ሃሳብ ተናግረው ነበር። ጠቅላይ ሚንስተሩ በኢትዮጵያ ጉዳይ “በተለያየ መልኩ” ከሚንቀሳቀሱ የፖለቲካ ሀይሎች ጋር አብሮ ለመስራት እንደሚፈልጉ ጠቅሰው ነበር።

የዲስፖራው ፖለቲካ

ብዙውን ጊዜ ከኢህአዴግ ቤትና ደጋፊዎቹ በሆኑ “አክቲቪስቶች” እንደሚወራው የሀገራችን አብዛኛዎቹ የፖለቲካ ትኩሳት አባባሹና ለተከሰቱ ተራ ችግሮች የተለየ ትርጓሜ የሚሰጠውና የሚያቀጣጥለው ዲያስፖራው ነው። በእነዚህ ሰዎች “እምነት” ዲያስፖራው ዶላርና ዩሮ እየተቀበለ ሀገሪቱን በማተራመስ የውጪ ሃይሎች ማስፈጸሚያ ሆንዋል።

የዲያስፖራ ፖለቲካ በሀገራችን መታየት የጀመረው ሀገራችን የአውሮፓ ትምህርትን አካሄድ መከተል ከጀመረችበት 20ኛው መቶ ክፍለ ዘመን ጀምሮ እንደሆነ የታሪክ ድርሳናት ይናገራሉ። ቀ/ኃይለ ስላሴ ከሸዋ መሳፍንት ይደርስባቸው የነበረውን ተግዳሮት ለመቋቋም ዲያስፖራውንና ከውጪ የተመለሰውን አውሮፓ ቀመስ ምዑር ወጣት (በዘመኑ ትንሽ ቁጥር ቢኖረውም) እንደተጠቀሙና ውጤታማም እንደነበሩ ታሪክ ያወሳናል። ይህ በዲያስፖራውና በንጉሱ መካከል የተጀመረው ጥሩ ግንኙነት ሀገሪቱን ወደተሻለ ምዕራፍ ሊያስኬዳት ቢችልም ብዙም አልዘለቀም ነበር። በ1956 ዓ.ም የተካሄደውም መፈንቅለ መንግስት ጨምሮ ሌሎችም ስር ነቀል እንቅስቃሴዎች በዲያስፖራውና ከዲያስፖራ ተመላሽ ወጣቶች የተቀነባበሩ ነበር።

ከንጉሳዊው ስርዓት ግብአተ መሬት በኃላም ቢሆን ደርግ ለዲያስፖራው (በተለይ በምዕራቡ አለም ላሉት) ቀና የሆነ አመለካከት አልነበረውም። ሁሉም በአድዓሪና አናርኪስት አይን ያያቸው ነበር። በዘመነ ደርግና ኢሰፓ የበዙ ወጣቶች በፖለቲካ አመለካከታቸው ምክንያት ከሀገር በስደት ወጥተዋል።

የትግራይ ህዝብን ብሶት በመያዝ ደርግን ለመናድ በረሃ የወረደው ህወሃት ምንም እንኳን በረሃ በነበረበት የመጀመሪያዎቹ አመታት ከዲያስፖራው ጋር ጥሩ ግንኙነት ነበረው ማለት ቢቻልም ኢህአዴግ/ህወሃት 4 ኪሎ ከገባባት ሰአት ጀምሮ ግን ይህ ግንኙነት ጥሩ ባልሆነ መልኩ ተቀይሯል።

ባለፉት 100 አመታት ሀገሪቱን ያስተዳደሩት መንግስታት በመጀመሪያ የስልጣን ዘመናቸው ከዲያስፖራው ጋር ጥሩ ሊባል የሚችል ግንኙነት ቢኖራቸውም ዘላቂ ግን አይደለም። ሁሉም ማለት በሚያስችል መልኩ ዲያስፖራውን በአንድ አይነት መልካም ያልሆነ አመለካከት ነበር የሚመለከቱት። ይህ መሆኑ ደግሞ ሀገሪቱን እጅጉ ጎድቷታል።

ነገር ግን በ21ኛው መቶ ክፍለ ዘመን ያለው የአለም ነባራዊ ሁኔታ ዲያስፖራውን የትም ሆኖ እንደልቡ በሀገሩ አጠቃላይ ጉዳይ ያለምንም ፍራቻ እንዲሳተፍ አስችሎታል። ይህ ዲያስፖራው ያለው ጥሩ አጋጣሚ (የቴክኖሎጂ፣ እውቀትና የነጻነት) አሁንም በሀገሪቱ ሁኔታ ከማንም በላይ ተሳታፊ እንዲሆንና በሀገር ውስጥ ያለውን ህዝባዊ ብሶት እንዲቀጣጠል አስችሎታል። ስለዚህ በሀገሩ ጉዳይ የሚሳተፈውን ዲያስፖራው እንደ ሀገር ጠላትና ከሃዲ በማየት የሀገሪቱን ሰላም ማምጣት ከባድ ነው።

ተስፋ ያሣጡ የሀገር ውስጥ ተቃዋሚዎች

በዲሞክራሲያዊ ስርኣት ስልጣን ሊገኝ የሚችለው በሰላማዊ መልኩ በሚደረግ ፉክክርና ምርጫ ብቻ ነው። እንዳለመታደል ሆኖ ለዚህ ኢትዮጵያውያን የታደልን አይደለንም (በቅርቡ የተደረገው የስልጣን ሽግግር በአንድ ፓርቲ ውስጥ እንጂ የስርአት ለውጥ አይደለም)። በዲሞክራሲያዊ መልኩ ለመወዳደርና ስልጣን ለመያዝ የበዙ ጉዳዮች መሟላት አለባቸው። ከእነዚህ ጉዳዮች ዋናው ግን ህዝብ በተቃዋሚዎችና በስልጣን ላይ ባለው ፓርቲ ላይ ያለው አመኔታና ድጋፍ ነው።

ኢትዮጵያ በአለም ደካማ የፖለቲካ ፓርቲ ስርአት ካላቸው ሀገራት ግንባር ቀደሟ ነች። መረጃዎች እንደሚጠቁሙት አንዳንድ በሰላማዊ መልኩ በሀገራችን የሚንቀሳቀሱት ተቃዋሚ ፓርቲዎች ከመስራቾቹ ቤተሰብ በቀር ምንም ድጋፍ የሌላቸው፣ አንዳንዶቹ እስከነ መኖራቸው እንኳን በህዝብ የማይታወቁ፣ በቅጡ አባልና አማራጭ ፖሊስም ሆነ እስትራቴጂ የሌላቸው፣ አብዛኛዎቹን ደግሞ የኢህአዴግ ሰዎች እራሳቸው በእጅ አዙር የሚያሽከረክሯቸው መሆናቸው የአደባባይ ሚስጥር ነው። ይህ ሁኔታ ህዝቡ በተቃዋሚዎቹ ተስፋ ቆርጦ በዲያስፖራውና ውጪ ባሉት ተቃዋሚዎች ተስፋ እንዲያደርግ ያስገደደው ይመስላል።

ለዘላቂ ሰላም ሁሉን አሳታፊ ውይይት

ባለፉት ጥቂት አመታት ወዲህ በሀገራችን በተለያዩ አካባቢዎች የታዩት ክስተቶች እንደጠቆሙት በስልጣን ላይ ያለው አካል እንደ ከዚህ ቀደሙ በማስፈራራት ወይም ስም በመስጠት የፖለቲካ እድሜን ማራዘም የሚቻለው አይደለም። ዶ/ር አብይ እንዳሉትና በአንዳንድ ሀቀኛ ተቃዋሚ ፓርቲዎች ሲባል እንደነበረው ሁሉን የፖለቲካ ሃይሎች ያካተተ ውይይት በተለያዩ ሀገራዊ ጉዳዮች በፍጥነት ሊካሄድ ይገባል።

ዶ/ር አብይ ሊያደርጉት የሚገባው እንደ ከዚህ ቀደሞቹ የኢህአዴግና የተቃዋሚዎች የይስሙላ ውይይቶች ሳይሆኑ ትክክለኛ ያልሆነ ታርጋ የተለጠፈባቸውን ጨምሮ በውስጥም በውጭም ከተደራጁ ሃይሎችና ስለዚህች ሀገር ጉዳይ ይመለከተናል ከሚሉ አካላት ጋር መሆን ይኖርበታል።

ዳንኤል መኮንን ይልማ
በወልቂጤ ዩኒቨርስቲ የፖለቲካል ሳይንስ መምህር
ኢሜል፦ yalewyalew3@gmail.com


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ። ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው።

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions, Politics Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የእምዬ ምኒልክ አዳራሽ October 30, 2023 10:27 am
  • የኢትዮጵያ መከላከያ መሥራች አጼ ምኒልክ መሆናቸውን ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ተናገሩ October 26, 2023 01:30 pm
  • ጥቅምት 15 ለምን? October 26, 2023 01:29 am
  • “በተፈተነ ጊዜ ሁሉ የሚፀና የድል ሠራዊት” October 26, 2023 12:57 am
  • “ውትድርና ሕይወቴ ነው” October 26, 2023 12:13 am
  • መከላከያ በሁሉም መስክ ኢትዮጵያን የሚመጥን ኃይል እየገነባ ነው October 20, 2023 05:07 pm
  • “ሁሉም ኢትዮጵያዊ ትምህርት ቤት እኩል ነው በችሎታው ነው እንጂ የሚመዘነው” ፕ/ር ብርሃኑ October 20, 2023 04:47 pm
  • 42 የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት አመራሮች እና ሠራተኞች ታሰሩ October 18, 2023 04:29 pm
  • በተማሪዎች ፈተና ውጤት ለታየው ውድቀት ትምህርት ሚ/ር ኃላፊ መሆን አለበት ተባለ October 18, 2023 04:00 pm
  • ቀይ ባሕር እና ዓባይ “የኅልውና ጉዳይ ናቸው”፤ “መተንፈሻ ወደብ ያስፈልገናል” October 13, 2023 10:04 pm
  • ከ3,106 ትምህርት ቤቶች 1,328ቱ (44%) አንድም ተማሪ አላሳለፉም October 10, 2023 01:51 pm
  • “አቋጥሬ” በአማራ ክልል እያጫረሰ ነው፤ ” ኑሮውን መቋቋም አልቻልንም ” ነዋሪዎች October 10, 2023 09:07 am
  • እሸቴ አሸባሪ፤ ቲዲኤፍ/ትሕነግ “ሰማዕት” – የዘመናችን ጉድ! October 7, 2023 06:47 am
  • በወልቃይት 1.1ሚሊዮን ኩንታል ሰሊጥ ለመሰብሰብ ከ1 ሚሊዮን በላይ ሠራተኛ ይፈለጋል September 27, 2023 10:42 am
  • በአማራ ክልል ሰላም ዕጦት ከ90.5 ቢሊዮን ብር በላይ ፕሮጀክቶች ቆመዋል September 27, 2023 08:41 am
  • ወርቁ አይተነው የሸሹት ከዝርፊያ፣ ውንብድናና ዕዳ ጋር በተያያዘ ነው September 21, 2023 02:38 pm
  • ወደ አማራ ክልል ሊተላለፍ የነበረ መሣሪያና ሰነድ ተያዘ September 19, 2023 04:35 pm
  • በትግራይ መርዶ በይፋ ሊታወጅ ነው September 19, 2023 04:22 pm
  • ጃርቶች ለምን ይጮኻሉ? September 19, 2023 04:37 am
  • “ዐቢይ ግድቡን ሸጦታል” ጌታቸው ረዳ September 11, 2023 10:18 am
  • አቶ አገኘሁ መረጃ አሳልፎ በመስጠት ዋጋ እንደሚከፍሉ ተሰማ September 10, 2023 06:52 pm
  • ለዋዜማ ሬዲዮ “ኢትዮጵያን ቋሚ የውሀ ባለ እዳ” ያደርጋል ያላችሁት ረቂቅ ሰነድ የታለ? September 10, 2023 01:58 am
  • ወደር የሌለው የኅብረተሰባዊት ኢትዮጵያ ጀግና! ብርጋዴር ጄኔራል ተስፋዬ ኃብተማርያም September 8, 2023 02:31 pm
  • የትግራይ መፍረስ በርዕሰ መስተዳደሩ አንደበት September 8, 2023 02:49 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule