ኢትዮጵያዊነት በተቃርኖ የተሞላ የግሳንግስ ስብስብ አይደለም። ኢትዮጵያዊነት የወጪት ሰባሪዎች ትግል፣ ለኔ በገሌ ነው ባዮች ምክር አይደለም። ኢትዮጵያዊነት በበግ ጸጉር ቡክርናውን እንደቀውማው ያዕቆብም ( "አታላይ ማለት ነው") አይነትም አይደለም። በጎሳ አሽክላ ተተብትበን፣ በቂም ቆመን፣ ጭረት አመርቅዘን ቁስል አርገን ፣ የዛሬ ውድቀታችንን ፣ የዘምን ምክነት አስመስለን፣ ላለመቻላችን መወጣጫ፣ ላለመቆማችን የ ምክንያት መቆናጠጫ ብንፈልግ ፣ ካለፈ ጥፋትም ሆነ ሕዝብ ካለፈለት እውነት ጀርባ መዶለታችንን እስካልተውን ፣ የድርሻችንን ለመወጣት ታጥቀን እስካልተነሳን ድረስ ፣ ትግላችን እንደ እስከ ዛሬው "ለ አፈ ግም አፍንጫ ድፍን ያዝለታል" ሆኖ ስለመቀጠሉ አዋቂ መሆን አይጠይቅም። የፕለቲካ ድርጅቶች መግለጫና ትርጉም የ-ወያኔው ስርዓት እንደ ወየነ 40 ዓመት ሞላው። እኛም የዚህ … [Read more...] about ኢትዮጵያዊነት – ክፍል አንድና ሁለት
Archives for May 2014
የወያኔ ጥላቻ ፍሬ
ወያኔ ለትግራይ ሕዝብ ሀብትንና ብልጽግናን አመጣ ብለው የሚያምኑ ሰዎች ብዙ ናቸው፤ ወያኔ የሥልጣን ወንበሩ ላይ በመውጣቱ ትግሬዎች ሁሉ አልፎላቸዋል ተብሎ ይታመናል፤ በተለይ በአውሮፓና በአሜሪካ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን በዚህ ላይ የጠነከረ እምነት አላቸው፤ በዚህ ጉዳይ ላይ ከኢትዮጵያ ውጭ ብዙ ውይይትም ይሁን ንትርክ ይደረጋል፤ በኢትዮጵያ ውስጥ ግን የተፈራ ርእስ ነው፤ ውስጥ-ውስጡን እንጂ አደባባይ አይወጣም፤ ይህንን ጉዳይ በኢትዮጵያ ውስጥ አደባባይ ለማውጣት ጊዜው የደረሰ ይመስለኛል፤ አረጋዊ በርሄ፣ ገብረ መድኅን አርአያ፣ አስገደ ገብረ ሥላሴ፣ አብርሃ ደስታ (አሥር ቢሞሉልኝ ደስ ይለኝ ነበር!) እየደጋገሙ ቢያነሡትም ሌሎች በቁም-ነገር የተቀበሉት አይመስልም፤ ሕዝቡ ግን በራሱ መንገድ እየተናገረና ምስክርነቱን እየሰጠ ነው፤ በመቀሌ የተሠራውን የመኳንንት መንደር ሕዝቡ አፓርቴይድ ብሎ … [Read more...] about የወያኔ ጥላቻ ፍሬ
“የኔ” የምለውን፤
ባለፈው "ምን ይባላል?" በሚል ርዕስ ላቀረብነው የብሌን ከበደ ግጥም በመሳተፍ ጨዋታውን በግጥም ላደመቃችሁት Yaredo Enkubi እና በለው ምስጋናችን የላቀ ነው:: ሌሎችም በፌስቡክ ገጻችን በኩል አስተያየት የሰጣችሁንን ከልብ እናመሰግናለን:: ለዛሬ ደግሞ የዘወትር ተሳታፊያችን የካናዳው ከበደ ይህንን ግጥም ለከውንናል - "የኔ" የምለው በማለት ለላኩልን ግጥም እናንተስ ምን ትላላችሁ? "የኔ" የምትሉትን በማለት ጨዋታውን እናድምቀው - ሃሳባችንን እንንወጣው - የልባችንን እንግለጽ:: “የኔ” የምለውን፤ ታሪኬን ኩራቴን መብቴን ነፃነቴን ...ኢትዮጵያዊነቴን ከውስጤ አውጥታችሁ መሬቴን ወስዳችሁ፤ ቤቴን አፍርሳችሁ መንገድ ብትሠሩ ፎቅ ብትደረድሩ ቢትረፈረፍ እንኳን መብራቱ ባቡሩ እኔ “የኔ” ብየ እስካልተቀበልኩት፤ እስካልያዝኩት ድረስ ምንም አይመስለኝም ቢነድ፤ … [Read more...] about “የኔ” የምለውን፤
በሪያድ የሃገር ሽማግሌዎች እና የሃይማኖት አባቶች “አሸባሪ” መባላቸው ተቃውሞ አስነሳ
በቅርቡ በሪያ የኢትዮጵያ ኮሚኒቲ አዳራሽ የተከበረውን የአባይ የኤሌክትሪክ ሃይል ማመንጫ ግደብ 3ኛ አመት ክብረ በዓል አሰመልክቶ ኤምባሲው በጠራው ስብሰባ ላይ ሪያድ ከተማ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን የሃይማኖት አባቶች እና የሃገር ሽማግሌዎች እንዳይገኙ በሳውዲ አረቢያ የኢትዮጵያው አምባሳደር መሃመድ ሃሰን ባስተላለፉት ቀጭን ትዕዛዝ አዛውንቱ በአሸባሪነት ተፈርጀው በአሉን እንዳይታደሙ መታገዳቸው ሪያድ በሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ዘንድ ከፈተኛ ቁጣን ቀስቅሷል። በተለይ ሰሞኑን ውስጥ ወስጡን ሲነገር የነበረው የአምባሳደሩ መሃመድ ሃሰን ነውረኝነት ተግባር አርብ ሜይ 9 2014 ምሸት በሪያድ የኢትዮጵያ ኮሚኒት አዳራሽ ውስጥ ለአንድ ኢትዮጵያዊ በተዘጋጀ የእርዳታ ገቢ ማሰባሰቢያ ፕሮግራም ላይ ህዝቡ ተቃውሞውን ማሰማቱን ለማወቅ ተችሏል። በወቅቱ አንድ የሃይማኖት አባት ሪያድ ከተማ ውስጥ መኖር … [Read more...] about በሪያድ የሃገር ሽማግሌዎች እና የሃይማኖት አባቶች “አሸባሪ” መባላቸው ተቃውሞ አስነሳ
Wholesome Ethiopiawinet: Unity & Beyond
Unity is just the beginning. The way it is going, the ethnic centered thought and the status quo ethiopiawinet thought will never reconcile to give us the true one Ethiopia unseen before. Here is an independent voice urging all to look for a third way: Wholesome Ethiopiawinet. The Other 10 Theses… Thesis I. The Mask is not Our Identity All governments of Ethiopia disguised our true identity by constructing an identity of their own creation for us, which in actuality is a mere mask on the … [Read more...] about Wholesome Ethiopiawinet: Unity & Beyond
A Mothers’ Day Tribute to Ethiopian Women
We want to take a moment to express our outrage about the abduction of hundreds of Nigerian school girls. In solidarity with Nigerian mothers on this Mother’s Day, we say, BRING BACK OUR GIRLS! We also wish all women around the world to have a peaceful Mother’s Day. To all Ethiopian women at home and in the Diaspora, we pay tribute to your courage, struggle for freedom, equality and justice. For generations, Ethiopian women have played major roles in their society. They are the center of the … [Read more...] about A Mothers’ Day Tribute to Ethiopian Women
Ethnic Politics is No Other Than Institutionalizing Racism
This article is intended to reach out to innocent citizens who might have been confused with political propaganda and underestimate the negative consequences of ethnic politics. It is to remind fellow citizens, as a concerned and responsible citizen that we need to take measured steps in our effort to support political parties. Simply stated people’s major interest is to have peace and equal opportunities in their own country. The interest of political elites is different, more than anything; it … [Read more...] about Ethnic Politics is No Other Than Institutionalizing Racism
በሬየን አልሸጥም – አጭር ወግ
አዲሱን (የነበረውን ግን ሰሞኑን የሾረውን) የ"ኦሮሞ ወጣቶች" ግድያ። በነገራችን ላይ ለምንድን ነው "የኢትዮጵያ ወጣቶች " የማንለው? ማለት ስለማንፈልግ? ወይስ ብንል ባንል ምን ይጠቅማል (ምንስ ይጎዳል በሚል ሃሳብ?) ሁለቱንም ያዙልንና እንቀጥል። ሰሞኑን አምቦ ላይ የተፈጸመውን ግድያ ተከትሎ ወዳጆች "ልጅ ሄኖክ በዚህ ጉዳይ ላይ አንድ ነገር በል እንጂ "ጠላቶች ደሞ" አንተ ምንትስ አማራ አሁን አማራ ቢሆን ኖሮ ይሄ ሁሉ መከራ የደረሰበት አምሳ ገጽ ጽፈህ፣ ነገሩን ለውጠሕና ለጥጠህ ባቀረብከው ነበር ''የሚሉ መልዕክቶችን አስቀምጠውልኛል። እኔም እንደ ለገዳዲ ሬዲዮ "ጦማሪዎች ሆይ ምልእክታችሁ ደርሶኛል ለሁሉም እንደነገሩ ለመመለስ እንሆ -- " በነገራችን ላይ አማራ ስለመሆኔ እኔ በበኩሌ እርግጠኛ አይደለሁም፣ ቢያንስ እርግጠኛ እስክሆን ብትታገሱኝ ምን ነበረበት ( ስለ-ኔ … [Read more...] about በሬየን አልሸጥም – አጭር ወግ
የባዕዳን ምሁራን የግዕዝና የፊደሎቹን ዕድሜ ለማሳጠር ምን ያህል ደከሙ?
እንደ የቋንቋና የታሪክ አጥኚዎች እምነት የግዕዝ ቋንቋ ፊደላት ከካዕብ እስከ ሳብዕ እና እንደአስፈላጊነቱ ከዚያም በላይ ሆሄያት የተቀረጹት ከአራተኛው መቶ ክፍለ ዘመን በኋላ ነው ብለው ለማሳመን ይጣጣራሉ፡፡ በማስረጃነትም በዐፄ ኢዛና ዘመነ መንግሥት ከ፫፻፳ወ፬-፫፻፴ወ፮ ዓ.ም. የነበረ ንጉሥ የመገበያያ የወርቅ ሳንቲም ላይ “ኢዛና ንጉሠ አክሱም” ተብሎ ለመጻፍ ተፈልጐ “አዘነ ነገሠ አከሰመ” ተብሎ የተጻፈበት ሳንቲም አግኝተናል ይላሉ፡፡ ይህ ሁሉ ነገርግን ካሉት ነባራዊ ታሪካዊና ሃይማኖታዊ መረጃዎች አንፃር ሲታይ ሊታመን የማይችል ከመሆኑም በላይ በተለያዩ ተጨባጭ ምክንያቶች በእነዚህ አጥኚዎች ዘንድም የሆነ አንዳች ደባ እንዳለም የሚጠቁም ሆኖ ይገኛል፡፡ ፩. እንደሚታወቀው የግዕዝ ሆሄያት አደራደር ከአሌፋቱ ወይም ከአበገደው ሥርዓት ወደ ሀ ለ ሐ መው ለአጠናን እንዲያመች በሚል … [Read more...] about የባዕዳን ምሁራን የግዕዝና የፊደሎቹን ዕድሜ ለማሳጠር ምን ያህል ደከሙ?
ብአዴን ማን ነው?
የአንድን ድርጅት ማንነቱን ከማቅረብ በፊት ቀደም ብሎ የተፈጸመውን ስህተት፣ ቀጥሎም ኢህአፓን ለማጥፋት በህወሓት እና በሻእቢያ የደረሰበትን ጥቃት አጠር ባለ መልኩ ማቅረብ አስፈላጊ ይሆናል። የስትራተጂ ስህተት ለከባድ ወድቀት ይዳርጋል ኢህአፓ ትግሉን የጀመረው ገና በ1960 መጀመሪያ ነበር። አብዮቱ እየተቀጣጠለ ሃገር አቀፍ ሆነ። ዘውዳዊ ስርዓት ወድቆ በማርክሲዝም ሌኒኒዝም ርእዮተ ዓለም የሚመራ ሶሻሊዝም የኢትዮጵያ ስርአት እንዲሆን ነበር። ይህ ግራ አክራሪ ስታሊኒዝም በቀ. ኃ. ሥ. ዩኒቨርሲቲ ይማሩ በነበሩ የተሰባሰበ ቡድን፣ የወቅቱ አብዮተኞች ተገቢውን መልክ የያዘ አደረጃጀት ያልነበረው፣ አብዮተኛ የሚል ስም በማግኘታቸው ብቻ “ዲሞክራሲያ” ተብሎ የሚታወቀውን የኢህአፓ ልሳን በየሳምንቱ በመበተን አሁን ኢትዮጵያ የደረሰባትና እየደረሰባት ያለው ከባድ ችግር የከፈተው እነ ዋለልኝ … [Read more...] about ብአዴን ማን ነው?