• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“የኔ” የምለውን፤

May 12, 2014 06:18 am by Editor 4 Comments

ባለፈው “ምን ይባላል?” በሚል ርዕስ ላቀረብነው የብሌን ከበደ ግጥም በመሳተፍ ጨዋታውን በግጥም ላደመቃችሁት Yaredo Enkubi እና በለው ምስጋናችን የላቀ ነው:: ሌሎችም በፌስቡክ ገጻችን በኩል አስተያየት የሰጣችሁንን ከልብ እናመሰግናለን:: ለዛሬ ደግሞ የዘወትር ተሳታፊያችን የካናዳው ከበደ ይህንን ግጥም ለከውንናል – “የኔ” የምለው በማለት ለላኩልን ግጥም እናንተስ ምን ትላላችሁ? “የኔ” የምትሉትን በማለት ጨዋታውን እናድምቀው – ሃሳባችንን እንንወጣው – የልባችንን እንግለጽ::

“የኔ” የምለውን፤

ታሪኬን ኩራቴን
መብቴን ነፃነቴን
…ኢትዮጵያዊነቴን

ከውስጤ አውጥታችሁ
መሬቴን ወስዳችሁ፤ ቤቴን አፍርሳችሁ

መንገድ ብትሠሩ
ፎቅ ብትደረድሩ

ቢትረፈረፍ እንኳን

መብራቱ ባቡሩ

እኔ “የኔ” ብየ እስካልተቀበልኩት፤

እስካልያዝኩት ድረስ

ምንም አይመስለኝም

ቢነድ፤ ቢቃጠል፤ ቢናድና ቢፈርስ

ትዕግሥቱ ሲሟጠጥ

ሰው ሲቆርጥ ተስፋ

ተመልከት ሲሪያን፤

አገር በልጆቿ እንደምትጠፋ

(የካናዳው ከበደ)

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Literature Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Comments

  1. በለው ! says

    May 12, 2014 12:38 pm at 12:38 pm

    ***************
    ታሪከ! ነፃነት! ክብር! ዜግነትማ! ተገፎ ተዋርዶ
    ሕዝብ እየተናቀ ገንዘብና ጉልበት ህብሪትን ወልዶ
    ለመኖር ለመሄድ መናገር ለቀብር ለምኖ አስፈቅዶ
    ተገዛም ተሰጠ ፍቅረ-ንዋይማ ስብዕናን ወስዶ
    በቋንቋ በዘር በአሳላጭ ተጫጭቶ በጥቅም ተሞዳምዶ
    በሙስና ፍቅር በመሬት ተጣልቶ በሕንፃው ላይ ተዋዶ
    ከሰው የበለጠው የድንጋይ ክምር ዋሻ ነው ወይ ነዶ !
    ___—-___——___አዎን!
    ሲዘርፉ ሲግድሉ ሲበሉ ለእናንተ ነው ሲሉን
    የእናንተ የእኛ በእኛ ለእኛ ብቻ ይሆናል ያሉን
    በጥቅም ሲጣሉ ሲሻሙ ሲቃሙ እሪ በሉ የሚሉን
    የጠገበ እርስ በርሱ ይባላል የተራበ ይበላል መሪውን
    የማን ነው ብለን ነው ዘራፍ በሉ ያሉን!?
    ከቶ ለማን ብለን? አባሉን እንጂ መች አበሉን?አስበሉን?
    አውቀነዋል ለምን ባልበላ አንጀታችን ሙት እያሉ የሚምሉልን ።
    በለው! ከሀገረ ካናዳ

    Reply
  2. Mohammed Seid Ali says

    May 13, 2014 10:24 pm at 10:24 pm

    ደግ ተንፍሰሃል የካናዳው ከቤ፤
    ይህ የኔም ሃሳብ ነው የነፍሴ የልቤ፣
    ግንኮ ወዳጄ እኔ የኔ ምለው አለኝ ብዙ ሀብት፤
    አንበሽብሾኝ የለ ፀሃዩ መንግስት፤
    ቢፈርስንኳ ቤቴ መልሶ እንዲለማ፤
    ሰጥቶኛል ቅሊንጦን አሲዮ ቤሌማ፤
    አባይም ይገደብ ዛሬ እኔ ታርዤ፤
    ነገ እቀዳዋለሁ ጀሪካኔን ይዤ፤
    ስደትም የኔ ነው ስቃይ እንግልት፤
    አስፓልቱም ይደልደል ነገ ባደባባይ እንድሞትበት፤
    ኢቲቪም የኔ ነው ፋናየም የኔው ናት፤
    የተኸለቁልኝ ስሜን ለማጠልሸት፤
    አጋዚው ልዩ ሃይል ፌዴራል ፖሊሱ፤
    በየኮሌጆቼ ፈጥነው የሚደርሱ፤
    አሉኝኮ አስጠኚ ሂሳብ ኬሚስትሪ፤
    እያገላበጡ በጥቁር ጉማሬ፤
    ከፈለኩኝ ደግሞ ለነፍሴ ማደር፤
    በየመስጊዶቹ ገዳማት ደብር፤
    ቁርአን የሚያቀራ ወንጌልን የሚሰብክ፤
    ልማታዊ ካድሬ ፂሙን አንዠርግጎ ቆቡን አርጎ ልክክ፤
    አለኝ ቄስ ቃልቻ የሽፈራው ምሩቅ፤
    የሚያቃርብ ሳይሆን ከጌታ የሚያርቅ፤
    እና ወዳጄ ሆይ እኔ የኔምለው፤
    የወያኔ መንግስት ዘርቶ ያበቀለው፤
    አለኝ አለኝ አለኝ እልፍ ወአእላፍ፤
    አንዷን ካጎደልኩኝ ቶርች የሚያስገርፍ።

    Reply
  3. Bombu says

    May 19, 2014 10:24 pm at 10:24 pm

    የካናዳው ከቤ ያቀረብከው ግጥም
    ካርስቱ ጀምሮ በቁምነገር ፍርጥም
    ያለ ስለሆነ እኔም ወድጃልሁ
    ይልመድብህ ብዬ ወደኔ መጣልሁ

    እንደኔ ከሆነ እንደተራ ዜጋ
    ሰማይ መሬት ወርዶ ባግድም ቢዘረጋ
    ኣይደለም ሥርዓት የሕዝብ ድጋፍ ያጣ
    እምቢ ለዜግነት እረ ማንም ይምጣ

    የሥልጣኔማ መነሻው ከድሮ
    ሓገር መንግሥት ዜጋ ባንድነት ተሳስሮ
    ነበረ ዕውቀቱ ከውነት መዳረሻ
    ይባስ በኢትዮጵያ በስው ዘር መነሻ»

    Reply
  4. አሥራደው (ከፈረንሳይ) says

    May 24, 2014 12:19 am at 12:19 am

    “የኛ” ነው! “የኛ” ነው! – “የኛ”ነው የ’ኔ ቃል፤
    “የኔ” እምለው የለም – “የ’ኛ” ይበልጥብኛል::
    ያንቺ የሷ ይሁን – የነሱ ለነዚያ፤
    አብሮነት አንድነት – ይሁነን መመሪያ፤
    ያንተ የኔ ሆኖ – የኔ ያንተ ይሁን፤
    ኢትዮጵያ የኛ ናት – እኛም ያገራችን::
    ወዳጅ እንዲያከብረን – ጠላት እንዲፈራን፤
    በጋራ አብሮ መኖር – “እኛ” ነው እሚበጀን::
    የ’ኔ የ’ኔ ቀርቶ – የ’ኛ ስንባባል፤
    ፍቅራችን ያብባል – አገርም ይለማል::

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule