• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“የኔ” የምለውን፤

May 12, 2014 06:18 am by Editor 4 Comments

ባለፈው “ምን ይባላል?” በሚል ርዕስ ላቀረብነው የብሌን ከበደ ግጥም በመሳተፍ ጨዋታውን በግጥም ላደመቃችሁት Yaredo Enkubi እና በለው ምስጋናችን የላቀ ነው:: ሌሎችም በፌስቡክ ገጻችን በኩል አስተያየት የሰጣችሁንን ከልብ እናመሰግናለን:: ለዛሬ ደግሞ የዘወትር ተሳታፊያችን የካናዳው ከበደ ይህንን ግጥም ለከውንናል – “የኔ” የምለው በማለት ለላኩልን ግጥም እናንተስ ምን ትላላችሁ? “የኔ” የምትሉትን በማለት ጨዋታውን እናድምቀው – ሃሳባችንን እንንወጣው – የልባችንን እንግለጽ::

“የኔ” የምለውን፤

ታሪኬን ኩራቴን
መብቴን ነፃነቴን
…ኢትዮጵያዊነቴን

ከውስጤ አውጥታችሁ
መሬቴን ወስዳችሁ፤ ቤቴን አፍርሳችሁ

መንገድ ብትሠሩ
ፎቅ ብትደረድሩ

ቢትረፈረፍ እንኳን

መብራቱ ባቡሩ

እኔ “የኔ” ብየ እስካልተቀበልኩት፤

እስካልያዝኩት ድረስ

ምንም አይመስለኝም

ቢነድ፤ ቢቃጠል፤ ቢናድና ቢፈርስ

ትዕግሥቱ ሲሟጠጥ

ሰው ሲቆርጥ ተስፋ

ተመልከት ሲሪያን፤

አገር በልጆቿ እንደምትጠፋ

(የካናዳው ከበደ)

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Literature Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Comments

  1. በለው ! says

    May 12, 2014 12:38 pm at 12:38 pm

    ***************
    ታሪከ! ነፃነት! ክብር! ዜግነትማ! ተገፎ ተዋርዶ
    ሕዝብ እየተናቀ ገንዘብና ጉልበት ህብሪትን ወልዶ
    ለመኖር ለመሄድ መናገር ለቀብር ለምኖ አስፈቅዶ
    ተገዛም ተሰጠ ፍቅረ-ንዋይማ ስብዕናን ወስዶ
    በቋንቋ በዘር በአሳላጭ ተጫጭቶ በጥቅም ተሞዳምዶ
    በሙስና ፍቅር በመሬት ተጣልቶ በሕንፃው ላይ ተዋዶ
    ከሰው የበለጠው የድንጋይ ክምር ዋሻ ነው ወይ ነዶ !
    ___—-___——___አዎን!
    ሲዘርፉ ሲግድሉ ሲበሉ ለእናንተ ነው ሲሉን
    የእናንተ የእኛ በእኛ ለእኛ ብቻ ይሆናል ያሉን
    በጥቅም ሲጣሉ ሲሻሙ ሲቃሙ እሪ በሉ የሚሉን
    የጠገበ እርስ በርሱ ይባላል የተራበ ይበላል መሪውን
    የማን ነው ብለን ነው ዘራፍ በሉ ያሉን!?
    ከቶ ለማን ብለን? አባሉን እንጂ መች አበሉን?አስበሉን?
    አውቀነዋል ለምን ባልበላ አንጀታችን ሙት እያሉ የሚምሉልን ።
    በለው! ከሀገረ ካናዳ

    Reply
  2. Mohammed Seid Ali says

    May 13, 2014 10:24 pm at 10:24 pm

    ደግ ተንፍሰሃል የካናዳው ከቤ፤
    ይህ የኔም ሃሳብ ነው የነፍሴ የልቤ፣
    ግንኮ ወዳጄ እኔ የኔ ምለው አለኝ ብዙ ሀብት፤
    አንበሽብሾኝ የለ ፀሃዩ መንግስት፤
    ቢፈርስንኳ ቤቴ መልሶ እንዲለማ፤
    ሰጥቶኛል ቅሊንጦን አሲዮ ቤሌማ፤
    አባይም ይገደብ ዛሬ እኔ ታርዤ፤
    ነገ እቀዳዋለሁ ጀሪካኔን ይዤ፤
    ስደትም የኔ ነው ስቃይ እንግልት፤
    አስፓልቱም ይደልደል ነገ ባደባባይ እንድሞትበት፤
    ኢቲቪም የኔ ነው ፋናየም የኔው ናት፤
    የተኸለቁልኝ ስሜን ለማጠልሸት፤
    አጋዚው ልዩ ሃይል ፌዴራል ፖሊሱ፤
    በየኮሌጆቼ ፈጥነው የሚደርሱ፤
    አሉኝኮ አስጠኚ ሂሳብ ኬሚስትሪ፤
    እያገላበጡ በጥቁር ጉማሬ፤
    ከፈለኩኝ ደግሞ ለነፍሴ ማደር፤
    በየመስጊዶቹ ገዳማት ደብር፤
    ቁርአን የሚያቀራ ወንጌልን የሚሰብክ፤
    ልማታዊ ካድሬ ፂሙን አንዠርግጎ ቆቡን አርጎ ልክክ፤
    አለኝ ቄስ ቃልቻ የሽፈራው ምሩቅ፤
    የሚያቃርብ ሳይሆን ከጌታ የሚያርቅ፤
    እና ወዳጄ ሆይ እኔ የኔምለው፤
    የወያኔ መንግስት ዘርቶ ያበቀለው፤
    አለኝ አለኝ አለኝ እልፍ ወአእላፍ፤
    አንዷን ካጎደልኩኝ ቶርች የሚያስገርፍ።

    Reply
  3. Bombu says

    May 19, 2014 10:24 pm at 10:24 pm

    የካናዳው ከቤ ያቀረብከው ግጥም
    ካርስቱ ጀምሮ በቁምነገር ፍርጥም
    ያለ ስለሆነ እኔም ወድጃልሁ
    ይልመድብህ ብዬ ወደኔ መጣልሁ

    እንደኔ ከሆነ እንደተራ ዜጋ
    ሰማይ መሬት ወርዶ ባግድም ቢዘረጋ
    ኣይደለም ሥርዓት የሕዝብ ድጋፍ ያጣ
    እምቢ ለዜግነት እረ ማንም ይምጣ

    የሥልጣኔማ መነሻው ከድሮ
    ሓገር መንግሥት ዜጋ ባንድነት ተሳስሮ
    ነበረ ዕውቀቱ ከውነት መዳረሻ
    ይባስ በኢትዮጵያ በስው ዘር መነሻ»

    Reply
  4. አሥራደው (ከፈረንሳይ) says

    May 24, 2014 12:19 am at 12:19 am

    “የኛ” ነው! “የኛ” ነው! – “የኛ”ነው የ’ኔ ቃል፤
    “የኔ” እምለው የለም – “የ’ኛ” ይበልጥብኛል::
    ያንቺ የሷ ይሁን – የነሱ ለነዚያ፤
    አብሮነት አንድነት – ይሁነን መመሪያ፤
    ያንተ የኔ ሆኖ – የኔ ያንተ ይሁን፤
    ኢትዮጵያ የኛ ናት – እኛም ያገራችን::
    ወዳጅ እንዲያከብረን – ጠላት እንዲፈራን፤
    በጋራ አብሮ መኖር – “እኛ” ነው እሚበጀን::
    የ’ኔ የ’ኔ ቀርቶ – የ’ኛ ስንባባል፤
    ፍቅራችን ያብባል – አገርም ይለማል::

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • በጦርነቱ የተጎዱ አካባቢዎችን ለማቋቋም የሚውል የ15 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር ድጋፍ የዓለም ባንክ May 16, 2022 10:22 am
  • በአዲስ አበባ 1 ሺህ 98 የብሬን እና 2 ሺህ 162 የክላሽ ጥይት ተያዘ May 16, 2022 10:10 am
  • በአዲስ አበባ ከተማ በግለሰብ መኖሪያ ቤት ከ5 ሺህ በላይ የአሜሪካ ዶላርና የተለያዩ አገራት ገንዘቦች ተያዙ May 16, 2022 09:53 am
  • አገር አፍራሹ ትህነግ ለቀለብ፣ መድኃኒትና ሥራ ማስኬጃ 76 ቢሊዮን ብር ቀርጥፏል May 16, 2022 08:30 am
  • እየተባባሰ ከመጣው የማህበራዊ ሚዲያ አጭበርባሪዎች ዜጎች ራሳቸውን እንዲጠብቁ ተጠየቀ May 15, 2022 09:38 am
  • የትህነግና ሸኔ መሠልጠኛ የምትባለው ዩጋንዳ መከላከያ ሚ/ር ከኤታማዦር ሹሙ ጋር ተወያዩ May 13, 2022 09:55 am
  • በትግራይ የውጊያ ምልመላው ጉዳይ May 11, 2022 02:37 am
  • መከላከያ በተጨማሪ ድሮን፣ በሥልጠና፣ በዝግጅት ራሱን አብቅቷል May 11, 2022 01:35 am
  • ትህነግ ለሌላ ውጊያ እየተዘጋጀ ነው ተባለ May 10, 2022 01:04 pm
  • ኤርትራ 8 ሩስያ ሠራሽ ድሮኖችን ተረክባለች May 10, 2022 12:37 am
  • ሙስሊምና ክርስቲያን በአንድነት የሚያከብረው የአኾላሌ ባሕላዊ ጭፈራ May 9, 2022 01:46 pm
  • በወልዲያ ፋኖዎች ተመረቁ May 9, 2022 12:51 pm
  • “ሠራዊታችን ድልን በአስተማማኝ መልኩ ማምጣት በሚችል ቁመና ላይ” ጀኔራል ጌታቸው May 9, 2022 11:57 am
  • ዋጋው 64 ሚሊዮን ብር የሚሆን (16 ኪሎ) ሕገወጥ ወርቅ ተያዘ May 9, 2022 11:51 am
  • አብን ክርስቲያን ታደለን ለመጨረሻ ጊዜ አስጠነቀቀ፤ 10 አባላቱን አገደ May 9, 2022 08:58 am
  • ራሱ አቡክቶ፣ ራሱ አሟሽሾ፣ ራሱ ጋግሮ በሰዓት 460 እንጀራ የሚያወጣ ፈጠራ May 9, 2022 08:17 am
  • በህገ ወጥ መንገድ 19 ህጻናትን ሲያዘዋወሩ የነበሩ 6 ሴቶች ተያዙ May 8, 2022 12:39 am
  • በአርሲ ሙስሊሞች ለቤ/ክ ማሠሪያ 3 ሚሊዮን ብርና 20 የቀንድ ከብት ሰጡ May 6, 2022 09:35 am
  • በአዲስ አበባ የሚኖረው የትህነግ ደጋፊ ማንነት በማስረጃ May 4, 2022 11:04 pm
  • ሙስሊም ወንድማማች የቤ/ክ ዘራፊዎችን በቁጥጥር ሥር አዋሉ May 4, 2022 09:04 am
  • ከ6 ሺህ የዓሳ ጫጩት ወደ 80 ሺህ May 4, 2022 08:57 am
  • ተስፋቢሱ ቴድሮስ May 3, 2022 12:16 pm
  • ከሽፏል! April 6, 2022 11:58 am
  • “ሩሲያ ዩክሬይንን ወረረች” እየተባለ ስለሚነዛው ወሬ ጥቂት እውነታዎች March 8, 2022 11:30 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2022 · Goolgule