• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“የኔ” የምለውን፤

May 12, 2014 06:18 am by Editor 4 Comments

ባለፈው “ምን ይባላል?” በሚል ርዕስ ላቀረብነው የብሌን ከበደ ግጥም በመሳተፍ ጨዋታውን በግጥም ላደመቃችሁት Yaredo Enkubi እና በለው ምስጋናችን የላቀ ነው:: ሌሎችም በፌስቡክ ገጻችን በኩል አስተያየት የሰጣችሁንን ከልብ እናመሰግናለን:: ለዛሬ ደግሞ የዘወትር ተሳታፊያችን የካናዳው ከበደ ይህንን ግጥም ለከውንናል – “የኔ” የምለው በማለት ለላኩልን ግጥም እናንተስ ምን ትላላችሁ? “የኔ” የምትሉትን በማለት ጨዋታውን እናድምቀው – ሃሳባችንን እንንወጣው – የልባችንን እንግለጽ::

“የኔ” የምለውን፤

ታሪኬን ኩራቴን
መብቴን ነፃነቴን
…ኢትዮጵያዊነቴን

ከውስጤ አውጥታችሁ
መሬቴን ወስዳችሁ፤ ቤቴን አፍርሳችሁ

መንገድ ብትሠሩ
ፎቅ ብትደረድሩ

ቢትረፈረፍ እንኳን

መብራቱ ባቡሩ

እኔ “የኔ” ብየ እስካልተቀበልኩት፤

እስካልያዝኩት ድረስ

ምንም አይመስለኝም

ቢነድ፤ ቢቃጠል፤ ቢናድና ቢፈርስ

ትዕግሥቱ ሲሟጠጥ

ሰው ሲቆርጥ ተስፋ

ተመልከት ሲሪያን፤

አገር በልጆቿ እንደምትጠፋ

(የካናዳው ከበደ)

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Literature Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Comments

  1. በለው ! says

    May 12, 2014 12:38 pm at 12:38 pm

    ***************
    ታሪከ! ነፃነት! ክብር! ዜግነትማ! ተገፎ ተዋርዶ
    ሕዝብ እየተናቀ ገንዘብና ጉልበት ህብሪትን ወልዶ
    ለመኖር ለመሄድ መናገር ለቀብር ለምኖ አስፈቅዶ
    ተገዛም ተሰጠ ፍቅረ-ንዋይማ ስብዕናን ወስዶ
    በቋንቋ በዘር በአሳላጭ ተጫጭቶ በጥቅም ተሞዳምዶ
    በሙስና ፍቅር በመሬት ተጣልቶ በሕንፃው ላይ ተዋዶ
    ከሰው የበለጠው የድንጋይ ክምር ዋሻ ነው ወይ ነዶ !
    ___—-___——___አዎን!
    ሲዘርፉ ሲግድሉ ሲበሉ ለእናንተ ነው ሲሉን
    የእናንተ የእኛ በእኛ ለእኛ ብቻ ይሆናል ያሉን
    በጥቅም ሲጣሉ ሲሻሙ ሲቃሙ እሪ በሉ የሚሉን
    የጠገበ እርስ በርሱ ይባላል የተራበ ይበላል መሪውን
    የማን ነው ብለን ነው ዘራፍ በሉ ያሉን!?
    ከቶ ለማን ብለን? አባሉን እንጂ መች አበሉን?አስበሉን?
    አውቀነዋል ለምን ባልበላ አንጀታችን ሙት እያሉ የሚምሉልን ።
    በለው! ከሀገረ ካናዳ

    Reply
  2. Mohammed Seid Ali says

    May 13, 2014 10:24 pm at 10:24 pm

    ደግ ተንፍሰሃል የካናዳው ከቤ፤
    ይህ የኔም ሃሳብ ነው የነፍሴ የልቤ፣
    ግንኮ ወዳጄ እኔ የኔ ምለው አለኝ ብዙ ሀብት፤
    አንበሽብሾኝ የለ ፀሃዩ መንግስት፤
    ቢፈርስንኳ ቤቴ መልሶ እንዲለማ፤
    ሰጥቶኛል ቅሊንጦን አሲዮ ቤሌማ፤
    አባይም ይገደብ ዛሬ እኔ ታርዤ፤
    ነገ እቀዳዋለሁ ጀሪካኔን ይዤ፤
    ስደትም የኔ ነው ስቃይ እንግልት፤
    አስፓልቱም ይደልደል ነገ ባደባባይ እንድሞትበት፤
    ኢቲቪም የኔ ነው ፋናየም የኔው ናት፤
    የተኸለቁልኝ ስሜን ለማጠልሸት፤
    አጋዚው ልዩ ሃይል ፌዴራል ፖሊሱ፤
    በየኮሌጆቼ ፈጥነው የሚደርሱ፤
    አሉኝኮ አስጠኚ ሂሳብ ኬሚስትሪ፤
    እያገላበጡ በጥቁር ጉማሬ፤
    ከፈለኩኝ ደግሞ ለነፍሴ ማደር፤
    በየመስጊዶቹ ገዳማት ደብር፤
    ቁርአን የሚያቀራ ወንጌልን የሚሰብክ፤
    ልማታዊ ካድሬ ፂሙን አንዠርግጎ ቆቡን አርጎ ልክክ፤
    አለኝ ቄስ ቃልቻ የሽፈራው ምሩቅ፤
    የሚያቃርብ ሳይሆን ከጌታ የሚያርቅ፤
    እና ወዳጄ ሆይ እኔ የኔምለው፤
    የወያኔ መንግስት ዘርቶ ያበቀለው፤
    አለኝ አለኝ አለኝ እልፍ ወአእላፍ፤
    አንዷን ካጎደልኩኝ ቶርች የሚያስገርፍ።

    Reply
  3. Bombu says

    May 19, 2014 10:24 pm at 10:24 pm

    የካናዳው ከቤ ያቀረብከው ግጥም
    ካርስቱ ጀምሮ በቁምነገር ፍርጥም
    ያለ ስለሆነ እኔም ወድጃልሁ
    ይልመድብህ ብዬ ወደኔ መጣልሁ

    እንደኔ ከሆነ እንደተራ ዜጋ
    ሰማይ መሬት ወርዶ ባግድም ቢዘረጋ
    ኣይደለም ሥርዓት የሕዝብ ድጋፍ ያጣ
    እምቢ ለዜግነት እረ ማንም ይምጣ

    የሥልጣኔማ መነሻው ከድሮ
    ሓገር መንግሥት ዜጋ ባንድነት ተሳስሮ
    ነበረ ዕውቀቱ ከውነት መዳረሻ
    ይባስ በኢትዮጵያ በስው ዘር መነሻ»

    Reply
  4. አሥራደው (ከፈረንሳይ) says

    May 24, 2014 12:19 am at 12:19 am

    “የኛ” ነው! “የኛ” ነው! – “የኛ”ነው የ’ኔ ቃል፤
    “የኔ” እምለው የለም – “የ’ኛ” ይበልጥብኛል::
    ያንቺ የሷ ይሁን – የነሱ ለነዚያ፤
    አብሮነት አንድነት – ይሁነን መመሪያ፤
    ያንተ የኔ ሆኖ – የኔ ያንተ ይሁን፤
    ኢትዮጵያ የኛ ናት – እኛም ያገራችን::
    ወዳጅ እንዲያከብረን – ጠላት እንዲፈራን፤
    በጋራ አብሮ መኖር – “እኛ” ነው እሚበጀን::
    የ’ኔ የ’ኔ ቀርቶ – የ’ኛ ስንባባል፤
    ፍቅራችን ያብባል – አገርም ይለማል::

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ከፍተኛ የፋኖ አመራሮች መገደላቸው ተነገረ May 6, 2025 10:40 pm
  • ሃይማኖትን ለተራ የፖለቲካ ሸቀጥ ማዋል ውርደት ነው April 24, 2025 12:43 am
  •  የኬሪያ ኢብራሒም ኑዛዜ “ብትንትናችን ወጥቷል” April 22, 2025 12:08 am
  • ለወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን አመራሮች ወታደራዊ ሥልጠና ተሰጠ April 16, 2025 11:44 pm
  • ዓቅም እንደሌለው የገመገመው ሻዕቢያ ፊቱን ከጦርነት ወደ ዲፕሎማሲ እያዞረ ነው   April 15, 2025 12:32 am
  • “አንድ የፋኖ ተቋም (የእስክንድር) ተመሥርቷል፤ ሌሎቹ ደግሞ እንዲሁ አንድ ተቋም መሥርተው ወደዚህ ይመጡ” አበበ ጢሞ April 11, 2025 12:07 am
  • መለስ (ለገሰ) ዜናዊ – ተዋርዶ ያዋረደን! April 9, 2025 10:28 pm
  • የተከዜ ዘብ: የሉዓላዊነት መጠበቂያ April 8, 2025 11:49 pm
  • አዲስ አበባ አስተዳደር የሪፖርተርን የተዛባ መረጃ ኮነነ፤ ሕጋዊ እርምጃ እወስዳለሁ አለ April 8, 2025 10:06 pm
  • ሀሰተኛውን የሪፖርተር ዘገባ ንግድ ባንክ በጽኑ ተቃወመ፤ እርማትም ጠየቀ April 8, 2025 09:48 pm
  • “ኦሮሚያ ላይ ወይም ሌላ ቦታ ላይ ስታደርገው ከነበረ ትግራይ ወስጥም የማታደርግበት ምንም ምክንያት አይኖርህም” ነው ጌታቸው ረዳ April 7, 2025 10:22 pm
  • “TPLF’s belief in a strong federal government was always tied to its own dominance in Addis Ababa” April 7, 2025 10:15 pm
  • Counter-Video by EBC Challenges EBS Broadcast, Sparks Public Outcry Over Alleged Misinformation March 31, 2025 02:36 am
  • የኤሊያስ መሠረትን ፌክ መረጃ ማን ያጋልጥ? February 19, 2025 06:00 pm
  • አዘርባጃን፡ የሻዕቢያን ሸምቀቆ ማጥበቂያ?! February 19, 2025 12:29 am
  • የአሜሪካ ድምፅ/ቪኦኤ ይዘጋ ተባለ  February 12, 2025 03:37 am
  • የብልፅግና ፓርቲ ሹመኛ ካድሬዎች February 3, 2025 11:07 am
  • ትግሉን የጎዳው የእስክንድር ነጋ አካሄድ February 3, 2025 10:29 am
  • ኤሊያስ መሠረት “ጭምብሉ ዛሬ ወለቀ”፤ ተከፋይ ነው! February 2, 2025 05:32 pm
  • የፋሲል ግንብ እድሳት እንዴት ተካሄደ? የመንጣቱ ምክንያት? January 23, 2025 03:41 pm
  • ታሪካዊዉ የፋሲል ቤተመንግሥት ለምን ነጣ? January 23, 2025 03:04 pm
  • የኢትዮጵያ አየር መንገድ በተወልደ አስተዳደር ዘመን ለተሠራ ስህተት 425ሺ ዶላር ተቀጣ December 14, 2024 01:44 am
  • በትግራይ ከሞትና ከአካላዊ ጉዳት የተረፉት ለስደት ተዳርገዋል November 27, 2024 12:09 pm
  • የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት አሠራሩን እንዲያርም ጥብቅ መመሪያ ተሰጠው November 27, 2024 11:31 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule