• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ኢትዮጵያዊነት – ክፍል አንድና ሁለት

May 13, 2014 12:12 am by Editor Leave a Comment

ኢትዮጵያዊነት በተቃርኖ የተሞላ የግሳንግስ ስብስብ አይደለም። ኢትዮጵያዊነት የወጪት ሰባሪዎች ትግል፣ ለኔ በገሌ ነው ባዮች ምክር አይደለም። ኢትዮጵያዊነት በበግ ጸጉር ቡክርናውን እንደቀውማው ያዕቆብም ( “አታላይ ማለት ነው”) አይነትም አይደለም። በጎሳ አሽክላ ተተብትበን፣ በቂም ቆመን፣ ጭረት አመርቅዘን ቁስል አርገን ፣ የዛሬ ውድቀታችንን ፣ የዘምን ምክነት አስመስለን፣ ላለመቻላችን መወጣጫ፣ ላለመቆማችን የ ምክንያት መቆናጠጫ ብንፈልግ ፣ ካለፈ ጥፋትም ሆነ ሕዝብ ካለፈለት እውነት ጀርባ መዶለታችንን እስካልተውን ፣ የድርሻችንን ለመወጣት ታጥቀን እስካልተነሳን ድረስ ፣ ትግላችን እንደ እስከ ዛሬው “ለ አፈ ግም አፍንጫ ድፍን ያዝለታል” ሆኖ ስለመቀጠሉ አዋቂ መሆን አይጠይቅም።

የፕለቲካ ድርጅቶች መግለጫና ትርጉም

የ-ወያኔው ስርዓት እንደ ወየነ 40 ዓመት ሞላው። እኛም የዚህ ስርዓት አድማቂዎች መሆን ከጀመርን እንዲሁ። የተላዩ ያልተቀናጁ፣ በማይረባ የትግል ቅርጽ የተጠረቡ ድርጅቶችም ይሄንን ስርዓት እሱን በሚመቸው መልኩ እየታገሉት (በጩኸት እያጫፈሩት) ተጉዘዋል፣ ብዙዎቹ መሰረት አልባ፣ የማይጨበጥ፣ የማይያዝ ትግል አድርገዋል። ባንጻሩ ደሞ ጥቂቶች ደማቸውን አፍስሰዋል፣ ጥቂቶች ራሳቸውን ባደባባይ ገብረዋል፣ ጥቂቶች ተሰውተዋል። እና በዚህ በማይረባ የትግል መስመር ውስጥ ባሉትና በቆራት አቁዋም ራሳቸውን በሰዉት መሃከል ግን በሚሊዮን የሚቆጠር ሕዝብ ይህ ነው የማይባል በደል ( እስር ፣እንግልት፣ ግድያ፣ አፈና ፣ስደት እና ወዘተ ) ደርሶበታል እየደረሰበትም ነው፣ ገና ወደፊትም ይደርስበታል። ታጋዮቻችን ለአመታት ከማሳሰቢያ ያለፈ ነገር ሲያደርጉ አይስተዋሉም ” የ ወያኔ መንግስ በንጹሃን ኢትዮጵያውያኖች ላይ እያደረሰ ያለውን ነገር ባስቸኩዋይ እንዲያቆም አከሌ የተባለው ድርጅት አበክሮ አሳሰበ ” ።

እኔ እምለው እንዲህ አይነት ማስጠንቀቂያ ስትጽፉ ነው የኖራችሁት፣ በማስጠንቀቂያ ቢሆን ኖሮ ወያኔ አዲስ አበባም አይገባ ነበር። እስኪ ማስጠንቀቂያችሁ አልሰማ ሲል አጸፋ መመለስ የምትችሉ እስክትሆኑ ድረስ እባካችሁ ማስጠንቀቁን ተዉት። ይሄ ጭፍን እና መሰረት አልባ ጀብደንነት ነው አርባ ዓመት አጫፋሪ ያደረገን። እስኪ አሁን ማን ይሙት ዛሬም ( በ 2006) ማስጠንቀቂያ የምንጽፍ ሰዎች መሆን ነበርን ? “ብልህነት እንጂ ብልጠት ባከተመለት ዘመን ተፈጥረን ” ማንን ለማሞኘት ነው። ወይስ አንድን ድርጅት ድርጅት የሚያስብለው እንዲህ ነገሮች ሲጦዙ እመር እያለ በማስጠንቀቂያ ቀለም መጨረሱ ነው። አይግባኝም። እዚህ በምኖርበት ሀገር አማሪካ አንድ ሰው የቤት ክራዩን ወይም የስልክ አገልግሎት ክፍያውን በአግባቡ መፈጸም ካልቻለ ማስጠንቀቂያ ወረቀት ይደርሰዋል፣ ሰውየው/ሰትይቱ በተባለው ግዜ ክፍያውን ካልፈጸመ/መች አገልግሎት ሰጪው ድርጅት የአገልግሎት ተጠቃሚነቱዋን ይሰርዛል። ማስጠንቀቂያ ማለት እንዲህ ነው። እኛ ግን ወያኔ አርባ ዓመት ሲረብሽ፣ አርባ ዓመት ማስጠንቀቂያ የምንጽፍ ተራ ጀብደኞች ነን። በምክንያት የታጠርን፣ የማናታግል፣ የማንታገል፣ ስለ አንድነት የምንሰብክ ግለኞች ፣ በጠባብ ተሰፍረን ስለ ሆደ ሰፊነት የምናወራ። አረ እንደውም ይሄ ሆዴ ሰፊነት ስለሚባለው ነገር እናውራ። በአዲስ መስመር ይጀመር።

ሆዴ ሰፊነት ማለት ምን ማለት ነው? ጭቆናን መቀበል? በኢትዮጵያዊነት ጉዳዮች ላይ የጋራ ዝንባሌም ብቻ ሳይሆን ፍጹም ተቃራኒ በሆነ መልኩ ከሚሄዱት ጋ ፣ ኢትዮጵያ የምትባል ሀገር የለችም ከሚሉት ጋም’ እስከ መተባበር ድረስ ነው? ሆዴ ሰፊነት እና ሆደ ቡቡነት እኮ የተለያዩ ነገሮች ናቸው። እንደውም ታጋዮቻችንን የምጠይቀው ነገር አለኝ። በእውነት መታገል ትፈልጋላችሁ ? በእውነት ለውጥ ማምጣት ትፈልጋላችሁ ? በእውነት እየሆነ ያለው ነገር ይገባችሁዋል ? ቢሆን ኖሮ ዘንድሮም ወረቀት በተንን ብላችሁ ባላወራችሁ፣ ቢሆን ኖሮ እንደ ትልቅ ነገር በየ ድህረ ገጾቻችሁ የማስጠንቀቂያ ሐተታ ባላወጣችሁ። የምታደርጉት ነገር ልክ አይደልም እያልኩ አይደለም፣ ግን ከዚያ አንድ ጋት ፈቀቅ ማለት አልቻላችሁም፣ ግብራችሁ ከአንደበታችሁ ( ከምታወሩልን ነገር ጋ) ይጣረሳል። ከስብሰባና ዓመት እየጠበቁ የምስረታ በአላችሁን ከማክበር ያለፈ አንድም ነገር ስታረጉ አላየናቹም። አለን ትላላችሁ እንጂ የላችሁም። መነሳት አልቻላችሁም፣ ወጣቶች እንዲነሱ መንገድ ማሳየት አትፈልጉም፣ ከስር ሆኖ ጉልበት የሚስም እንጂ የናንተን ጉልበት ይዞ የሚነሳ ልጅ አልወላዳቹም፣ ስመቻችሁ ትውልዱን ጫታም፣ ሴሰኛ፣ ራስ ወዳድ ፣ ምናምን ብላችሁ ጥረግሙታላችሁ። ትውልዱ በማን ይውጣ፣ ማንን ይከተል፣ ምን አስተማራችሁት። ከናንተ የተማራው እምብ ማለትን ሳይሆን፣ ከእሳት መሸሽን ነው።

መስእዋትነትን የምታውቁት ከናንተ ጋ ቆመው በተሰዉት ሰዎች እንጂ በራሳችሁ አይደልም። በሰው ደም ለመንገስ ፣ በሰው ደም ለመኮፈስ፣ በሰው ደም አናት ለመሆን ከመዳዳት ውጪ ፣ ጉልበታቹም ውኔያችሁም፣ እምቢታቹም በራሳችሁ ገድል ላይ የተመሰረተ አይደለም። መጋደልንም ሆነ መሞትን ማወቅ አትፈልጉም፣ የኢትዮጵያ ጉዳይ ያሳስባችሁ ይሆናል ግን እንቅልፍ አይነሳችሁም፣ ነገሮች መስመር ሲለቁና የህዝቡ እሪታ ሰማይ ሲደርስ፣ ባፋጣኝ ድርጅት ትመሰርታላችሁ፣ የሚገርመው ከሚያልቀው ሰው ይልቅ አብልጣችሁ የምትጨነቁት ስለድርጅታችሁ ስም እና አባላት ነው። እያንዳንዱ የኢትዮጵያ መከራ ለናንተ የገንዘብ መሰብሰቢያን ዕድል ይፈጥራል፣ ይህንንም ያለ ሀፍረት ባደባባይ ታደርጉታላችሁ። ባጭሩ ትግል ምን እንደሆነ አታውቁም። እናንተን የሚያታግላችሁ በየጊዜው የሚፈነዳው የህዝብ ብሶት እንጂ አላማችሁ አይደለም። አጀንዳም፣ የትግል መዋቅርም፣ ሕልምም የላችሁም። በተገኘው አጋጣሚ ትግሉ እንዲፋፋም ትፈልጋላችሁ፣ ስለዚህ አልተሳካላችሁም፣ ምክንያቱም እያንዳንዱ አጋጣሚ የራሱ የሆኑ ውድቀቶች አሉትና።

ምሁርነታችሁ ፋና ወጊ ከመሆን ይልቅ መመጻደቂያ ስታደርጉት ነው ያየነው። በሁለት ሃሳቦች መሃከል ያለውን ልዩነት ለመፍታት የምታደርጉት ውይይት የምሁርነታችን ልክ ሳይሆን የጥላቻችሁን ቁመት ነው የሚያሳየን። ባልነበርንበት፣ በማናውቀው፣ ፍጹም ልክ የሚባል መረጃ በሌለበት ሆኔታ እንኩዋ ፍጹም ልክ የሆነ ተበዳይ እንሆናለን።

እስኪ ትንሽ ምሳሌዎች ላንሳ

ዶ/ር መራራ ጉድና ከኢሳት ጋዜጠኛ ሲሳይ አጌና ጋ ባደረገው ቃለ ምልልስ። ” አያቴም በሚኒልክ መሬታቸው ተወርሶዋል ይህም የሆነው አድዋ አልዘምትም በማለታቸው ነው ” ይላል። እንዴ ጋሼ መራራ ለካ የእርሶም አያት አድዋ አልዘምትም ብለው ነበር። እኔ ይሄ የሰሜን ባንዳዎች ታሪክ ብቻ ይመስለኝ ነበር። እንግዲህ እግዚአብሔር ይግለጥላችሁ ምንሊክ ምክንያታቸው አደዋ ዝመት ነው። አይ አድዋ አልዘምትም ! እንግዲያውስ አንተ ኢትዮጵያዊ አይደለክም ስለዚህ የኢትዮጵያውያኖች መብት ሁሉ ያንተ መብት አይደለም ይመስለኛል የምንሊክ ሃሳብ። ይሄን ውሳኔ የሚቃረኑ ሰዎች ሊኖሩ ይችላሉ ግን እስኪ ደሞ ዘንድሮ እየተደረገ ያለውን እንመልከት። መሬትትህን ሽጥ ወይም ልቀቅ ? ገበሬ ” ወይ መራራ ራሳቸው ” ለምን የህንድ ገበሬ እንዲያርስበት። አዩ ያባቶት አለመዝመት ያመጣብዎ ጣጣ ?

ፕሮፌሰር መስፍን ወልደማርያም በሰማያዊ ፓርቲ አዘጋጅነት ፣ ” መክሸፍ እንደ ኢትዮጵያ ታሪክ” የሚለው መጽሐፋቸው ላይ በሚደር ውይይት ካንድ ተሳታፊ ለቀረበላቸው ትያቄ ሲመልሱ፣

“አንዳን የሚያሳዝኑ ነገሮች ተነስተዋል እዚህ አካባቢ ነው መሰል ትግሬ ነኝ ያለ ልጅ አለ ፣ ትግሬ ነኝ ብለሃል፣ እኔም ትግሬ ነኝ፣ ነገር ግን ልዩነታችን ትግሬ ሆነህ በማንበብህና ኢትዮጵያዊ ሆነህ በማንበብህ ላይ ነው። እውነት ነው፣ ትግሬነትን እያሰቡ እንደ ኢትዮጵያዊ መኖር አይቻልም ፣ ኦሮሞነት ኢትዮጵያዊ ለመሆን ባሰበ ቁጥር የተበዳይነት እና የተገፊነት ስሜት የሚጭር ከሆነ በምንም መልኩ ኢትዮጵያዊ መሆን አይቻልም። ፋሲለደስን ስንመለከት አማራ አደረሰብን የምንለው በደል ከሆነ ትዝ የሚለን ኢትዮጵያዊ መሆን አይቻልም ፣ አክሱምን ስንመለከት የትግሬዎች ክፋት ከሆነ ትዝ የሚለን ኢትዮጵያዊ መሆን አይቻልም፣ ሰንደቅ አላማችንን ስንመለከት አሁንም ሰንደቁ ከተሸከመው ምልክታዊ ትርጉም ውጪ የአማራነት መለኪያአንድን ጎሳ የጥፋት ብብሃር ታሪክ ካደረግነው አሁንም ኢትዮጵያዊ መሆን አይቻልም። ስለ ብራና እና መሰንቆ ስናወራ ወደ አእምሮዋችን ቀድሞ የሚመጣው ቁሶቹ የኢትዮጵያውያኖች እሴት ስለ-መሆናቸው ካልሆነ ኢትዮጵያዊ መሆን ይከብዳል።

ፕሮፌሰር መስፍን ወ/ ማርያም በዚሁ ከላይ በጠቀስኩት መጽሐፋቸው ላይ “ድሃነት የጥቃት መከታ መሆኑ የልማቱ መንገድ ፍጽሞ መክሸፉን የሚያረጋግጥ መንገድ ነው ” ይላሉ።

አዋ! የተጠቂነት ስሜትን አዝሎ የተጠያቂነት ባለቤት ነው ከምንለው አካል ጋ የፖለቲካ ውህደት ሲደረግ ጥምረቱ ሳይመሰረት ይፈርሳል ። ሁለት በፍጹም የተለያየ አላማ ያላቸው አካላት ፣ በጋራ ጠላትነት የሚፈርጁት አንድ የጋራ ጠላት ስላላቸው ብቻ ውህደታቸው መፍትሄ ያመጣል ብሎ ማሰብ ዘበት ነው። አንበሳም ጅብም ሚዳቆን አድነው ይበሉ ይሆናል፣ የሚዳቁ’ዐ ምግብነት ግን አንበሳ እና ጅብን ዘመድ አያደርጋቸውም ፣ ምክንያቱም በአመጋገብ ስርዓታቸውም ይሁን ፣ በተፈጥሮ ባህሪያቸው የተለያዩ ፍጥረቶች ናቸውና።

የተበዳይነትን ስሜት የትግል አላማው አድርጎ የተነሳ ድርጅት የተሸነፈው ሲመሰረት ነው። የተፈጠረበትን ምድር፣ መልካም ምድራዊ አቀማመጥ፣ የህዝቡን ባህል፣ ስነልቦናና ታሪክ ወደ ጎን ጥሎ ፣ መሆን አለበት ብሎ ስለሚያስበው ነገር ብቻ እያሰበ በርሃ የወረደ ታጋይ ቢያሸንፍም እንኩዋ ተሸንፎዋል ፣ ለዚህ ከወያኔ የተሻል ጥሩ ምሳሌ ማግኘት አንችልም። ግን ማሸነፍ ብለን የምንለው፣ መንበሩን መቆናጠጥ፣ ወዲህ ሂድ፣ ወዲህ ተመለስ የሚል ት’ዛዝን መስጠት ከሆነ እሱ ሌላ ነገር ነው። እንደምሳሌ ብዙ ግዜ የምሰማው እና የሚገርመኝ ነገር አለ። አብዛኛዎቹ የትግል አቀንቃኞች ” ወያኔን አሸንፈን መስቀል አደባባይ ተሰብስበን እንዲህ እናደርጋለን ፣ እንዘፍናለን፣ አንተም ሄኖክ ግጥም ታነብልናለህ ወዘተ ወዘተ ሲሉ መስማት አሁን አሁን የተለመደ ነገር ሆኖዋል ። ቁም ነገሩ እኮ መስቀል አደባባይ ላይ መደነስ አይመስለኝም ፣ዳንሱ የድሉ ማድመቂያ እንጂ የድሉ የመጨረሻ ግብ መሆን አለበትም ብዬ አላስብም። ሕልማችን ከድል አጥቢያ ጭፈራ ልቆ መሄድ ያለበት ይመስለኛል። ፍጹም ተገዢዎች ሆነን ሳለ ከድል ማግስት ስለምንረግጠው ጮቤ ከሆነ የምናስበው፣ ገና ስንነሳ ነው የወደቅነው። የትግል አላማ ከዚህ ሁሉ ፍሬ ከርስኪ ሃሳቦች ይልቃል የሚባለው ለዚያ ነው። ታግለው አሸንፈው ለውጥ ማምጣት በቻሉትና ምንም ባልተሳካላቸው ( እንደውም ወደ ባሰ መቀመቅ በመሩን) መሪዎቻችን መሃከልም ያለው ልዩነት ይሄው ነው ። የትግላቸው መነሻ እራሳቸውን ደርሶብናል ብለው ያሳመኑት በደል ሲሆን፣ መድረሻው ደሞ በቀል ነው።

ጆን ዶኔ (ትርጉም በቀብጽ እና በግርድፉ ) ብቻህን ተነጥለህ የምትኖር አንተ ማነ ነህ? ደንመና ውቂያኖሱን ቢጠርገው አውሮጳ ታንሳለች፣ የማንም ሰው ሞት እኔን ያጎለኛል ምክንያቱም ሰው ነኝና ምናምን ይላል ) በሱ ቁዋንቁዋ

No man is an island,
Entire of itself,
Every man is a piece of the continent, A part of the main.
If a clod be washed away by the sea, Europe is the less.
As well as if a promontory were.

As well as if a manor of thy friend’s
Or of thine own were:
Any man’s death diminishes me,
Because I am involved in mankind,
And therefore never send to know for whom the bell tolls; It tolls for thee.

እኔም ከሱ የተለየ ስሜትም እምነትም የለኝም፣ ግን ሞትህ የሚያሳዝነኝ ቢያንስ ቢያንስ አንተ በኔ ሞት ባታዝን እንኩዋ ደስተኛ እስካልሆንክ ነው። አንተ ለኔ መቆም ባፀራ እንኩዋ ለጥፋቴ እስካልታተርክ ድረስ ነው። አዎ ሞትህ ያሳዝነኛል፣ በደልህ ያመኛል፣ ስቃይህ ይቆጨኛል፣ ግን ቢያንስ ቢያንስ የሃዘኔን ያህል ባይሆንም እንኩዋ የሰው ልጆች የመሆናችንን ያህል አንተም ለኔ ፍቅር ይኑርህ። እኛ ግን እንደዚያ አይነት አይደለንም እኛ

“No man can Judge his agony against an objective scale, his toothache is more than a 1000 death in another part of continent “

እንዳለው አይነቶች ሆንን። ላይቤርያ ውስጥ አንድ ሺ ሰው አለቀ ሲሉን ” የራሳቸው ጉዳይ እኔ ጥርሴን አሞኛል ” የምንል ሆነን። የበደል ትንሽ የለውም፣ የሞት ግማሽ የለውም።

አንተ አንቦ ላይ ስትገደል ለምን አላዘንክም አትበለኘን ይልቅ እኔ ሌሎች ሲበደሉ ተሙዋግቼላቸዋለሁ ወይ ብለህ ራስህን ጠይቅ፣ እምነት ቢኖርም ባይኖርም በሰፈሩት ቁና መሰፈር አይቀርም፣ ተሰፋፋሪ ሆኖ ከመኖር ግን የሚሻለው ተፋቅሮ መኖር ነው። ፍቅርን መሰረት ያላደረገ ትግል ፣ እሱም ላይ ሌላ ትግል እንዲነሳ ያደርጋል እንጂ የለውጥ ምሰሶ አይሆንም። በእርግጥ እወድሃለሁ፣ በእርግጥ ግማሽ ማንነቴ አንተ ነህ፣ ግን ፍቅሬን መሰረት አልባ አታድርገው፣ ካንተም፣ ከራሴም ፣ ከማውው ጥሩ ነገር ሁሉ ሃገሬን አስቀድማለሁ፣ ምክንያቱ ደሞ አማራ ወይ ኦሮሞ ስለሆንኩ አይደልም፣ ምክንያቱ እኔና አንተ አላፊና ጠፍ መሆናችንን ስለማውቅ ነው። ስለዚህ አስብ ይሄ የምለውን ነገር ትግሬ ሆነህ አታንብበው ይልቁንስ ኢትዮጵያዊ ሆነህ አንብበው።

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm
  • የተመሠረተው የፋኖ አደረጃጀት ዋነኛ ዓላማው ድርድር መሆኑ ተነገረ May 14, 2025 11:07 pm
  • ከፍተኛ የፋኖ አመራሮች መገደላቸው ተነገረ May 6, 2025 10:40 pm
  • ሃይማኖትን ለተራ የፖለቲካ ሸቀጥ ማዋል ውርደት ነው April 24, 2025 12:43 am
  •  የኬሪያ ኢብራሒም ኑዛዜ “ብትንትናችን ወጥቷል” April 22, 2025 12:08 am
  • ለወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን አመራሮች ወታደራዊ ሥልጠና ተሰጠ April 16, 2025 11:44 pm
  • ዓቅም እንደሌለው የገመገመው ሻዕቢያ ፊቱን ከጦርነት ወደ ዲፕሎማሲ እያዞረ ነው   April 15, 2025 12:32 am
  • “አንድ የፋኖ ተቋም (የእስክንድር) ተመሥርቷል፤ ሌሎቹ ደግሞ እንዲሁ አንድ ተቋም መሥርተው ወደዚህ ይመጡ” አበበ ጢሞ April 11, 2025 12:07 am
  • መለስ (ለገሰ) ዜናዊ – ተዋርዶ ያዋረደን! April 9, 2025 10:28 pm
  • የተከዜ ዘብ: የሉዓላዊነት መጠበቂያ April 8, 2025 11:49 pm
  • አዲስ አበባ አስተዳደር የሪፖርተርን የተዛባ መረጃ ኮነነ፤ ሕጋዊ እርምጃ እወስዳለሁ አለ April 8, 2025 10:06 pm
  • ሀሰተኛውን የሪፖርተር ዘገባ ንግድ ባንክ በጽኑ ተቃወመ፤ እርማትም ጠየቀ April 8, 2025 09:48 pm
  • “ኦሮሚያ ላይ ወይም ሌላ ቦታ ላይ ስታደርገው ከነበረ ትግራይ ወስጥም የማታደርግበት ምንም ምክንያት አይኖርህም” ነው ጌታቸው ረዳ April 7, 2025 10:22 pm
  • “TPLF’s belief in a strong federal government was always tied to its own dominance in Addis Ababa” April 7, 2025 10:15 pm
  • Counter-Video by EBC Challenges EBS Broadcast, Sparks Public Outcry Over Alleged Misinformation March 31, 2025 02:36 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule