• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ኢትዮጵያዊነት – ክፍል አንድና ሁለት

May 13, 2014 12:12 am by Editor Leave a Comment

ኢትዮጵያዊነት በተቃርኖ የተሞላ የግሳንግስ ስብስብ አይደለም። ኢትዮጵያዊነት የወጪት ሰባሪዎች ትግል፣ ለኔ በገሌ ነው ባዮች ምክር አይደለም። ኢትዮጵያዊነት በበግ ጸጉር ቡክርናውን እንደቀውማው ያዕቆብም ( “አታላይ ማለት ነው”) አይነትም አይደለም። በጎሳ አሽክላ ተተብትበን፣ በቂም ቆመን፣ ጭረት አመርቅዘን ቁስል አርገን ፣ የዛሬ ውድቀታችንን ፣ የዘምን ምክነት አስመስለን፣ ላለመቻላችን መወጣጫ፣ ላለመቆማችን የ ምክንያት መቆናጠጫ ብንፈልግ ፣ ካለፈ ጥፋትም ሆነ ሕዝብ ካለፈለት እውነት ጀርባ መዶለታችንን እስካልተውን ፣ የድርሻችንን ለመወጣት ታጥቀን እስካልተነሳን ድረስ ፣ ትግላችን እንደ እስከ ዛሬው “ለ አፈ ግም አፍንጫ ድፍን ያዝለታል” ሆኖ ስለመቀጠሉ አዋቂ መሆን አይጠይቅም።

የፕለቲካ ድርጅቶች መግለጫና ትርጉም

የ-ወያኔው ስርዓት እንደ ወየነ 40 ዓመት ሞላው። እኛም የዚህ ስርዓት አድማቂዎች መሆን ከጀመርን እንዲሁ። የተላዩ ያልተቀናጁ፣ በማይረባ የትግል ቅርጽ የተጠረቡ ድርጅቶችም ይሄንን ስርዓት እሱን በሚመቸው መልኩ እየታገሉት (በጩኸት እያጫፈሩት) ተጉዘዋል፣ ብዙዎቹ መሰረት አልባ፣ የማይጨበጥ፣ የማይያዝ ትግል አድርገዋል። ባንጻሩ ደሞ ጥቂቶች ደማቸውን አፍስሰዋል፣ ጥቂቶች ራሳቸውን ባደባባይ ገብረዋል፣ ጥቂቶች ተሰውተዋል። እና በዚህ በማይረባ የትግል መስመር ውስጥ ባሉትና በቆራት አቁዋም ራሳቸውን በሰዉት መሃከል ግን በሚሊዮን የሚቆጠር ሕዝብ ይህ ነው የማይባል በደል ( እስር ፣እንግልት፣ ግድያ፣ አፈና ፣ስደት እና ወዘተ ) ደርሶበታል እየደረሰበትም ነው፣ ገና ወደፊትም ይደርስበታል። ታጋዮቻችን ለአመታት ከማሳሰቢያ ያለፈ ነገር ሲያደርጉ አይስተዋሉም ” የ ወያኔ መንግስ በንጹሃን ኢትዮጵያውያኖች ላይ እያደረሰ ያለውን ነገር ባስቸኩዋይ እንዲያቆም አከሌ የተባለው ድርጅት አበክሮ አሳሰበ ” ።

እኔ እምለው እንዲህ አይነት ማስጠንቀቂያ ስትጽፉ ነው የኖራችሁት፣ በማስጠንቀቂያ ቢሆን ኖሮ ወያኔ አዲስ አበባም አይገባ ነበር። እስኪ ማስጠንቀቂያችሁ አልሰማ ሲል አጸፋ መመለስ የምትችሉ እስክትሆኑ ድረስ እባካችሁ ማስጠንቀቁን ተዉት። ይሄ ጭፍን እና መሰረት አልባ ጀብደንነት ነው አርባ ዓመት አጫፋሪ ያደረገን። እስኪ አሁን ማን ይሙት ዛሬም ( በ 2006) ማስጠንቀቂያ የምንጽፍ ሰዎች መሆን ነበርን ? “ብልህነት እንጂ ብልጠት ባከተመለት ዘመን ተፈጥረን ” ማንን ለማሞኘት ነው። ወይስ አንድን ድርጅት ድርጅት የሚያስብለው እንዲህ ነገሮች ሲጦዙ እመር እያለ በማስጠንቀቂያ ቀለም መጨረሱ ነው። አይግባኝም። እዚህ በምኖርበት ሀገር አማሪካ አንድ ሰው የቤት ክራዩን ወይም የስልክ አገልግሎት ክፍያውን በአግባቡ መፈጸም ካልቻለ ማስጠንቀቂያ ወረቀት ይደርሰዋል፣ ሰውየው/ሰትይቱ በተባለው ግዜ ክፍያውን ካልፈጸመ/መች አገልግሎት ሰጪው ድርጅት የአገልግሎት ተጠቃሚነቱዋን ይሰርዛል። ማስጠንቀቂያ ማለት እንዲህ ነው። እኛ ግን ወያኔ አርባ ዓመት ሲረብሽ፣ አርባ ዓመት ማስጠንቀቂያ የምንጽፍ ተራ ጀብደኞች ነን። በምክንያት የታጠርን፣ የማናታግል፣ የማንታገል፣ ስለ አንድነት የምንሰብክ ግለኞች ፣ በጠባብ ተሰፍረን ስለ ሆደ ሰፊነት የምናወራ። አረ እንደውም ይሄ ሆዴ ሰፊነት ስለሚባለው ነገር እናውራ። በአዲስ መስመር ይጀመር።

ሆዴ ሰፊነት ማለት ምን ማለት ነው? ጭቆናን መቀበል? በኢትዮጵያዊነት ጉዳዮች ላይ የጋራ ዝንባሌም ብቻ ሳይሆን ፍጹም ተቃራኒ በሆነ መልኩ ከሚሄዱት ጋ ፣ ኢትዮጵያ የምትባል ሀገር የለችም ከሚሉት ጋም’ እስከ መተባበር ድረስ ነው? ሆዴ ሰፊነት እና ሆደ ቡቡነት እኮ የተለያዩ ነገሮች ናቸው። እንደውም ታጋዮቻችንን የምጠይቀው ነገር አለኝ። በእውነት መታገል ትፈልጋላችሁ ? በእውነት ለውጥ ማምጣት ትፈልጋላችሁ ? በእውነት እየሆነ ያለው ነገር ይገባችሁዋል ? ቢሆን ኖሮ ዘንድሮም ወረቀት በተንን ብላችሁ ባላወራችሁ፣ ቢሆን ኖሮ እንደ ትልቅ ነገር በየ ድህረ ገጾቻችሁ የማስጠንቀቂያ ሐተታ ባላወጣችሁ። የምታደርጉት ነገር ልክ አይደልም እያልኩ አይደለም፣ ግን ከዚያ አንድ ጋት ፈቀቅ ማለት አልቻላችሁም፣ ግብራችሁ ከአንደበታችሁ ( ከምታወሩልን ነገር ጋ) ይጣረሳል። ከስብሰባና ዓመት እየጠበቁ የምስረታ በአላችሁን ከማክበር ያለፈ አንድም ነገር ስታረጉ አላየናቹም። አለን ትላላችሁ እንጂ የላችሁም። መነሳት አልቻላችሁም፣ ወጣቶች እንዲነሱ መንገድ ማሳየት አትፈልጉም፣ ከስር ሆኖ ጉልበት የሚስም እንጂ የናንተን ጉልበት ይዞ የሚነሳ ልጅ አልወላዳቹም፣ ስመቻችሁ ትውልዱን ጫታም፣ ሴሰኛ፣ ራስ ወዳድ ፣ ምናምን ብላችሁ ጥረግሙታላችሁ። ትውልዱ በማን ይውጣ፣ ማንን ይከተል፣ ምን አስተማራችሁት። ከናንተ የተማራው እምብ ማለትን ሳይሆን፣ ከእሳት መሸሽን ነው።

መስእዋትነትን የምታውቁት ከናንተ ጋ ቆመው በተሰዉት ሰዎች እንጂ በራሳችሁ አይደልም። በሰው ደም ለመንገስ ፣ በሰው ደም ለመኮፈስ፣ በሰው ደም አናት ለመሆን ከመዳዳት ውጪ ፣ ጉልበታቹም ውኔያችሁም፣ እምቢታቹም በራሳችሁ ገድል ላይ የተመሰረተ አይደለም። መጋደልንም ሆነ መሞትን ማወቅ አትፈልጉም፣ የኢትዮጵያ ጉዳይ ያሳስባችሁ ይሆናል ግን እንቅልፍ አይነሳችሁም፣ ነገሮች መስመር ሲለቁና የህዝቡ እሪታ ሰማይ ሲደርስ፣ ባፋጣኝ ድርጅት ትመሰርታላችሁ፣ የሚገርመው ከሚያልቀው ሰው ይልቅ አብልጣችሁ የምትጨነቁት ስለድርጅታችሁ ስም እና አባላት ነው። እያንዳንዱ የኢትዮጵያ መከራ ለናንተ የገንዘብ መሰብሰቢያን ዕድል ይፈጥራል፣ ይህንንም ያለ ሀፍረት ባደባባይ ታደርጉታላችሁ። ባጭሩ ትግል ምን እንደሆነ አታውቁም። እናንተን የሚያታግላችሁ በየጊዜው የሚፈነዳው የህዝብ ብሶት እንጂ አላማችሁ አይደለም። አጀንዳም፣ የትግል መዋቅርም፣ ሕልምም የላችሁም። በተገኘው አጋጣሚ ትግሉ እንዲፋፋም ትፈልጋላችሁ፣ ስለዚህ አልተሳካላችሁም፣ ምክንያቱም እያንዳንዱ አጋጣሚ የራሱ የሆኑ ውድቀቶች አሉትና።

ምሁርነታችሁ ፋና ወጊ ከመሆን ይልቅ መመጻደቂያ ስታደርጉት ነው ያየነው። በሁለት ሃሳቦች መሃከል ያለውን ልዩነት ለመፍታት የምታደርጉት ውይይት የምሁርነታችን ልክ ሳይሆን የጥላቻችሁን ቁመት ነው የሚያሳየን። ባልነበርንበት፣ በማናውቀው፣ ፍጹም ልክ የሚባል መረጃ በሌለበት ሆኔታ እንኩዋ ፍጹም ልክ የሆነ ተበዳይ እንሆናለን።

እስኪ ትንሽ ምሳሌዎች ላንሳ

ዶ/ር መራራ ጉድና ከኢሳት ጋዜጠኛ ሲሳይ አጌና ጋ ባደረገው ቃለ ምልልስ። ” አያቴም በሚኒልክ መሬታቸው ተወርሶዋል ይህም የሆነው አድዋ አልዘምትም በማለታቸው ነው ” ይላል። እንዴ ጋሼ መራራ ለካ የእርሶም አያት አድዋ አልዘምትም ብለው ነበር። እኔ ይሄ የሰሜን ባንዳዎች ታሪክ ብቻ ይመስለኝ ነበር። እንግዲህ እግዚአብሔር ይግለጥላችሁ ምንሊክ ምክንያታቸው አደዋ ዝመት ነው። አይ አድዋ አልዘምትም ! እንግዲያውስ አንተ ኢትዮጵያዊ አይደለክም ስለዚህ የኢትዮጵያውያኖች መብት ሁሉ ያንተ መብት አይደለም ይመስለኛል የምንሊክ ሃሳብ። ይሄን ውሳኔ የሚቃረኑ ሰዎች ሊኖሩ ይችላሉ ግን እስኪ ደሞ ዘንድሮ እየተደረገ ያለውን እንመልከት። መሬትትህን ሽጥ ወይም ልቀቅ ? ገበሬ ” ወይ መራራ ራሳቸው ” ለምን የህንድ ገበሬ እንዲያርስበት። አዩ ያባቶት አለመዝመት ያመጣብዎ ጣጣ ?

ፕሮፌሰር መስፍን ወልደማርያም በሰማያዊ ፓርቲ አዘጋጅነት ፣ ” መክሸፍ እንደ ኢትዮጵያ ታሪክ” የሚለው መጽሐፋቸው ላይ በሚደር ውይይት ካንድ ተሳታፊ ለቀረበላቸው ትያቄ ሲመልሱ፣

“አንዳን የሚያሳዝኑ ነገሮች ተነስተዋል እዚህ አካባቢ ነው መሰል ትግሬ ነኝ ያለ ልጅ አለ ፣ ትግሬ ነኝ ብለሃል፣ እኔም ትግሬ ነኝ፣ ነገር ግን ልዩነታችን ትግሬ ሆነህ በማንበብህና ኢትዮጵያዊ ሆነህ በማንበብህ ላይ ነው። እውነት ነው፣ ትግሬነትን እያሰቡ እንደ ኢትዮጵያዊ መኖር አይቻልም ፣ ኦሮሞነት ኢትዮጵያዊ ለመሆን ባሰበ ቁጥር የተበዳይነት እና የተገፊነት ስሜት የሚጭር ከሆነ በምንም መልኩ ኢትዮጵያዊ መሆን አይቻልም። ፋሲለደስን ስንመለከት አማራ አደረሰብን የምንለው በደል ከሆነ ትዝ የሚለን ኢትዮጵያዊ መሆን አይቻልም ፣ አክሱምን ስንመለከት የትግሬዎች ክፋት ከሆነ ትዝ የሚለን ኢትዮጵያዊ መሆን አይቻልም፣ ሰንደቅ አላማችንን ስንመለከት አሁንም ሰንደቁ ከተሸከመው ምልክታዊ ትርጉም ውጪ የአማራነት መለኪያአንድን ጎሳ የጥፋት ብብሃር ታሪክ ካደረግነው አሁንም ኢትዮጵያዊ መሆን አይቻልም። ስለ ብራና እና መሰንቆ ስናወራ ወደ አእምሮዋችን ቀድሞ የሚመጣው ቁሶቹ የኢትዮጵያውያኖች እሴት ስለ-መሆናቸው ካልሆነ ኢትዮጵያዊ መሆን ይከብዳል።

ፕሮፌሰር መስፍን ወ/ ማርያም በዚሁ ከላይ በጠቀስኩት መጽሐፋቸው ላይ “ድሃነት የጥቃት መከታ መሆኑ የልማቱ መንገድ ፍጽሞ መክሸፉን የሚያረጋግጥ መንገድ ነው ” ይላሉ።

አዋ! የተጠቂነት ስሜትን አዝሎ የተጠያቂነት ባለቤት ነው ከምንለው አካል ጋ የፖለቲካ ውህደት ሲደረግ ጥምረቱ ሳይመሰረት ይፈርሳል ። ሁለት በፍጹም የተለያየ አላማ ያላቸው አካላት ፣ በጋራ ጠላትነት የሚፈርጁት አንድ የጋራ ጠላት ስላላቸው ብቻ ውህደታቸው መፍትሄ ያመጣል ብሎ ማሰብ ዘበት ነው። አንበሳም ጅብም ሚዳቆን አድነው ይበሉ ይሆናል፣ የሚዳቁ’ዐ ምግብነት ግን አንበሳ እና ጅብን ዘመድ አያደርጋቸውም ፣ ምክንያቱም በአመጋገብ ስርዓታቸውም ይሁን ፣ በተፈጥሮ ባህሪያቸው የተለያዩ ፍጥረቶች ናቸውና።

የተበዳይነትን ስሜት የትግል አላማው አድርጎ የተነሳ ድርጅት የተሸነፈው ሲመሰረት ነው። የተፈጠረበትን ምድር፣ መልካም ምድራዊ አቀማመጥ፣ የህዝቡን ባህል፣ ስነልቦናና ታሪክ ወደ ጎን ጥሎ ፣ መሆን አለበት ብሎ ስለሚያስበው ነገር ብቻ እያሰበ በርሃ የወረደ ታጋይ ቢያሸንፍም እንኩዋ ተሸንፎዋል ፣ ለዚህ ከወያኔ የተሻል ጥሩ ምሳሌ ማግኘት አንችልም። ግን ማሸነፍ ብለን የምንለው፣ መንበሩን መቆናጠጥ፣ ወዲህ ሂድ፣ ወዲህ ተመለስ የሚል ት’ዛዝን መስጠት ከሆነ እሱ ሌላ ነገር ነው። እንደምሳሌ ብዙ ግዜ የምሰማው እና የሚገርመኝ ነገር አለ። አብዛኛዎቹ የትግል አቀንቃኞች ” ወያኔን አሸንፈን መስቀል አደባባይ ተሰብስበን እንዲህ እናደርጋለን ፣ እንዘፍናለን፣ አንተም ሄኖክ ግጥም ታነብልናለህ ወዘተ ወዘተ ሲሉ መስማት አሁን አሁን የተለመደ ነገር ሆኖዋል ። ቁም ነገሩ እኮ መስቀል አደባባይ ላይ መደነስ አይመስለኝም ፣ዳንሱ የድሉ ማድመቂያ እንጂ የድሉ የመጨረሻ ግብ መሆን አለበትም ብዬ አላስብም። ሕልማችን ከድል አጥቢያ ጭፈራ ልቆ መሄድ ያለበት ይመስለኛል። ፍጹም ተገዢዎች ሆነን ሳለ ከድል ማግስት ስለምንረግጠው ጮቤ ከሆነ የምናስበው፣ ገና ስንነሳ ነው የወደቅነው። የትግል አላማ ከዚህ ሁሉ ፍሬ ከርስኪ ሃሳቦች ይልቃል የሚባለው ለዚያ ነው። ታግለው አሸንፈው ለውጥ ማምጣት በቻሉትና ምንም ባልተሳካላቸው ( እንደውም ወደ ባሰ መቀመቅ በመሩን) መሪዎቻችን መሃከልም ያለው ልዩነት ይሄው ነው ። የትግላቸው መነሻ እራሳቸውን ደርሶብናል ብለው ያሳመኑት በደል ሲሆን፣ መድረሻው ደሞ በቀል ነው።

ጆን ዶኔ (ትርጉም በቀብጽ እና በግርድፉ ) ብቻህን ተነጥለህ የምትኖር አንተ ማነ ነህ? ደንመና ውቂያኖሱን ቢጠርገው አውሮጳ ታንሳለች፣ የማንም ሰው ሞት እኔን ያጎለኛል ምክንያቱም ሰው ነኝና ምናምን ይላል ) በሱ ቁዋንቁዋ

No man is an island,
Entire of itself,
Every man is a piece of the continent, A part of the main.
If a clod be washed away by the sea, Europe is the less.
As well as if a promontory were.

As well as if a manor of thy friend’s
Or of thine own were:
Any man’s death diminishes me,
Because I am involved in mankind,
And therefore never send to know for whom the bell tolls; It tolls for thee.

እኔም ከሱ የተለየ ስሜትም እምነትም የለኝም፣ ግን ሞትህ የሚያሳዝነኝ ቢያንስ ቢያንስ አንተ በኔ ሞት ባታዝን እንኩዋ ደስተኛ እስካልሆንክ ነው። አንተ ለኔ መቆም ባፀራ እንኩዋ ለጥፋቴ እስካልታተርክ ድረስ ነው። አዎ ሞትህ ያሳዝነኛል፣ በደልህ ያመኛል፣ ስቃይህ ይቆጨኛል፣ ግን ቢያንስ ቢያንስ የሃዘኔን ያህል ባይሆንም እንኩዋ የሰው ልጆች የመሆናችንን ያህል አንተም ለኔ ፍቅር ይኑርህ። እኛ ግን እንደዚያ አይነት አይደለንም እኛ

“No man can Judge his agony against an objective scale, his toothache is more than a 1000 death in another part of continent “

እንዳለው አይነቶች ሆንን። ላይቤርያ ውስጥ አንድ ሺ ሰው አለቀ ሲሉን ” የራሳቸው ጉዳይ እኔ ጥርሴን አሞኛል ” የምንል ሆነን። የበደል ትንሽ የለውም፣ የሞት ግማሽ የለውም።

አንተ አንቦ ላይ ስትገደል ለምን አላዘንክም አትበለኘን ይልቅ እኔ ሌሎች ሲበደሉ ተሙዋግቼላቸዋለሁ ወይ ብለህ ራስህን ጠይቅ፣ እምነት ቢኖርም ባይኖርም በሰፈሩት ቁና መሰፈር አይቀርም፣ ተሰፋፋሪ ሆኖ ከመኖር ግን የሚሻለው ተፋቅሮ መኖር ነው። ፍቅርን መሰረት ያላደረገ ትግል ፣ እሱም ላይ ሌላ ትግል እንዲነሳ ያደርጋል እንጂ የለውጥ ምሰሶ አይሆንም። በእርግጥ እወድሃለሁ፣ በእርግጥ ግማሽ ማንነቴ አንተ ነህ፣ ግን ፍቅሬን መሰረት አልባ አታድርገው፣ ካንተም፣ ከራሴም ፣ ከማውው ጥሩ ነገር ሁሉ ሃገሬን አስቀድማለሁ፣ ምክንያቱ ደሞ አማራ ወይ ኦሮሞ ስለሆንኩ አይደልም፣ ምክንያቱ እኔና አንተ አላፊና ጠፍ መሆናችንን ስለማውቅ ነው። ስለዚህ አስብ ይሄ የምለውን ነገር ትግሬ ሆነህ አታንብበው ይልቁንስ ኢትዮጵያዊ ሆነህ አንብበው።

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule