I would like to deeply thank distinguished members of the Society of Ethiopians Established in Diaspora (SEED) and my fellows’ citizens of Ethiopia for this recognition. I am both humbled and honored to be here tonight as a recipient of this award. I receive this honor with deep gratitude and great humility. I want to acknowledge others who have helped make this possible because, although I am accepting this award, this is not only about me. I did not come to this point alone, but must recognize … [Read more...] about “The Journey to a New Vision for Ethiopia”
Archives for May 2014
የሞረሽ ሕዝባዊ ስብሰባ ጥሪ
40 – 23 የኢህአዴግ የጎሳና የመጥበብ ሰረገላ ሐዲዱ ላይ ነውን?
ህወሃት በነጻ አውጪ ስም ታግሎ ኢትዮጵያን መግዛት የጀመረበትን 23ኛ ዓመት በዓሉን እያከበረ ነው። ወዳጆቹና መሪዎቹ ባስቀመጡት እቅድ መሰረት ኢትዮጵያን "በመተካካትና በተሃድሶ" ስም ራሱን እያገላበጠ ለመግዛት የቆረጠው ጊዜ በትንሹ 40 ዓመታት እንደሆነ ይታወቃል። አሁን ባለው የሰረገላው ጉዞ ኢህአዴግ ከ40 - 23 ከመቀነሱ ውጪ አሰበበት ስለመድረሱ መገመት የሚያስችል ምልክት የለም። እንደውም ስጋት እንጂ። ሲጀመር "የገበሬ ተሟጋች" ነኝ በማለት ራሱን የአርሶ አደሩ ወኪል አድርጎ የተነሳው ህወሃት፣ ኢህአዴግ ሆኖ አገር መግዛት ሲጀምር ያስቀደመው የብሄር ብሄረሰቦችን የመብት ጥያቄ እንደ ውዳሴ ጸሎት በመደጋገም ነበር። በዚሁ በጎሳ ላይ ተመስርቶ በቋንቋ የተቆለፈው የአገዛዝ ስልት ሲጀመር ማስጠንቀቂያ የሰጡ፣ ለመታገል የሞከሩ፣ የታገሉ፣ ያስተባበሩ፣ ያደራጁ የህወሃት የ40 ዓመት ጉዞ … [Read more...] about 40 – 23 የኢህአዴግ የጎሳና የመጥበብ ሰረገላ ሐዲዱ ላይ ነውን?
ጠረኑ የሚከረፋው የግንቦት ሃያ 23ኛ ዓመት “ዓመድ”
ሚስት ከቤቷ ጥጋ ጥግ ትንንሽ ጊዜያዊ ጉልቻ ጎልታ ካንዱ ወዳንዱ እየተዛወረች ስራዋን ስትሰራ፣ ስትቀቅል፣ ስታነኩር፣ ስትጋግር፣ ስትወጠውጥ … ድንገት ባንዱ አቅጣጫ እሳቱ መልኩን ቀየረ። ቀስ ብሎ ለካስ ወደ ቤቱ ተዛምቶ ነበርና ቤቱ ነደደ። እሳቱን ያዩ ለማጥፋት እየተሯሯጡ ደረሱ። አልሆነም የቤተሰቡ መኖሪያ ነደደ። ቤቱ የቆመው ለመቀጣጠል በሚያመች ማዋቀሪያ ነበርና ወደ አመድ ተቀየረ። ልክ እንደ ጎሳ ፖለቲካ!! እንደ ግንቦት 20 ዓመዳማ ፍሬዎች!! እሳቱን ለማጥፋት የሞክሩት ጎረቤቶች አዘኑ። "እሳት በቀላሉ የሚበላው ቤት ይዘሽ ዙሪያውን እሳት ማቀጣጠል አልነበረብሽም" ብለው ገሰጿት። ማጣፊያው ያጠራት ሴት "እባካችሁ ባለቤቴ ሲመጣ አትንገሩት" አለቻቸውና ተማጸነች። ጎረቤቶቿ በንግግሯ ተገርመው "ከሄደበት ሲመጣ የሚገባበት ካገኘ ማን ይነግረዋል" ብለዋት ተሰናበቷት። "ቤት ባገር … [Read more...] about ጠረኑ የሚከረፋው የግንቦት ሃያ 23ኛ ዓመት “ዓመድ”
ማሳሰቢያ ለእሥራኤል መንግስት
አንተ የተከበርክ የእሥራእል መንግስት ሆይ! ከያዕቆብ፣ ከዳዊት እና ከታቦተ ጽዮን አምሊክ የተላከ መልዕክትና አደራ ተቀበል፡፡ (ሙሉውን መልክት ለማንበብ እዚህ ላይ ይጫኑ) … [Read more...] about ማሳሰቢያ ለእሥራኤል መንግስት
ልማታዊ ፓትርያርክ
መግቢያ ይህችን ክታብ በዚህ ርእስ እንዳዘጋጅ ያነሳሳችኝ “ልማታዊ መንግስት-እንደ ቻይና፤ ነገሩስ ባልከፋ” በሚል ርእስ ዶ/ር ደስታው አንዳርጌ ግንቦት ፲ ቀን ፪ሺ፮ ዓ.ም ያቀረቡልን ክታብ ናት። ከሀ እስከ ሠ ተዘርዝራ የቀረበችውን ይህችን ክታብ ሳነብ፤ እንደኔ ያለውን እንቅልፋም ተማሪ ቀስቃሽ ምሁር፤ በክታባቸው አማካይነት ጣቴን ይዘው ወደ ጠቀሷቸው አገሮች ወደ እስያ፤ ቻይና፤ ታይዋንና ጃፓን በመንፈስ ወሰዱኝ። ተመልከት! ልማታዊ መንግስት ይሉሀል:: ሰላም በምድራቸው፤ በጎ ፈቃድ በዜጎቻቸው አዕምሮ እና ስነ ልቡና ላይ ልማትን የመሰረቱ እነዚህ የቻይና የጃፓንና የታይዋን መንግስታት ናቸው። የኢትዮጵያ መንግሥት የዘረጋው የልማት ግን፤ በጅብና በአህያ፤ በተኩላና በበግ፤ በጃርትና በዱባ መካከል የተዘረጋ የልማታ ተቃራኒ ጥፋት ነው።” እያሉ በማነጻጸር ያስጎበኙኝ መሰለኝ። ቀጥለውም፤ … [Read more...] about ልማታዊ ፓትርያርክ
የኢትዮጵያ ህዝብ ይወቅልኝ!
እኔ ወ/ሮ እታገኝ መኮንን ካሣ አድራሻ፡- አዲስ አበባ የካ ክ/ከተማ ወረዳ 09 የቤት ቁጥር 760/ሀ ነዋሪ ነኝ፡፡ በአሁኑ የካ ክ/ከተማ ወረዳ 09 ከላይ ቁጥሩ በተገለፀበት ቤት ከ40 ዓመት በላይ ተከ ራይቼ ስኖር በ1990 ዓ.ም በኤች አይ ቪ ኤድስ ቫይረስ መያዜን አወኩ፡፡ ቤቴንም ሆነ ልጆቼን እን ዲጠብቅልኝና እንዲረዳኝ በማለት ከ1994-1997ዓ.ም ድረስ በውክልና ሰጥቸው የነበረ ሲሆን ከ97 በኋላ ግን ውክልናውን ትቶ የራሱን ቤት ሰርቶ ሄዷል፡፡ ቤቱ እስከታሸገበት ጥር 12 ቀን 2003 ዓ.ም ድረስ ለአቶ ደረጄ ጎዳና ከመንግስት ተከራይ በማስመሰል በቤት ቁጥር 760/ሐ በአቶ ደረጄ ስም የአንድ አመት (በ1998 ዓ.ም) የቤት ኪራይ በስማቸው ቀበሌ ሂዶ ከፍሏል በማለት እኔ ደካማና በሽተኛዋን የፍርድ ቤት ውሳኔ ነው በማለት ቤቴን ጥር 12 ቀን 2006 ዓ.ም ጀምሮ በመ ድኃኒቴ … [Read more...] about የኢትዮጵያ ህዝብ ይወቅልኝ!
የግንቦት 20 “ፍሬዎች”
ነገረ ኢትዮጵያ የግንቦት 20 ልዩ እትም ጋዜጣዋ የግንቦት 20 "ፍሬዎች" ተዳሰውባታል፡፡ (ለማንበብ እዚህ ላይ ይጫኑ) ታምራት ታረቀኝ የግንቦት 20 ሰለባ የሆኑትንና ሐኪም አጥተው የሞቱትን እውቁን ሐኪም ፕሮፌሰር አስራት ወልደየስ ያስታውሰናል፡፡ የተቃዋሚ ፓርቲ አመራሮች ስለ ግንቦት 20 ፍሬዎች የራሳቸውን እይታ ገልተውባታል፡፡ የመኢአድ ፕሬዝደንት አቶ አበባው መሃሪ፣ የሰማያዊ ፓርቲ ም/ሊቀመንበር አቶ ስለሽ ፈይሳ፣ የአረና የህዝብ ግንኙነት አቶ አብርሃ ደስታ፣ እንዲሁም የአንድነት ለፍትህና ለዴሞክራሲ የፖለቲካ ጉዳይ ኃላፊ ሰሎሞን ስዩም ስለ ግንቦት 20 ይናገሩባታል፡፡ አቶ ታዴዎስ ታንቱ የግንቦት 20ን እንክርዳድ ለመመንገል ስለሚያስችለው ስልት ጽፈውባታል፡፡ ሰንደቅ አላማውና ግንቦት 20፣ ግንቦትና ግንቦታውያን፣ ግንቦት 20 የበላቸው ቀሽ ገብሩዎች፣ ግንቦት … [Read more...] about የግንቦት 20 “ፍሬዎች”
ኢትዮጵያን ያለብሔሮች የሚፈልጓት ያፈርሷታል!
Nation: large aggregate of people united by common descent, culture, or language, inhabiting a particular territory. Tribe: A social division in a traditional society consisting of linked families or communities with a common dialect. Clan: a group of close knit and interrelated families/offspring. በኢትዮጵያ እስከ አሁን ከገዙዋት ገዥዎቹዋ አንድም ገዢ ወይንም የፖለቲካ ስርዓት ለኢትዮጵያ ብሔሮች ኖረው እንደማያውቅ የኢትዮጵያ ፖለቲካ ታሪክ ግልጽ አድርገው ያሳያል፡፡ የኢትዮጵያ ነገሥታት ኖረው ያለፉት አንድም ለመንግስታቸው ያለገደብ ገዢ ሆኖ መኖር ስሰሩ በሌላ በኩል በዙሪያቸው ለኮለኮሏቸው መሳፍንቶችና … [Read more...] about ኢትዮጵያን ያለብሔሮች የሚፈልጓት ያፈርሷታል!
እኚህ ሰው ማናቸው? – ፩
ከአዘጋጆቹ፤ የዘወትር የጋዜጣችን ተሳታፊና የጎልጉል ወዳጅ ወለላዬ “እኚህ ሰው ማናቸው?” በሚል ርዕስ በየሳምንቱ የታዋቂ ሰዎችን ፎቶ ከግጥም ጋር በመላክ ጥያቄ ለማቅረብና አንባቢያንን ለማሳተፍ ውሳኔ አድርገዋል፡፡ ለዚህ ከግጥምና ፎቶ ጋር ለሚቀርብ ዝግጅት አንባቢያን ጥያቄውን በግጥም በመመለስ እንዲሳተፉ እንፈልጋን፡፡ በሳምንቱ ቀጣዩን “እኚህ ሰው ማናቸው?” ስናትም መልሱን አብረን እናወጣለን፡፡ በዚህ መልክ ውይይቱ እንዲቀጥል ለማድረግ ያቀድን ሲሆን አንባቢያንም የእውቅ ሰዎች ፎቶዎችና ማንነታቸውን ብትልኩልን ለማስተናገድ የምንችል መሆናችንን እንገልጻለን፡፡ በተለይ የታዋቂ ሰዎች የልጅነት ፎቶዎች ቢሆን የበለጠ አስተማሪ ይሆናል ብለን እናስባለን፡፡ ለዛሬው የእኚህን ታዋቂ ሰው ፎቶ ከግጥም ጋር አቅርበናል፡፡ ምላሹን ከእናንተ እንጠብቃለን፡፡ ይህንን የዝግጅት ሃሳብ ላቀረቡትና … [Read more...] about እኚህ ሰው ማናቸው? – ፩