• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የኢትዮጵያ ህዝብ ይወቅልኝ!

May 28, 2014 12:16 am by Editor 3 Comments

እኔ ወ/ሮ እታገኝ መኮንን ካሣ አድራሻ፡- አዲስ አበባ የካ ክ/ከተማ ወረዳ 09 የቤት ቁጥር 760/ሀ ነዋሪ ነኝ፡፡ በአሁኑ የካ ክ/ከተማ ወረዳ 09 ከላይ ቁጥሩ በተገለፀበት ቤት ከ40 ዓመት በላይ ተከ ራይቼ ስኖር በ1990 ዓ.ም በኤች አይ ቪ ኤድስ ቫይረስ መያዜን አወኩ፡፡

ቤቴንም ሆነ ልጆቼን እን ዲጠብቅልኝና እንዲረዳኝ በማለት ከ1994-1997ዓ.ም ድረስ በውክልና ሰጥቸው የነበረ ሲሆን ከ97 በኋላ ግን ውክልናውን ትቶ የራሱን ቤት ሰርቶ ሄዷል፡፡ ቤቱ እስከታሸገበት ጥር 12 ቀን 2003 ዓ.ም ድረስ ለአቶ ደረጄ ጎዳና ከመንግስት ተከራይ በማስመሰል በቤት ቁጥር 760/ሐ በአቶ ደረጄ ስም የአንድ አመት (በ1998 ዓ.ም) የቤት ኪራይ በስማቸው ቀበሌ ሂዶ ከፍሏል በማለት እኔ ደካማና በሽተኛዋን የፍርድ ቤት ውሳኔ ነው በማለት ቤቴን ጥር 12 ቀን 2006 ዓ.ም ጀምሮ በመ ድኃኒቴ እና በንብረቴ ላይ በማሸግ በእኔም ሆነ ቤተሰቦቼን ከፍተኛ ችግር ደርሶብናል፡፡

ሆኖም መጋቢት 24 ቀን 2006 ዓ.ም እኛን በፖሊስና በመሣሪያ ኃይል ከግቢ ውስጥ አስወጥተው ንብረቴን በሌለሁበት አውጥተውብኝ እኔ ስምንት ቤተሰቤን ይዤ ዕቃ ቤት እንድኖርና ግማሹ ንብረቴን ውጭ ተጥሎ ለዝናብምና ለፀኃይ እንዲጋለጥ በማድረግ ከፍተኛ ውድመት እንዲደርስብኝ አድርገዋል፡፡

በየደረጃው ላሉት የመንግስት አካላት በተደጋጋሚ አቤት ብልም ቤቱን ለፈለጉት ሠው ለመስጠት ሲሉ ያላደረኩትን አድራጎት እያቀረቡ ጥፋተኛ ነሽ በማለት ለረዥም ወራት እያንከራተቱኝ መሄጃው ጠፍቶብኝ እገኛለሁ፡፡

ሁከት ስለፈጠሩብኝ ይወግድልኝ ጥያቄ ለፍርድ ቤት ባቀርብም የወረዳ 09 ቤቶች ልማት ፅህፈት ቤት የሀሰት ማስረጃ እያቀረቡ ሁከት አልፈጠረም በማለት ውሳኔ ተሰጠብኝ፡፡ በበኩሌ በ2005ዓ.ም ይግባኝ ብልም ወረዳውን መጥራት ሳያስፈልገኝ የተሠጠው ውሳኔ ትክክል መሆኑን አረጋግጭአለሁ፤ መልስ ሰጪውን መጥራት አያስፈልግምብሎ መዝገቡን ዘግቶብኛል፡፡

እንዲሁም ሠው ሁልጊዜ ከማስችገር በማለት ትንሽዬ የሸራ መጠለያ አድርጌ ከሰል ቸርችሬ የማድርባትን መጠለያ የደረጄ ነው በማለት ግቢው ውስጥ ሁለት ክፍል አድርገው ቀምተው ሰኔ 16/2004 ዓ.ም ለአስቴር መለስና ለጌታቸው መለስ የልማት ተነሺ ናቸው በማለት ሰጥተውብኛል፡፡ አሁን ደግሞ የምኖርበትን ከመንግስት በየአመቱ የምዋዋልበትን ቤት ለኃይልና ለውኃ ልማት በፃፉት ደብዳቤ ቤቴ መሆኑን በማመልከቻ ላይ ገልጸውልኛል፡፡

እኔ እታገኝ መኮንን በየካ ክ/ከተማ በወረዳ 09 መንግስት ቤት ቁጥር 760ነዋሪ መሆኔን በ26 ዝውውር 2006 እስከ ዛሬ እኖርበት የነበረውን መኖሪያ ቤት ለልማት ተነሺዎች የተሰጠ መሆኑን በደብዳቤያቸው አረጋግጠዋል፡፡

እኔ የ63 አመት አዛውንት የሙት ልጆች ይዤ ብርድና ፀሀይ እየተፈራረቀብኝ እገኛለሁ፡፡ ስለሆነም የኢትዮጵያ ህዝብ ይፍረደኝ እላለሁ! (ምንጭ: – ነገረ ኢትዮጵያ)

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Social Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Comments

  1. mahi says

    May 29, 2014 11:16 am at 11:16 am

    berasachewu bet ema edi mederegi yelebetm 🙂 meseteti alebachewu betachewu 🙂 hgi yelem ede 🙂 qoyi ede

    Reply
  2. በለው ! says

    May 29, 2014 03:50 pm at 3:50 pm

    “በዚሁ የየካ ክፍለ ከተማ ቀበሌ ፰ ውስጥ ሁለት ተያያዥ ቤቶች አሉ። ሁለቱ ተከራዮች ቢያንስ ቤቱን ከመንግስት ተከራይተው የኖሩበት ከ፶ዓመት በላይ ነው። አንደኛዋ ተከራይ ፫ የደረሱ ልማታዊ ልጆችና አንድ በራሱ የተመካ መሀንዲስ አማች አላቸው። ሁለተኛዋ ተከራይ ፮ ልጆች ሲኖራቸው ፫ከዚህ ዓለም አልፈዋል።የሁለቱም ቀደምት ኖሮ ዝቅተኛና ተመሳሳይ ነበር። ሁለቱም ተከራዮች የመግቢያ ጠፈጠፍ ሲያስቸግራቸው በአንድ ቆርቆሮ ዕርዝምት በረንዳ ዘርግተው ለመሸፈን ሲፈልጉ ልጆችና አማች ያላቸው ፍቀድ አጝኝተው መሠረቱ በኒሚንቶ ቋሚው በብረት አራት ቆርቆሮ ድርድረው ሠርተዋል። ሁለተኛዋ ተከራይ ግን ቆርቆሮውን አቁመው በረንዳውን በእንጨት ቀስት እነጂ በብረት ለመሥራት አልተፈቀደላቸውም።(ዳግማዊ ደርግ!)…. በዚያን ዘመን ሁለት ቀበሌ ተመራጮች ለ፲፯ዓመት የቤት ኪራይ ሳይክፍሉ በመጣው ምርጫ ሁሉ የማሟያ ምርጫ እየተባለ ሲጠቀሙ ኖረዋል ዛሬ በኢህአዴግ የኪራይ ቤታቸውን ባላቤት ሆነው ሸጠው በጥሩ አሸናኘት ተደርጎላቸው መላ ቤተሰባቸውን ይዘው በአሜሪካ ይኖራሉ። ይህ ነበር የኖርንበት እሳቸውም ሚኖሩበት አለም!!

    **በውጭ ሀገር ተቀምጣችሁም እያማሰላችሁም ያሳረራችሁን..ሀገራችሁ ገብታችሁ ፵/፷ የምታበስሉ…ፖለቲካ በድረ ገፅ የምትቀቅሉም ይሁን..በፓልቶክ የምትቆሉ…ይህ የተዘበራረቀ በቀለም ያበደ ባንዲራ ይዛችሁ የሰው ሀገር የምትቀውጡም…የፀሐዩ መንግስት እያላችሁ እንጀራና ቅመማቅመም ከሕዝብ ጉሮሮ ነጥቃችሁ በመሸጥ የከበራችሁ…ኢትዮጵያውያን የራሳቸውን ባህልና ሃይማኖት ቋንቋ መልካም ሥነምግባርን ጥለው የባዕድ ይዘው ገደል እንዲገቡ ጥረት የምታደርጉ እራስ-ወዳዶችም ብትሆኑ…ለግል ጥቅም አድርባይነት..አውርቶ-አደርና ሠርቆ-አደር መሆን ዘለዓለማዊ ለሚመስላችሁ…በቀን አስር ግዜ እየበላችሁ ለወገኖቻችሁና ለፆም-አዳሪው ወጣት ትውልድ የማቀጣጠያውና መቃጠያው ነዳጅ የምታቀብሉ ዲያስፐርስ…ዘረኝነትን ሙስናን ጎጠኝነትን ዘርታችሁ የድሃ ልጅ በጥይት ለምታስቀጥፉ ሁሉ…የምታመጡት ለውጥ ከነበረው የተሻለ እንጂ ጭራሽ በመከፋፈልና በጎሪጥ በመተያየት ጥቅማጥቅመኞት(ለልማት ተነሳሺ!) ካድሬ… ታማኝ ምሁራን…አክቲቪስት አርቲስት ኢንቨስትር…ተብለው ሥርዓቱን እንዳለ ያለ ‘ተፎካካሪ ተወዳዳሪ አማራጭ’ ፓርቲና የነፃ ሚዲያ እራሱ አውርቶ.. እራሱን አድንቆና አጨብጭቦ እንዲቀጥል ለሚያደርጉ ምቹ ሁኔታን መፍጠራችሁ እነደሆነ ልትገነዘቡ ይገባል። ዝምታም ትብብር ነው!።ከበላተኛውም ጎን ሆኖ በሌላ አጀንዳ ንጹሕ ሕዝብን ማተራመስም ሥርዓቱን መተባባር ነው!።

    **አቶ መለስ ” እኛ ለሽማግሌውና ለአዛውንቱ ግድ የለንም እኛ የምንፈልገው አዲሱ ትውልድ እንዲከተለን ብቻ ነው” ብለው ነበር…አዎን! በዚህ ዘመን በአራቱም አቅጣጫ(ማዕዘን) የሚሰራው ይህ ነው። ትምህርት ቤቶች የኢትዮጵያ ታሪክ የላቸውም የሚያስተምሩት ብሄርና የግለሰቦችን ራዕይ ነው.. ሽማግሌና አሮጊት የድሮ ሥራዓት ናፋቂ ይባላሉ ግን ያለ እነኝህ ዜጎች አስተዋጽዎ ኢትዮጵያ አትኖርም ነበር።፡አዲሱ ትውልድ እነደፈለጉት የሚነዱት የቁም ከብት ሆኖ ተከልሎና ተከልክሎ ጸጥ ብሎ ይገዛል!! ዕለታዊ ጉርሱን በቀን አበልም ይሁን ጥቅማጥቅም ካገኘ እናቱን ለገንዘብ ያስማማል… እናት በሎ ሀገር አደለምን!?ቻይና ሕንድ ዓረብ ቱርክ ሲከራየውና ሲገዛው መች እንቢኝ አለ!? ዙሪያውን ይጨፍር የለምን! ታዲያ እርስ በእርሱ ሲሆን ሜንጫ ስሎ! ሽመል ቆርጦ እሳት ጎርሶ.. እሳት ልሶ አቃጥሎ በጥይት ይቃጠል ለምን!? አልቅስ ያለው ዓይን ጭስን አጥብቆ ጠየቀ!

    ***አቶ ኀይለመለስ “ኢትዮጵያዊነት ደምቋል አሉ” በሸውራራ ዓይን መነፅር ተደርጎ ተጥበርብሮባቸው ካልሆነ ወይንም ይህ ዙሪያውን የሚጠዛጠዘው ሕዝብ ኢትዮጵያዊ አደለም ካላሉ ወይንም እራሳቸው እንዲበጣበጥ ከላዘዙና በእጅ አዙር እንቨስት ካላደረጉ በቀር የደመቀች ኢትዮጵያ የት ነሽ? ወይ ተበድሮና ለምኖ መድመቅ!? ፻፷፮ ኪሎ ሜትር ወልቂጤ ከተማ እሳት አዳጋ መኪና የሌላት የ፷፭ዓመት አዛውንት ፰ቤተሰብ ይዘው ቤታቸው ተነጥቆ ዜግነታቸው ተረግጦ ይህ ዕድገት…ሠርቶ በማፍረስ የት ይደርሳል! እነኛ በበረሃ የአሞራ እራት ሆነው የቀሩ ታጋዮች ጭቆናን አስወግደው ብላ ተባላን መርሆአችን፣ አንድነታችን እፍረታችን!ብሔር!፩ ብሔረሰብና፪ ሕዝቦች ፫ (የአፓርታይድ ከተማ) መስርተው ልዩነታችን ውበታችን! ብለውን ለመናገር.. ለመንቀሳቀስ.. ለመሰብሰብ..ለመዘዋወር..ለመሰለፍና ሞተንም ለመቀበር አሳውቀን አስፈቅድንና ለምነን በፍርሃት እንድንሸበብ አድርገው ከልለውና አስከልክለው ለእራሳቸው ለቤተሰባቸው ለወገኖቻቸው ለእኛና ለኢትዮጵያ ሳይሆኑ ገድለውን ለምን አረፉ!!!?ሠላም ለሁሉም በቸር ይግጠመን!

    Reply
  3. abikiya says

    May 29, 2014 11:57 pm at 11:57 pm

    Not fair

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ከፍተኛ የፋኖ አመራሮች መገደላቸው ተነገረ May 6, 2025 10:40 pm
  • ሃይማኖትን ለተራ የፖለቲካ ሸቀጥ ማዋል ውርደት ነው April 24, 2025 12:43 am
  •  የኬሪያ ኢብራሒም ኑዛዜ “ብትንትናችን ወጥቷል” April 22, 2025 12:08 am
  • ለወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን አመራሮች ወታደራዊ ሥልጠና ተሰጠ April 16, 2025 11:44 pm
  • ዓቅም እንደሌለው የገመገመው ሻዕቢያ ፊቱን ከጦርነት ወደ ዲፕሎማሲ እያዞረ ነው   April 15, 2025 12:32 am
  • “አንድ የፋኖ ተቋም (የእስክንድር) ተመሥርቷል፤ ሌሎቹ ደግሞ እንዲሁ አንድ ተቋም መሥርተው ወደዚህ ይመጡ” አበበ ጢሞ April 11, 2025 12:07 am
  • መለስ (ለገሰ) ዜናዊ – ተዋርዶ ያዋረደን! April 9, 2025 10:28 pm
  • የተከዜ ዘብ: የሉዓላዊነት መጠበቂያ April 8, 2025 11:49 pm
  • አዲስ አበባ አስተዳደር የሪፖርተርን የተዛባ መረጃ ኮነነ፤ ሕጋዊ እርምጃ እወስዳለሁ አለ April 8, 2025 10:06 pm
  • ሀሰተኛውን የሪፖርተር ዘገባ ንግድ ባንክ በጽኑ ተቃወመ፤ እርማትም ጠየቀ April 8, 2025 09:48 pm
  • “ኦሮሚያ ላይ ወይም ሌላ ቦታ ላይ ስታደርገው ከነበረ ትግራይ ወስጥም የማታደርግበት ምንም ምክንያት አይኖርህም” ነው ጌታቸው ረዳ April 7, 2025 10:22 pm
  • “TPLF’s belief in a strong federal government was always tied to its own dominance in Addis Ababa” April 7, 2025 10:15 pm
  • Counter-Video by EBC Challenges EBS Broadcast, Sparks Public Outcry Over Alleged Misinformation March 31, 2025 02:36 am
  • የኤሊያስ መሠረትን ፌክ መረጃ ማን ያጋልጥ? February 19, 2025 06:00 pm
  • አዘርባጃን፡ የሻዕቢያን ሸምቀቆ ማጥበቂያ?! February 19, 2025 12:29 am
  • የአሜሪካ ድምፅ/ቪኦኤ ይዘጋ ተባለ  February 12, 2025 03:37 am
  • የብልፅግና ፓርቲ ሹመኛ ካድሬዎች February 3, 2025 11:07 am
  • ትግሉን የጎዳው የእስክንድር ነጋ አካሄድ February 3, 2025 10:29 am
  • ኤሊያስ መሠረት “ጭምብሉ ዛሬ ወለቀ”፤ ተከፋይ ነው! February 2, 2025 05:32 pm
  • የፋሲል ግንብ እድሳት እንዴት ተካሄደ? የመንጣቱ ምክንያት? January 23, 2025 03:41 pm
  • ታሪካዊዉ የፋሲል ቤተመንግሥት ለምን ነጣ? January 23, 2025 03:04 pm
  • የኢትዮጵያ አየር መንገድ በተወልደ አስተዳደር ዘመን ለተሠራ ስህተት 425ሺ ዶላር ተቀጣ December 14, 2024 01:44 am
  • በትግራይ ከሞትና ከአካላዊ ጉዳት የተረፉት ለስደት ተዳርገዋል November 27, 2024 12:09 pm
  • የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት አሠራሩን እንዲያርም ጥብቅ መመሪያ ተሰጠው November 27, 2024 11:31 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule