• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ጠረኑ የሚከረፋው የግንቦት ሃያ 23ኛ ዓመት “ዓመድ”

May 28, 2014 07:35 am by Editor Leave a Comment

ሚስት ከቤቷ ጥጋ ጥግ ትንንሽ ጊዜያዊ ጉልቻ ጎልታ ካንዱ ወዳንዱ እየተዛወረች ስራዋን ስትሰራ፣ ስትቀቅል፣ ስታነኩር፣ ስትጋግር፣ ስትወጠውጥ … ድንገት ባንዱ አቅጣጫ እሳቱ መልኩን ቀየረ። ቀስ ብሎ ለካስ ወደ ቤቱ ተዛምቶ ነበርና ቤቱ ነደደ። እሳቱን ያዩ ለማጥፋት እየተሯሯጡ ደረሱ። አልሆነም የቤተሰቡ መኖሪያ ነደደ። ቤቱ የቆመው ለመቀጣጠል በሚያመች ማዋቀሪያ ነበርና ወደ አመድ ተቀየረ። ልክ እንደ ጎሳ ፖለቲካ!! እንደ ግንቦት 20 ዓመዳማ ፍሬዎች!!

እሳቱን ለማጥፋት የሞክሩት ጎረቤቶች አዘኑ። “እሳት በቀላሉ የሚበላው ቤት ይዘሽ ዙሪያውን እሳት ማቀጣጠል አልነበረብሽም” ብለው ገሰጿት። ማጣፊያው ያጠራት ሴት “እባካችሁ ባለቤቴ ሲመጣ አትንገሩት” አለቻቸውና ተማጸነች። ጎረቤቶቿ በንግግሯ ተገርመው “ከሄደበት ሲመጣ የሚገባበት ካገኘ ማን ይነግረዋል” ብለዋት ተሰናበቷት። “ቤት ባገር ይመሰላል” እያለ የሚያስተምረኝ የመሰየሚያ ቤት ባልደረባዬ ታወሰኝ፡፡

የተለመደው ሰላምታዬን በቅድሚያ ኑሮ ለሚያላምጣችሁ … ለኑሮ ችጋር ሰለባዎች ይሁን!! ክረምት/ቡሄ መጣ። ክረምት ስጋት የሆነባችሁ ኗሪዎች “አንድዬ ይከልላችሁ” ከማለት የዘለለ ምርቃት የለኝም። ዶፉን፣ ውርጩን፣ ቁሩን …. በደጅ ሁናችሁ የምትገፉት የ”ኗሪዎች” “አኗኗሪዎች”፣ በወጉም አኗኗሪ መሆን እንኳን ያቃታችሁ፣ ለናንተም ምርጫ ደርሷል። አሁን እናንተን ምን ብለው ይሆን “ምረጡኝ” ብለው የሚጀነጅኗችሁ? ለነገሩ እኮ ዝናብ ሲመጣ የሚያነቡ ቤት ውስጥ ያሉ የውጪ/ደጅ አዳሪዎች ከናንተ ይበዛሉ። በፈረቃ የሚተኙትስ ከናንተ በምን ይሻላሉ? አረ ስንቱ … ቀኝኑ ዘ-ቄራ ነኝ!! ቋሚን አሳንሰው ለሙት መንፈስ በሚገብሩና በሚሰግዱ መመራትም ያው የደጅ ኑሮ ማለት ነው። ያለ ህግ መገዛትም ያው የዱር ኑሮ ነው !! ሲያስጠላ!!

ነብስ ይማር፣ ነብስ ያሽርልን!! ደጅ መውደቅ መከራ ሆነ። ደጅ በወደቁት ላይ ሌሎች ደጅ አዳሪዎች ማከል እንዲቆም የጠየቁ – “ታጨዱ” ። ለሰላማዊ ጥያቄ ያለ ጥይት መፍትሄ የለም ወይ? ያለ ጠብ መብ መንጃ አማራጭ የለም እንዴ? ሰዎች በተሰበሰቡ ቁጥር መደንበር ለምን? ያ ግብር የሚገባበት “የባቢሎን ሽራፊ” በደም ተነከረው የሲኦል ካባው አልቆበት ይሆን? ግራ የሚያጋባ ነው እኮ!! ቀጭኑ ተጨነቀ!!

የኢትዮጵያ ወቅታዊ አቋቋም እዛም እዛም እሳት የለኮሰችውን ሴት ይመስላል። ኦሮሚያ የእሳት ነበልባል አለ። አማራ ክልል እሳት ከረመጠ ውሎ አድሯል። ደቡብ ያለው እሳትም ልንደድ አልንደድ እያለ ነው። ሶማሌ ክልል ያለው እሳት ሃፎቱን እየሰበቀ ነው። አፋር ክልል በራሁ ጠፋሁ የሚል እሳት አለ። ጋምቤላ ከራሷ እሳት ሌላ ከአጎራባቿ የሚነደው እሳት እያጋላት ነው። ሁሉም ጋር እሳት አለ። እሳቱ ከያቅጣጫው ቤንዚን እየተርከፈከፈበት ነው። ኢህአዴግም በየቀኑ እሳቱን እየቆሰቆሰ 23 ዓመታትን “ደም ግብሩ” አድርጎ ልደቱን ለማክበር እየተክለፈለፈ ነው።

ላለፉት 23 ዓመታት የጎሳ ፖለቲካና ጥላቻ እየተጋቱ ያደጉ ትውልዶች ዙሪያውን እየፎከሩ ነው። የኢትዮጵያዊነት ልጓማቸውን ኢህአዴግ በጣጥሶ ስለጣለው ፉከራው ገደብ እንዳይለቅ ያስፈራል። ቀጭኑ ከየአቅጣጫው በሚሰማው በርግጓል። ለነገሩ ያልበረገገ ማን አለ? የገደሉ፣ ያስገደሉ፣ እየገደሉ ያሉ፣ ወደ ፊትም ለመግደል ቃታ ላይ የተጣዱ፣ ከሁሉም በላይ “እርሙና ግፉ በስማቸው የሚፈጸምባቸው” ተጨንቀዋል። ወደ ልቡና ወደ ቀልቡ የሚመለስ አልተገኘም። 23 ዓመታት ለትምህርት አልሆነም። አገሪቱ በጥላቻና በቂም እየነፈረች የሚያዝን መሪ ድምጽ አልተሰማም።

የሃይማኖት መሪዎችም በባቢሎን ቅሪት ተለውሰው፣ በካድሬነት ካባ ተሸፍነው “እረኝነታቸውን” ረስተውታል። “ደ-መና ሲሆን ዝናብ እንደሚመጣ” መለየት አልቻሉም። ታውረዋል። ልቡናቸው ደንድኖ የሎጥን ሚስት ሆነዋል። ደጉ መንፈስ ስለራቃቸው እይታቸው ከከርሳቸው ማለፍ አልቻለም። አማኑኤል ያለው “እብድ” ትዝ አለኝ። “የሚፈራ፣ የሚከበር ጠፋ፣ ማንን ፊት እናስቀድም? ማን ነው ቀልብ ያለው? መቅደስ ውስጥ ማን አለ? ክፋት፣ ክፋት፣ ክፋት….” እያለ ይጮህ ነበር። እንዲህ ስላለ ታስሯል። ተጠፍሯል። ቀናነት መጥፋቱ ያስጨነቀውን “ቀና” ሰው፣ ቀናነት የጎደላቸው አስረው ላርጋክቲን ይወጉታል። ግን ማን ነው በሽተኛ? ቀጭኑ ጠየቀ!!

አማኑኤል የጤነኞች መከማቻ ነው። አማኑኤል በቤት ጣጣ፣ በሃቴቴና በውቃቢ፣ በጋኔን “ግብር አነሰኝ” ቁጣ ከሚመጡት በስተቀር አብዛኞቹ የተነኩበት ጉዳይ ያሳዝናል። ካንዳበታቸው የሚወረወረው ሁሉ እውነት ነው። “አገሬ አይ እድልሽ” እያሉ የሚለፈልፉ፣ “አትግደል፣ አትግደል፣ አትግደል … “ እያሉ የሚወተውቱ፣ “ልብ ያለው ልብ ይበል፣ ልብ ያለው ያስተውል፣ አዳምጡን፣ ስሙኝ፣ ጆሯችሁን አቁሙ” እያሉ የሚያስጠነቅቁ ውብ ሰዎች አማኑኤል “እብድ” ተብለው አሉ። የሚገርመው ጡረተኛዋ ቀዳማዊት እመቤት ናቸው “የበላይ ጠባቂያቸው” አይ አለም!!

አንድ ጊዜ አንድ የአማኑኤል ሰራተኛ የነገሩኝ ታወሰኝ። አማኑኤል ሆስፒታል ያሉ ታካሚ እህቶች “ውርጃ ይከናወንላቸዋል” አለኝ። የሰማሁትን ማመን አቃተኝ። እንዴት እንደሆነ ለማወቅ ማብራሪያ አቀረብኩ። ሰራተኞች እንደሚተናኮሱዋቸው/እንደሚገለገሉባቸው ተረዳሁ። አፈርኩ። አመመኝ። አሁን ማን ነው ጤነኛ? የሚገርመው ውርጃ የሚፈጽምላቸው የግል ተቋም እንዳለ መሰማቱ ነው። ጉዳዩን ብዙም ማጣራት ባልችልም “እብዶች” ስለማርገዛቸው ከበቂ በላይ ማስረጃ አለ። ወ/ሮ አዜብ እንደ አሁኑ ሳይተነፍሱ ይህንን እንኳን ለፍርድ ቢያቀርቡ ምንኛ ከኖረው ሃጢያታቸው ሁሉ በነጹ ነበር!! መስመር ሳትኩ መሰል ወደ መነሻዬ ልመለስ።

አዎ ቤት አገር ነች። ቤት ከተቃጠለ መጠለያ የለም። በተለይ በግራም በቀኝም መሸሻ የሌላቸው ምስኪኖች ያሳዝናሉ። “አለን አለን ሲሉ፣ ይናዳል ገደሉ” ተብሎ የለ!! ከተናደ ተናደ ነው። ደርግ ሲናድ ጥላ ሳይቀር ያስደነግጥ ነበር። ሲናድ ጥላም ያስፈራል። ሲናድ ስንቄን፣ ሃብቴን፣ ወርቄን፣ ፋብሪካዬን፣ ህንጻዬን፣ መኪናዬን፣ ቤተመንግስቴን…. የሚባል ዘባተሎ ሃሳብ የለም። ሁሉም እንደ ጉም ይተናል። እንደ ሴትየዋ ቤት “ዓመድ” ይሆናል። ዓመድ!! ታዲያ ያ-ክፉ ሃሳብ ሳይሰለጥን ሁላችንም ወደ ልባችን ብንመለስስ? ስለ ሰላም ብናለቅስ? ይቅር ባይነት “ዓመድ” ከመሆን ይሰውራልና !! ከግንቦት ሃያ ያተረፍነው የጎሳ ፖለቲካ ምሱ ዓመድ ነውና 23ኛውን “በዓል” የግንቦት 20 ዓመዳማ ፍሬዎች!! ብንለውስ? ክብር ይህንን ጊዜና የተሰውበትን ዓላማ ሳይመለከቱ ላለፉ ታጋዮች!! ግን ይህንን በደማቸውና ባጥንታቸው ላይ የተገነባውን “ዓመድ” የሚያደርግ የፖለቲካ ቀመር ከሚያዩት ሞታቸው አይሻልም? ፍሬዎቹን ኢህአዴግ በሰፊው ስለሚመጣባቸው አልፌያቸዋለሁና። ለማመጣጠን ኢቲቪን ይመልከቱ!!

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule