• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ጠረኑ የሚከረፋው የግንቦት ሃያ 23ኛ ዓመት “ዓመድ”

May 28, 2014 07:35 am by Editor Leave a Comment

ሚስት ከቤቷ ጥጋ ጥግ ትንንሽ ጊዜያዊ ጉልቻ ጎልታ ካንዱ ወዳንዱ እየተዛወረች ስራዋን ስትሰራ፣ ስትቀቅል፣ ስታነኩር፣ ስትጋግር፣ ስትወጠውጥ … ድንገት ባንዱ አቅጣጫ እሳቱ መልኩን ቀየረ። ቀስ ብሎ ለካስ ወደ ቤቱ ተዛምቶ ነበርና ቤቱ ነደደ። እሳቱን ያዩ ለማጥፋት እየተሯሯጡ ደረሱ። አልሆነም የቤተሰቡ መኖሪያ ነደደ። ቤቱ የቆመው ለመቀጣጠል በሚያመች ማዋቀሪያ ነበርና ወደ አመድ ተቀየረ። ልክ እንደ ጎሳ ፖለቲካ!! እንደ ግንቦት 20 ዓመዳማ ፍሬዎች!!

እሳቱን ለማጥፋት የሞክሩት ጎረቤቶች አዘኑ። “እሳት በቀላሉ የሚበላው ቤት ይዘሽ ዙሪያውን እሳት ማቀጣጠል አልነበረብሽም” ብለው ገሰጿት። ማጣፊያው ያጠራት ሴት “እባካችሁ ባለቤቴ ሲመጣ አትንገሩት” አለቻቸውና ተማጸነች። ጎረቤቶቿ በንግግሯ ተገርመው “ከሄደበት ሲመጣ የሚገባበት ካገኘ ማን ይነግረዋል” ብለዋት ተሰናበቷት። “ቤት ባገር ይመሰላል” እያለ የሚያስተምረኝ የመሰየሚያ ቤት ባልደረባዬ ታወሰኝ፡፡

የተለመደው ሰላምታዬን በቅድሚያ ኑሮ ለሚያላምጣችሁ … ለኑሮ ችጋር ሰለባዎች ይሁን!! ክረምት/ቡሄ መጣ። ክረምት ስጋት የሆነባችሁ ኗሪዎች “አንድዬ ይከልላችሁ” ከማለት የዘለለ ምርቃት የለኝም። ዶፉን፣ ውርጩን፣ ቁሩን …. በደጅ ሁናችሁ የምትገፉት የ”ኗሪዎች” “አኗኗሪዎች”፣ በወጉም አኗኗሪ መሆን እንኳን ያቃታችሁ፣ ለናንተም ምርጫ ደርሷል። አሁን እናንተን ምን ብለው ይሆን “ምረጡኝ” ብለው የሚጀነጅኗችሁ? ለነገሩ እኮ ዝናብ ሲመጣ የሚያነቡ ቤት ውስጥ ያሉ የውጪ/ደጅ አዳሪዎች ከናንተ ይበዛሉ። በፈረቃ የሚተኙትስ ከናንተ በምን ይሻላሉ? አረ ስንቱ … ቀኝኑ ዘ-ቄራ ነኝ!! ቋሚን አሳንሰው ለሙት መንፈስ በሚገብሩና በሚሰግዱ መመራትም ያው የደጅ ኑሮ ማለት ነው። ያለ ህግ መገዛትም ያው የዱር ኑሮ ነው !! ሲያስጠላ!!

ነብስ ይማር፣ ነብስ ያሽርልን!! ደጅ መውደቅ መከራ ሆነ። ደጅ በወደቁት ላይ ሌሎች ደጅ አዳሪዎች ማከል እንዲቆም የጠየቁ – “ታጨዱ” ። ለሰላማዊ ጥያቄ ያለ ጥይት መፍትሄ የለም ወይ? ያለ ጠብ መብ መንጃ አማራጭ የለም እንዴ? ሰዎች በተሰበሰቡ ቁጥር መደንበር ለምን? ያ ግብር የሚገባበት “የባቢሎን ሽራፊ” በደም ተነከረው የሲኦል ካባው አልቆበት ይሆን? ግራ የሚያጋባ ነው እኮ!! ቀጭኑ ተጨነቀ!!

የኢትዮጵያ ወቅታዊ አቋቋም እዛም እዛም እሳት የለኮሰችውን ሴት ይመስላል። ኦሮሚያ የእሳት ነበልባል አለ። አማራ ክልል እሳት ከረመጠ ውሎ አድሯል። ደቡብ ያለው እሳትም ልንደድ አልንደድ እያለ ነው። ሶማሌ ክልል ያለው እሳት ሃፎቱን እየሰበቀ ነው። አፋር ክልል በራሁ ጠፋሁ የሚል እሳት አለ። ጋምቤላ ከራሷ እሳት ሌላ ከአጎራባቿ የሚነደው እሳት እያጋላት ነው። ሁሉም ጋር እሳት አለ። እሳቱ ከያቅጣጫው ቤንዚን እየተርከፈከፈበት ነው። ኢህአዴግም በየቀኑ እሳቱን እየቆሰቆሰ 23 ዓመታትን “ደም ግብሩ” አድርጎ ልደቱን ለማክበር እየተክለፈለፈ ነው።

ላለፉት 23 ዓመታት የጎሳ ፖለቲካና ጥላቻ እየተጋቱ ያደጉ ትውልዶች ዙሪያውን እየፎከሩ ነው። የኢትዮጵያዊነት ልጓማቸውን ኢህአዴግ በጣጥሶ ስለጣለው ፉከራው ገደብ እንዳይለቅ ያስፈራል። ቀጭኑ ከየአቅጣጫው በሚሰማው በርግጓል። ለነገሩ ያልበረገገ ማን አለ? የገደሉ፣ ያስገደሉ፣ እየገደሉ ያሉ፣ ወደ ፊትም ለመግደል ቃታ ላይ የተጣዱ፣ ከሁሉም በላይ “እርሙና ግፉ በስማቸው የሚፈጸምባቸው” ተጨንቀዋል። ወደ ልቡና ወደ ቀልቡ የሚመለስ አልተገኘም። 23 ዓመታት ለትምህርት አልሆነም። አገሪቱ በጥላቻና በቂም እየነፈረች የሚያዝን መሪ ድምጽ አልተሰማም።

የሃይማኖት መሪዎችም በባቢሎን ቅሪት ተለውሰው፣ በካድሬነት ካባ ተሸፍነው “እረኝነታቸውን” ረስተውታል። “ደ-መና ሲሆን ዝናብ እንደሚመጣ” መለየት አልቻሉም። ታውረዋል። ልቡናቸው ደንድኖ የሎጥን ሚስት ሆነዋል። ደጉ መንፈስ ስለራቃቸው እይታቸው ከከርሳቸው ማለፍ አልቻለም። አማኑኤል ያለው “እብድ” ትዝ አለኝ። “የሚፈራ፣ የሚከበር ጠፋ፣ ማንን ፊት እናስቀድም? ማን ነው ቀልብ ያለው? መቅደስ ውስጥ ማን አለ? ክፋት፣ ክፋት፣ ክፋት….” እያለ ይጮህ ነበር። እንዲህ ስላለ ታስሯል። ተጠፍሯል። ቀናነት መጥፋቱ ያስጨነቀውን “ቀና” ሰው፣ ቀናነት የጎደላቸው አስረው ላርጋክቲን ይወጉታል። ግን ማን ነው በሽተኛ? ቀጭኑ ጠየቀ!!

አማኑኤል የጤነኞች መከማቻ ነው። አማኑኤል በቤት ጣጣ፣ በሃቴቴና በውቃቢ፣ በጋኔን “ግብር አነሰኝ” ቁጣ ከሚመጡት በስተቀር አብዛኞቹ የተነኩበት ጉዳይ ያሳዝናል። ካንዳበታቸው የሚወረወረው ሁሉ እውነት ነው። “አገሬ አይ እድልሽ” እያሉ የሚለፈልፉ፣ “አትግደል፣ አትግደል፣ አትግደል … “ እያሉ የሚወተውቱ፣ “ልብ ያለው ልብ ይበል፣ ልብ ያለው ያስተውል፣ አዳምጡን፣ ስሙኝ፣ ጆሯችሁን አቁሙ” እያሉ የሚያስጠነቅቁ ውብ ሰዎች አማኑኤል “እብድ” ተብለው አሉ። የሚገርመው ጡረተኛዋ ቀዳማዊት እመቤት ናቸው “የበላይ ጠባቂያቸው” አይ አለም!!

አንድ ጊዜ አንድ የአማኑኤል ሰራተኛ የነገሩኝ ታወሰኝ። አማኑኤል ሆስፒታል ያሉ ታካሚ እህቶች “ውርጃ ይከናወንላቸዋል” አለኝ። የሰማሁትን ማመን አቃተኝ። እንዴት እንደሆነ ለማወቅ ማብራሪያ አቀረብኩ። ሰራተኞች እንደሚተናኮሱዋቸው/እንደሚገለገሉባቸው ተረዳሁ። አፈርኩ። አመመኝ። አሁን ማን ነው ጤነኛ? የሚገርመው ውርጃ የሚፈጽምላቸው የግል ተቋም እንዳለ መሰማቱ ነው። ጉዳዩን ብዙም ማጣራት ባልችልም “እብዶች” ስለማርገዛቸው ከበቂ በላይ ማስረጃ አለ። ወ/ሮ አዜብ እንደ አሁኑ ሳይተነፍሱ ይህንን እንኳን ለፍርድ ቢያቀርቡ ምንኛ ከኖረው ሃጢያታቸው ሁሉ በነጹ ነበር!! መስመር ሳትኩ መሰል ወደ መነሻዬ ልመለስ።

አዎ ቤት አገር ነች። ቤት ከተቃጠለ መጠለያ የለም። በተለይ በግራም በቀኝም መሸሻ የሌላቸው ምስኪኖች ያሳዝናሉ። “አለን አለን ሲሉ፣ ይናዳል ገደሉ” ተብሎ የለ!! ከተናደ ተናደ ነው። ደርግ ሲናድ ጥላ ሳይቀር ያስደነግጥ ነበር። ሲናድ ጥላም ያስፈራል። ሲናድ ስንቄን፣ ሃብቴን፣ ወርቄን፣ ፋብሪካዬን፣ ህንጻዬን፣ መኪናዬን፣ ቤተመንግስቴን…. የሚባል ዘባተሎ ሃሳብ የለም። ሁሉም እንደ ጉም ይተናል። እንደ ሴትየዋ ቤት “ዓመድ” ይሆናል። ዓመድ!! ታዲያ ያ-ክፉ ሃሳብ ሳይሰለጥን ሁላችንም ወደ ልባችን ብንመለስስ? ስለ ሰላም ብናለቅስ? ይቅር ባይነት “ዓመድ” ከመሆን ይሰውራልና !! ከግንቦት ሃያ ያተረፍነው የጎሳ ፖለቲካ ምሱ ዓመድ ነውና 23ኛውን “በዓል” የግንቦት 20 ዓመዳማ ፍሬዎች!! ብንለውስ? ክብር ይህንን ጊዜና የተሰውበትን ዓላማ ሳይመለከቱ ላለፉ ታጋዮች!! ግን ይህንን በደማቸውና ባጥንታቸው ላይ የተገነባውን “ዓመድ” የሚያደርግ የፖለቲካ ቀመር ከሚያዩት ሞታቸው አይሻልም? ፍሬዎቹን ኢህአዴግ በሰፊው ስለሚመጣባቸው አልፌያቸዋለሁና። ለማመጣጠን ኢቲቪን ይመልከቱ!!

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የገዳ ሥርዓት እና የኦሮሞ ገዢ መደብ June 20, 2022 11:34 pm
  • “የወልቃይትን ጉዳይ ለድርድር የማናቀርበው ቀይ መስመራችን ነው” ርዕሰ መስተዳድር ይልቃል June 12, 2022 07:09 pm
  • የሰሜን ምዕራብ ዕዝና የአማራ ልዩ ኃይል ተከዜ ክፍለ ጦር ዕውቅናና ሽልማት ተሰጣቸው June 12, 2022 06:21 pm
  • ሀገር በቀል ባህላዊ የግጭት አፈታቶችን በተገቢው በመጠቀም ዘላቂ እርቅና ሰላምን ማምጣት ይቻላል June 12, 2022 05:40 pm
  • የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን በገረጂና በቀበና ያስገነባቸውን የመኖሪያ አፓርትመንቶች አስመረቀ June 12, 2022 05:35 pm
  • በኦነግ ሸኔ ፈርሶ የነበረውና ወታደራዊ ጠቀሜታ ያለው ድልድይ ተጠግኖ አገልግሎት መስጠት ጀመረ June 10, 2022 09:13 am
  • ጃዋር በዳውድ ኢብሣ ቀይ መስመር ተሰመረለት June 8, 2022 12:59 pm
  • ወልቃይት: ቢመረንም ለመዋጥና ራሳችንን ለመመልከት እንሞክር June 8, 2022 11:53 am
  • እብድ ይሻለዋል እንጂ አይድንም፤ ሐጂ ጃዋር አሁን ለምን ብቅ አለ? June 8, 2022 05:59 am
  • ሕዝብ ድምፅ የነፈጋቸው “ፓርቲዎች” የሽግግር መንግሥት ይቋቋም አሉ June 7, 2022 01:11 am
  • “አድጌ እንደናንተ መሆን እፈልጋለሁ” June 5, 2022 06:58 pm
  • በሳምንት ለ100 ያህል ሕሙማን አገልግሎት የሚሰጥ የኩላሊት ዕጥበት ማዕከል ሥራ ጀመረ May 30, 2022 02:20 am
  • የጥቁር አንበሳ ዕጩ መኮንኖች (ካዴቶች) ተመረቁ May 29, 2022 04:01 pm
  • “ኢትዮጵያን መንካት አይቻልም!!” በሚል ቁጭት ነው እየሠራን ያለነው May 29, 2022 01:04 pm
  • “ከሞፈርና ቀንበር ወደ ትራክተር” በሚል መርህ ለአማራ ገበሬዎች የግብርና ሜካናይዜሽን ተሰጠ May 29, 2022 02:02 am
  • ኢትዮ 360 “የወያኔ፣ የጁንታ ሚዲያ ነው” – ባለከዘራው ጄኔራል May 27, 2022 02:51 am
  • “እኛ የምናውቀው ነገር የለም፤ የሚያጣሉን ፖለቲከኞች ናቸው” የአማራ ወዳጃቸውን አደራ ቤት የመለሱ የቅማንት ተወላጅ May 27, 2022 01:40 am
  • ትግራይን አገር እናደርጋለን፤ “በውይይት እና በጦርነት” ሁሉንም ጉዳይ እንቋጫለን – የወንበዴው መሪ ደብረጽዮን May 26, 2022 09:18 am
  • “ሁለቱ የምዕራብ ዕዝ ተዋጊ ዶክተሮች” May 26, 2022 08:19 am
  • ወደ ትህነግ ሊተላለፍ የነበረ አምስት ሚሊዮን ብር ከ20 ተጠርጣሪዎች ጋር ተያዘ May 25, 2022 01:57 am
  • የጦርነቱ ስትራቴጂያዊ እውነታዎች May 19, 2022 09:37 am
  • በጦርነቱ የተጎዱ አካባቢዎችን ለማቋቋም የሚውል የ15 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር ድጋፍ የዓለም ባንክ May 16, 2022 10:22 am
  • በአዲስ አበባ 1 ሺህ 98 የብሬን እና 2 ሺህ 162 የክላሽ ጥይት ተያዘ May 16, 2022 10:10 am
  • በአዲስ አበባ ከተማ በግለሰብ መኖሪያ ቤት ከ5 ሺህ በላይ የአሜሪካ ዶላርና የተለያዩ አገራት ገንዘቦች ተያዙ May 16, 2022 09:53 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2022 · Goolgule