እንደ - መግቢያ በኢትዮጵያ ታሪክ አፃፃፍ ላይ ብዙ ልዩነቶች ይስተዋላሉ፡፡ የልዩነቶቹ ሥረ-ምክንያት እንደ ጸሐፊው ማንነትና የሥርዓታቱን ባህሪ መነሻ ያደረገ ነው፡፡ ከዚህ የተነሳ የኢትዮጵያን የቀደመ ታሪክ የሚቃኙ የተለያዩ ኃይለ-ሐሳቦች በየጊዜዉ እንዲጸባረቁ ግድ ብሏል፡፡ የታሪክ ትንቅንቁ በአጥቂነትና በተከላካይነት የሚበየን ነው፡፡ በኢትዮጵያ ታሪክ ዙሪያ ፍልሰት፣ መስፋፋት፣ ብሔራዊ ጭቆና፣ ቅኝ ግዛትና መሰል ቃላት ላለፉት አርባ ዓመታት፤ በተለየ መልኩ ደግሞ ላለፉት ሃያ አራት ዓመታት የታሪክ ሙግት አጀንዳ አስቀማጭ ቃላት ሆነዋል፡፡ ባሳለፍነው የሩብ ክፍለ ዘመን ጉዟችን የታሪክ ጉዳይ እጅግ አብሰልሳይና ውርክብ የበዛበት ሊሆን የቻለው አገዛዙ ለኢትዮጵያ የቀደመ ታሪክ በጎ እይታ የሌለው በመሆኑ ነው፡፡ በዚህም የተነሳ የታሪክ ነክ ሙግቶች ታይቶ በማይታወቅ መልኩ ዱላ ቀረሽ ደረጃ … [Read more...] about የኢትዮጵያ የታሪክ ውዝግብ የወለደው አዲሱ የሕዝባዊ ታሪክ ፀሐፊና መርማሪ – በዕውቀቱ ሥዩም
Literature
ጽፈኪን
እኚህ ሰው ማናቸው? – ፳
ከአዘጋጆቹ፤ በጎልጉል ወዳጅ ወለላዬ ጀማሪነትና አቀናባሪነት ሲስተናገድ የነበረው “እኚህ ሰው ማናቸው?” የተሰኘው ዝግጅታችን እንደገና ተጀምሯል፡፡ ለረጅም ጊዜ በመቋረጡ ይቅርታ እየጠየቅን አሁን ግን በወዳጃችን ወለላዬ ብርቱ ትጋት ለመጀመር በመቻላችን ለወለላዬ ምስጋናችንን እናቀርባለን፡፡ በዝግጅቱ ስትካፈሉ ለነበራችሁና መልሳችሁን ስትሰጡ ለነበራችሁ ሁሉ አሁንም ይህንኑ ማድረግ እንድትጀምሩ ልናሳስባችሁ እንወዳለን፡፡ የዝግጅቱ ዋና ዓላማ በአገራችን ስማቸውን ተክለው ያለፉ በፎቶ አስደግፎ የግጥም ጥያቄ ማቅረብ ሲሆን ተሳታፊዎችም ምላሻችሁን በግጥም እንድትመልሱ ትደፋፈራላችሁ፡፡ ታሪክ በሥነቃል ታጅቦ ያዝናናል፤ ዝርዝር ጥናት ለማድረግ ለሚፈልግ ደግሞ ብርሃን ይፈነጥቃል፡፡ ለአሁኑ የእኚህን ሰው ፎቶ በግጥማዊ ጥያቄ አጅበን አቅርበናል፡፡ ከላይ እንዳልነው ቢቻል በግጥም ምላሻችሁን ከሥር … [Read more...] about እኚህ ሰው ማናቸው? – ፳
አንቺን አስታዋሼ
መቼ ትመጫለሽ መቼ ልጠብቅሽ ወይ መቼ ላምጣልሽ መቼ ላቀብልሽ ሽሮና . . . ምናምን ስለተላከልሽ ሽሮውን ውሰጂው በርበሬውን ውሰጅ ቅቤውንም ውሰጅ . . . ሚጥሚጣ ተይልኝ እሱ ስለሆነ - አንቺን ሚያስታውሰኝ ............................. ምን ይሰራልሀል ብቻውን ሚጥሚጣ ትደፋው የለም ወይ እንጀራ ስታጣ … [Read more...] about አንቺን አስታዋሼ
አቶ ዠ፣ ጸሃፌ-ተውኔት
አቶ ዠ ከጸሃፌ-መፈክር ወደ ጸሃፌ-ተውኔት እሸጋግራለሁ ብለው መፈከራቸው እንዳለ ሆኖ፣ ይንን አስመልክቶም ለኢሃዴግ ፍቅር ቴአትር ቤት ሥራ አስቀማጭ ደብዳቤ መላካቸው እንዳለ ሆኖ፣ ... ከወራት በኋላ የአቶ ዠ ባለቤት ወይዘሮ ዘ ቡና አፍልተው ከአቦል እስከ በረካ ተጠጥቶ እንዳለቀና ሥኒ እያጠቡ እያለ... ወይዘሮ ዘ ገረሙህ?“ባልና ሚስት ካንድ ባህር ይቀዳል” ሲባል አልሰማህም?ባላቸው ዠ ከሆኑ እሳቸው ከ ዘ ሌላ ምን ሊሆኑ ይችላሉ?ዠ እኮ ባርኔጣ የደፋ ዘ ነው።ከምሬ ነው። ካላመንከኝ ሥለ ቃላትና ፊደላት የሚፈላሰፉ “ዲባቶ”ዎች ፈልግና ጠይቅ። ሥምህ ጨ ከሆነ የምታጫትና የምታገባት ኮረዳ ጠ ነው የምትባለው። እና ቡና ተጠጥቶ እንዳለቀ፣ አቶ ዠ ከባለቤታቸ ጋር “ጨዋታ” ጀመሩ። “ጨዋታ“ው ሲያልቅ ጻፉት፣ አቶ ዠ፣ ጸሃፌ-ተውኔት። ገጸ-ባህርያት ዠ እና ዘ ብለው ጀመሩ። ዘ … [Read more...] about አቶ ዠ፣ ጸሃፌ-ተውኔት
ዳሪና ቀባሪ
ዳሪ ወዳጄ እንደምነህ - ውዱ ጎረቤቴ ባለህበት ቦታ - ይድረስህ መልክቴ የልጄ ሰርግና - የሟች ልጅህ ቀብር አንድ ላይ መሆኑ - ፈጥሮብኛል ችግር መቼም ይገባሃል - ግልጽ ነው ነገሩ ብዙ ነው ማዕረጉ - የሠርገኛ ክብሩ ስለዚህ አደራ - የልጄን ታላቅ ሠርግ በደስታ በሆታ - እንዳሳልፍ በወግ በዛ ቀን ተነስተህ - ልጅህን ስትቀብር ስዎችን ሰብስበህ - አታብዛ ግርግር እንደውም ጨርሶ - ከሞት ላታድናት በሳቅ በደስታ - በ`ልልታ ቅበራት ለለቅሶኛው ሁሉ - ይኼን ንገርልኝ ነገ ማታ ድረስ - መልስህን ላክልኝ ቀባሪ ክቡር አስተዳደር- የላኩልኝ መልዕክት እጅግ አስገራሚ - ድንቅ ነው በእውነት ታስራ ተገንዛ - ልጅ ልትቀበር ተሞሸረች አሉኝ - የርስዎ ልትዳር ለክብርዎ ሲባል - ለርስዎ ወግ … [Read more...] about ዳሪና ቀባሪ
“የናፈቀ ሰዉ በር በሩን የታከተ ሰዉ መስኮቱን ይመለከታል” በዕዉቀቱ ስዩም
ከዓመታት የንባብ ብህትዉና በኃላ በቀጣይ ሳምንት በመጽሃፍ መልኩ ብቅ የሚለዉ በዕዉቀቱ ስዩም፣ በርከት ያሉ ሞጋች ሃሳቦችን በሥነ-ጽሁፋዊ ለዛ እያዋዛ ወደ አደባባይ እንደሚያወጣ ጥርጥር የለዉም፡፡ "ከአሜን ባሻገር" ምን አለ? . . . የመራቂዉን ማንነት መፈተሸ …? ጥልቅ መጠይቅ …? ወይስ ለየት ያለ ፍንገጣ? ... ብቻ ብዙ ነገር ይጠበቃል፡፡ በተለይ ጽዮን ተኮር ኃይማኖታዊ ባህልና መስመር ያለፈ ጥብቅ ብሄርተኝነት ስላጎበጣት ኢትዮጵያ "ከአሜን ባሻገር" ብዙ የምትለን ይመስለኛል፡፡ ታሪክን ከፖለቲካዊ ወገንተኝነት እና ከኃይማኖታዊ ጥብቅና በጸዳ መልኩ ለማየት የሚጥረዉ በዕዉቀቱ፣ ንባብ የፈጠረለት አቅሙን ተጠቅሞ በግሉ ከደረሰበት የታሪክ ምልከታ አኳያ የሚያካፍለን ብዙ ነገር እንደሚኖር እጠብቃለሁ፡፡ ባለመርማሪ ልቦናዉ በዕዉቀቱ፣ የጊዜችን ቋሚ ሽፍቶችን በተመለከተ ሽሙጥን በተሻገረ … [Read more...] about “የናፈቀ ሰዉ በር በሩን የታከተ ሰዉ መስኮቱን ይመለከታል” በዕዉቀቱ ስዩም
የተቆለፈበት ቁልፍ!
ከዶ/ር ምህረት ደበበ፣ የአዕምሮ ህክምና ስፔሺያሊስት፣ እ.አ በ2005 ዓ.ም የተጻፈ መጽሀፍ፣ 438 ገጽ ትችት! በዶ/ር ፈቃዱ በቀለ፣ የስልጣኔ ተመራማሪና የኢኮኖሚ ዕድገት ባለሙያ! ይህን መጽሀፍ አግኝቴ ለማንበብ እድል ያጋጠመኝ ከሁለት ሳምንት በፊት ባለቤቴ ወደ ኢትዮጵያ ሄዳ ስትመለስ ይዛልኝ ከመጣች በኋላ ነው። በዶ/ር ምህረት ደበበ የተጻፉ ሁለት ወፈፍራም መጽሀፎች ሲሆኑ፣ አንደኛው መጽሀፍና በቅርብ የወጣውን የሽፋኑ ሰዕል ደስ ስላለኝ እንደ አጋጣሚ አንስቼ ካገላበጥኩኝ በኋላ፣ እስቲ ብዬ ደግሞ ሌላውን ሳገላብጥ አቀራረቡ ደስ ስላለኝ ሃሳቡን ይበልጥ ለመረዳትና ለመገምገም ሆነ ወይም ለመተቸት እንዲያመቸኝ በሚል በመጀመሪያ ያገላበጥኩትን በመተው ቀደም ብሎ የታተመውን ማንበብ ጀመርኩኝ። እንደ ዕውነቱ ከሆነ አንዳንድ ጊዜ ከኢትዮጵያ የሚመጡ በአማርኛ ቁንቋ የተጻፉ መጽሀፎችን … [Read more...] about የተቆለፈበት ቁልፍ!
በንቁጣጣሽ! ምን ቀጠፈሽ?
ዘመን ፊትሽ ተከምሮ እየታዬ ስራሽ አምሮ እንቁጣጣሽ አንድ ብለሽ አርባ ድረስ እድሜ ቆጥረሽ እንደ ቤቶች የሳቅ ተውኔት እንደ ጨቤ ስካር ህይወት ሞት ራሱን ያሾፍሽበት ለምንድነው? በይ ንገሪኝ እባክሽን አደብቂኝ ባንቺው ቀዬ የተወለድኩ ፊደል በጄ እዛው የያዝኩ መስፍን ሜዳ የተራገጥኩ በጨበጣ ብይ ያስቆጠርኩ ቲቸር ታዬ ያስተማሩኝ ገብሬ ኩርኩም ያቀመሰኝ የሲሚንቶ ጭስ ያወዛኝ ቅዱስ ያሬድ ተሳልሜ ከሽፋ ቤት ተሰይሜ ያቶ ማሞን ኪኒን ቅሜ እዛው ኖሬ እዛው ያደኩ የቃጠሎው ቀን የተረፍኩ እኔ እማውቅሽ የማታውቂኝ የሰፈርሽ አንድ ስው ነኝ ይሄን ሁሉ ዘርዝሬልሽ ጥያቄዬን ስጠይቅሽ ዝም አትይም መቼም ከፍተሽ ፊት ለፊትሽ ተስፋሽ ሞልቶ እየታየ ዝናሽ ጎልቶ እንደጸደይ ባገር ፈክተሽ በህዝብ ፊት ደምቀሽ ታይተሽ በአዲስ አመት በንቁጣጣሽ በ´ለቱ ለት … [Read more...] about በንቁጣጣሽ! ምን ቀጠፈሽ?
እነኚህ ሰዎች ማናቸው? – ፲፱ መልስ
ከአዘጋጆቹ፤ ከጥቂት ወራት በፊት በወዳጃችን ወለላዬ ለቀረበው የበርካታ በቀዳማዊ ኃይለሥላሴ አገዛዝ ዘመን የካቢኔ አባላት የነበሩ ባለሥልጣናትን ፎቶ ለያዘው ጥያቄ ምላሽ በመስጠት የተባበራችሁትን ሁሉ ከልብ እናመሰግናለን:: ከተለያዩ ምንጮ ያሰባሰቡትን ምላሽ ወለላዬ አጠር ካለች ግጥም ጋር በቁጥራቸው ቅደም ተከተል አቅርበውታል፡፡ ከዘመኑ መብዛትና መረጃ መዛባት ምክንያት በምላሹ ላይ ስማቸው ወይም ማዕረጋቸው የተዛባ ቢኖር ማስተካከያ ለሚሰጡ ሁሉ አሁንም በቅድሚያ ምስጋናችን ይድረሳቸው፡፡ መልስ በዝርዝር ማስቀመጥ - በቁጥሩ በስሙ ለመግጠም የሚያስችል - ነበረኝ አቅሙ ነገር ግን ለአንባቢ - እዚህጋ ሲቀመጥ እንደዚህ ሲሆን ነው - የሚጥመው ይበልጥ በማለት አስቤ - የሁሉም ዝርዝር ከስር አስፍሬያለሁ - በስማቸው አንፃር መርዕድ መንገሻ (ሜ/ጄኔራል) … [Read more...] about እነኚህ ሰዎች ማናቸው? – ፲፱ መልስ
ሌቦ ነይ …
ማስታወሻ፤ ከጥቂት ሳምንታት በፊት አንድ የህወሃት አባል ወይም ተላላኪ እንደሆነ የታሰበ ግለሰብ 5 ሚሊዮን የእንግሊዝ ፓውንድ የሚገመት (በፎቶው እንደሚታየው) ጥሬ ገንዘብና ወርቅ በሻንጣው ይዞ ከኢትዮጵያ ወደ ለንደን እንግሊዝ ሲገባ ጋትዊክ አየር ማረፊያ ላይ በፖሊሶች ተይዟል። ግለሰቡ ለመጀመሪያ የፍርድ ምርመራ ፍርድ ቤት በቀረበ ጊዜ ዳኛው “ይህን ያክል ገንዘብ እንዴት በሻንጣ ልትይዝ ቻልክ?” የሚል ጥያቄ ሲያቀርቡ፣ ግለሰቡ “ገንዘቡ የመንግስት መሆኑንና ለመንግስት ስራ ለማዋል መያዙን” ገልጾዋል። ይሁን እንጂ ዳኛው “ይህን ያህል ገንዘብ በሻንጣህ የያዝከው በአገራችሁ ባንክ ስለሌለ ነው እንዴ?” በማለት ጥያቄ አቅርበዋል። ግለሰቡ ለጊዜው በዋስ የተፈታ ሲሆን፣ መስከረም ላይ በድጋሚ እንደሚቀርብ ተነግሯል። የወለላዬ ግጥም በዚህ ዘረፋ ላይ የተመሠረተ ነው፡፡ (ቅርብ የሆናችሁ … [Read more...] about ሌቦ ነይ …










