• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

አቶ ዠ፣ ጸሃፌ-ተውኔት

January 29, 2016 08:47 am by Editor 1 Comment

አቶ ዠ ከጸሃፌ-መፈክር ወደ ጸሃፌ-ተውኔት እሸጋግራለሁ ብለው መፈከራቸው እንዳለ ሆኖ፣ ይንን አስመልክቶም ለኢሃዴግ ፍቅር ቴአትር ቤት ሥራ አስቀማጭ ደብዳቤ መላካቸው እንዳለ ሆኖ፣ … ከወራት በኋላ የአቶ ዠ ባለቤት ወይዘሮ ዘ ቡና አፍልተው ከአቦል እስከ በረካ ተጠጥቶ እንዳለቀና ሥኒ እያጠቡ እያለ…

ወይዘሮ ዘ ገረሙህ?“ባልና ሚስት ካንድ ባህር ይቀዳል” ሲባል አልሰማህም?ባላቸው ዠ ከሆኑ እሳቸው ከ ዘ ሌላ ምን ሊሆኑ ይችላሉ?ዠ እኮ ባርኔጣ የደፋ ዘ ነው።ከምሬ ነው። ካላመንከኝ ሥለ ቃላትና ፊደላት የሚፈላሰፉ “ዲባቶ”ዎች ፈልግና ጠይቅ። ሥምህ ጨ ከሆነ የምታጫትና የምታገባት ኮረዳ ጠ ነው የምትባለው። እና ቡና ተጠጥቶ እንዳለቀ፣ አቶ ዠ ከባለቤታቸ ጋር “ጨዋታ” ጀመሩ።

“ጨዋታ“ው ሲያልቅ ጻፉት፣ አቶ ዠ፣ ጸሃፌ-ተውኔት። ገጸ-ባህርያት ዠ እና ዘ ብለው ጀመሩ።

ዘ     እኔ የምልህ?ጠባብ ብሄርተኝነት ምንድነው?

ዠ    ዴሞክራሲያዊ ብሄርተኝነት ያልሆነ ማለትነው?

ዘ     “ውሃ ሲወቅጡት እምቦጭ አለ” አሉ። ልዩነቱ ምንድነው?

ዠ    ጠባብ ብሄርተኝነትማ ልክ እንደምታጥቢው ሥኒ ማለት ነው።(አሉ አቶ ዠ የሚታጠበውን ሥኒ እያዩ።)

ሥኒ ውስጥ ከጀበና ቡና ብትቀጂበት ያው ያቺኑ የተቀዳችውን ብቻ ነው የሚይዘው። ከዚያ በላይ አይችልም። ጠባብ ነዋ! በተፈጥሮው፣ ባሰራሩ ጠባብ ነዋ!ያ እንግዲህ የጠባብ ብሄርተኝነት ምሳሌ ሊሆን ይችላል።

ዘ     አሃ!(የገባቸው አይመስሉም፣ ወ/ሮ ዘ)

ዠ    ዴሞክራሲያዊ ብሄርተኝነት ደግሞ እንደ ጀበናሽ ነው። የያዘውን ሁሉ የሚያከፋፍል። አየሽ ጀበና ታጋሽና ለጋሽ ነው። እሳት ላይ በዝምታ ተጥዶ፣ ቡና ተፈልቶበት፣ ያን ሁሉ ችሎ፣ በኋላ ለሥኒዎች ሁሉ የያዘውን ያከፋፍላል።

ዘ     አሃ!ዴሞክራሲያዊ ብሄርተኝነት እንደ ጀበና ነው?ከሰል ላይ እንደምጥደው ጀበና ነው?እሳት ጠግቦ ግንፍል ግንፍል እንደሚለው ጀበናዬ ነው?

ዠ    ኤዲያ ያንቺ ነገር፣ ቢገነፍል ባይገነፍል የዴሞክራሲያዊ ብሄርተኝነት መብቱ ነው።

ዘ     እንግዲህ ቡናዬን በሰላም ለመጠጣት፣ ግንፍል ግንፍል ባዩን ጀበናዬን፣ ከፊሉን ቡናዬን አፍሳሹን ጀበናዬን፣ በዚህም ምክንያት ከሰሌን የሚያዳፍነውን ጀበናዬን፣ ከከሰል አውርጄው እሲኪሰክን በዝምታ መጠበቅ ያለብኝ ጀበናዬ ነው የዴሞክራሲያዊ ብሄርተኝነት ምሳሌ ነው የምትለኝ?

ዠ    እንዴ ይሄን ሁሉ አመት ታግሰሽ ኖረሽ የለም እንዴ?“ግንፍል፣ ግንፍል የሚለውን፣ ሁሌ እሲሰክን መጠበቅ ያለብኝን” ብለሽ የምትታዘቢው?

ዘ     ህምምምምም… እሱስ ልክ ነው። ታግሼ ችየዋለው። ሲሟሽ፣ ሲሟሽ ከከረመ፣ ከዛሬ ነገ ይሻለዋል ብዬ ችየዋለሁ።

(ጀበና ትተው የወሬ ርዕስ ቀየሩ፣ ወ/ሮ ዘ)

እኔ የምለው? ምሥር ደግሞ “ኢትዮጵያን እወራለሁ፣ አባይ ይነካና ዋ!” ብላ ትፎክራለች አሉ። እኔ እንኳን ጭምጭምታ ነው የሰማሁት። እሳት ላይ ተወርቷል አሉ። “ይቼ ጥሬ፣ ይቺ ምሥር፣ ካደረች አትቆረጠምም” አሉ አበው።

ዠ    ዛሬ ደግሞ ከበደ ሚካኤልን መሆን አማረሽ እንዴ?ምነው ተረትና ምሳሌ አበዛሽ?። ግብጽ በማለት ፈንታ ምሥር የምትይውና የምትተርቺው?ደግሞ የእሳት ወሬ አታምጭብኝ። እሳት ማለቴ “ኢሳት ይፋጃል” ሲባል አልሰማሽም?ሲፈጃቸው እኔ ዠ የእሳቱ ማብረጃ፣ ማጥፊያ መሆን አልፈልግም። “ግብጽ ብትመጣ እንዘምታለና!ግብጽ ምናባቷ እንዳትሆን ነው?እስኪ ትምጣና እናያለና!” ነው የሚባለው።

ዘ     ፉከራ!መፈከር ብቻ!

ዠ    መፈከር ሥራዬ እንደነበር አጣሽው እንዴ?

ዘ     ዘመቻ?ዘመቻ?የምንበላው የሌለን ሰዎች በባዶ ሆዳችን ነው የምንዘምተው?አሃ!

(አሉ ወ/ሮ ዘ ወደሰማይ አንጋጠው፣ መንግስተ ሰማያት ተከፍቶ የሆነ ነገር የነገራቸው መስለው ተናገሩ።)

አሃ! ስኳር! ስኳር ፋብሪካ ይስፋፋ የተባለው ለዚህ ነው ለካ!ስኳር እየበላን እንዘምታለና። ኢሃዴግ ስኳር እየቃመ ተዋግቶ አይደለም እንዴ ነጻ ያወጣን?ከተመክሮ የተገኘ መላ ነው። የስኳር ፋብሪካ ይስፋፋ!

(አቶ ዠ ለመናገር አፋቸውን ከፈቱ። ልክ ያኔ…)

ዠ   ደግሞ ይህንን ግንፍል፣ ግንፍል ባይ፣ ገሚሱን ቡናዬን ደፊ ጀበና ከዛሬ ጀምሮ አልፈልግም ብለው ጀበናውን ወለሉ ላይ ከሰከሱት።

አቶ ዠ ይህንን “ጨዋታ” ጻፉና ወረቀቱን ኪሳቸው ውስጥ ከተው ወደ ኢሃዴግ ፍቅር ቴአትር ቤት አቀኑ። በመንገዳቸው ላይ የአቡነ ጴጥሮስ ሃውልት ቆሞበት የነበረው ቦታ ላይ አንድ ሰውዬ ቆመው አዩ። ሰውዬ የአቡኑን ሃውልት የሚፈልግ ይመስላሉ። አቶ ዠ አልፈዋቸው ሊሄዱ ሲል ሰውዬው ጮክ ብለው ተናገሩ። የተናገሩት መንገደኛው፣ አላፊ አግዳሚው እንዲሰማቸው አልነበረም። አቶ ማሞ፣ ወፍጮ ቤታቸውና መኖሪያ ቤታቸው ለባቡር መሄጃ ተብሎ የፈረሰባቸው፣ አቶ ማሞ ለራሳቸው ተናገሩ።

“እኔና የአቡነ ጴጥሮስ ሃውልት የትም ወድቀን መቅረታችን ነው?”

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Literature, Opinions Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Comments

  1. Gilentufagonji says

    January 30, 2016 12:15 am at 12:15 am

    Please speak freely, you are born free.So,why you go all around?

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • በጦርነቱ የተጎዱ አካባቢዎችን ለማቋቋም የሚውል የ15 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር ድጋፍ የዓለም ባንክ May 16, 2022 10:22 am
  • በአዲስ አበባ 1 ሺህ 98 የብሬን እና 2 ሺህ 162 የክላሽ ጥይት ተያዘ May 16, 2022 10:10 am
  • በአዲስ አበባ ከተማ በግለሰብ መኖሪያ ቤት ከ5 ሺህ በላይ የአሜሪካ ዶላርና የተለያዩ አገራት ገንዘቦች ተያዙ May 16, 2022 09:53 am
  • አገር አፍራሹ ትህነግ ለቀለብ፣ መድኃኒትና ሥራ ማስኬጃ 76 ቢሊዮን ብር ቀርጥፏል May 16, 2022 08:30 am
  • እየተባባሰ ከመጣው የማህበራዊ ሚዲያ አጭበርባሪዎች ዜጎች ራሳቸውን እንዲጠብቁ ተጠየቀ May 15, 2022 09:38 am
  • የትህነግና ሸኔ መሠልጠኛ የምትባለው ዩጋንዳ መከላከያ ሚ/ር ከኤታማዦር ሹሙ ጋር ተወያዩ May 13, 2022 09:55 am
  • በትግራይ የውጊያ ምልመላው ጉዳይ May 11, 2022 02:37 am
  • መከላከያ በተጨማሪ ድሮን፣ በሥልጠና፣ በዝግጅት ራሱን አብቅቷል May 11, 2022 01:35 am
  • ትህነግ ለሌላ ውጊያ እየተዘጋጀ ነው ተባለ May 10, 2022 01:04 pm
  • ኤርትራ 8 ሩስያ ሠራሽ ድሮኖችን ተረክባለች May 10, 2022 12:37 am
  • ሙስሊምና ክርስቲያን በአንድነት የሚያከብረው የአኾላሌ ባሕላዊ ጭፈራ May 9, 2022 01:46 pm
  • በወልዲያ ፋኖዎች ተመረቁ May 9, 2022 12:51 pm
  • “ሠራዊታችን ድልን በአስተማማኝ መልኩ ማምጣት በሚችል ቁመና ላይ” ጀኔራል ጌታቸው May 9, 2022 11:57 am
  • ዋጋው 64 ሚሊዮን ብር የሚሆን (16 ኪሎ) ሕገወጥ ወርቅ ተያዘ May 9, 2022 11:51 am
  • አብን ክርስቲያን ታደለን ለመጨረሻ ጊዜ አስጠነቀቀ፤ 10 አባላቱን አገደ May 9, 2022 08:58 am
  • ራሱ አቡክቶ፣ ራሱ አሟሽሾ፣ ራሱ ጋግሮ በሰዓት 460 እንጀራ የሚያወጣ ፈጠራ May 9, 2022 08:17 am
  • በህገ ወጥ መንገድ 19 ህጻናትን ሲያዘዋወሩ የነበሩ 6 ሴቶች ተያዙ May 8, 2022 12:39 am
  • በአርሲ ሙስሊሞች ለቤ/ክ ማሠሪያ 3 ሚሊዮን ብርና 20 የቀንድ ከብት ሰጡ May 6, 2022 09:35 am
  • በአዲስ አበባ የሚኖረው የትህነግ ደጋፊ ማንነት በማስረጃ May 4, 2022 11:04 pm
  • ሙስሊም ወንድማማች የቤ/ክ ዘራፊዎችን በቁጥጥር ሥር አዋሉ May 4, 2022 09:04 am
  • ከ6 ሺህ የዓሳ ጫጩት ወደ 80 ሺህ May 4, 2022 08:57 am
  • ተስፋቢሱ ቴድሮስ May 3, 2022 12:16 pm
  • ከሽፏል! April 6, 2022 11:58 am
  • “ሩሲያ ዩክሬይንን ወረረች” እየተባለ ስለሚነዛው ወሬ ጥቂት እውነታዎች March 8, 2022 11:30 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2022 · Goolgule