• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

አቶ ዠ፣ ጸሃፌ-ተውኔት

January 29, 2016 08:47 am by Editor 1 Comment

አቶ ዠ ከጸሃፌ-መፈክር ወደ ጸሃፌ-ተውኔት እሸጋግራለሁ ብለው መፈከራቸው እንዳለ ሆኖ፣ ይንን አስመልክቶም ለኢሃዴግ ፍቅር ቴአትር ቤት ሥራ አስቀማጭ ደብዳቤ መላካቸው እንዳለ ሆኖ፣ … ከወራት በኋላ የአቶ ዠ ባለቤት ወይዘሮ ዘ ቡና አፍልተው ከአቦል እስከ በረካ ተጠጥቶ እንዳለቀና ሥኒ እያጠቡ እያለ…

ወይዘሮ ዘ ገረሙህ?“ባልና ሚስት ካንድ ባህር ይቀዳል” ሲባል አልሰማህም?ባላቸው ዠ ከሆኑ እሳቸው ከ ዘ ሌላ ምን ሊሆኑ ይችላሉ?ዠ እኮ ባርኔጣ የደፋ ዘ ነው።ከምሬ ነው። ካላመንከኝ ሥለ ቃላትና ፊደላት የሚፈላሰፉ “ዲባቶ”ዎች ፈልግና ጠይቅ። ሥምህ ጨ ከሆነ የምታጫትና የምታገባት ኮረዳ ጠ ነው የምትባለው። እና ቡና ተጠጥቶ እንዳለቀ፣ አቶ ዠ ከባለቤታቸ ጋር “ጨዋታ” ጀመሩ።

“ጨዋታ“ው ሲያልቅ ጻፉት፣ አቶ ዠ፣ ጸሃፌ-ተውኔት። ገጸ-ባህርያት ዠ እና ዘ ብለው ጀመሩ።

ዘ     እኔ የምልህ?ጠባብ ብሄርተኝነት ምንድነው?

ዠ    ዴሞክራሲያዊ ብሄርተኝነት ያልሆነ ማለትነው?

ዘ     “ውሃ ሲወቅጡት እምቦጭ አለ” አሉ። ልዩነቱ ምንድነው?

ዠ    ጠባብ ብሄርተኝነትማ ልክ እንደምታጥቢው ሥኒ ማለት ነው።(አሉ አቶ ዠ የሚታጠበውን ሥኒ እያዩ።)

ሥኒ ውስጥ ከጀበና ቡና ብትቀጂበት ያው ያቺኑ የተቀዳችውን ብቻ ነው የሚይዘው። ከዚያ በላይ አይችልም። ጠባብ ነዋ! በተፈጥሮው፣ ባሰራሩ ጠባብ ነዋ!ያ እንግዲህ የጠባብ ብሄርተኝነት ምሳሌ ሊሆን ይችላል።

ዘ     አሃ!(የገባቸው አይመስሉም፣ ወ/ሮ ዘ)

ዠ    ዴሞክራሲያዊ ብሄርተኝነት ደግሞ እንደ ጀበናሽ ነው። የያዘውን ሁሉ የሚያከፋፍል። አየሽ ጀበና ታጋሽና ለጋሽ ነው። እሳት ላይ በዝምታ ተጥዶ፣ ቡና ተፈልቶበት፣ ያን ሁሉ ችሎ፣ በኋላ ለሥኒዎች ሁሉ የያዘውን ያከፋፍላል።

ዘ     አሃ!ዴሞክራሲያዊ ብሄርተኝነት እንደ ጀበና ነው?ከሰል ላይ እንደምጥደው ጀበና ነው?እሳት ጠግቦ ግንፍል ግንፍል እንደሚለው ጀበናዬ ነው?

ዠ    ኤዲያ ያንቺ ነገር፣ ቢገነፍል ባይገነፍል የዴሞክራሲያዊ ብሄርተኝነት መብቱ ነው።

ዘ     እንግዲህ ቡናዬን በሰላም ለመጠጣት፣ ግንፍል ግንፍል ባዩን ጀበናዬን፣ ከፊሉን ቡናዬን አፍሳሹን ጀበናዬን፣ በዚህም ምክንያት ከሰሌን የሚያዳፍነውን ጀበናዬን፣ ከከሰል አውርጄው እሲኪሰክን በዝምታ መጠበቅ ያለብኝ ጀበናዬ ነው የዴሞክራሲያዊ ብሄርተኝነት ምሳሌ ነው የምትለኝ?

ዠ    እንዴ ይሄን ሁሉ አመት ታግሰሽ ኖረሽ የለም እንዴ?“ግንፍል፣ ግንፍል የሚለውን፣ ሁሌ እሲሰክን መጠበቅ ያለብኝን” ብለሽ የምትታዘቢው?

ዘ     ህምምምምም… እሱስ ልክ ነው። ታግሼ ችየዋለው። ሲሟሽ፣ ሲሟሽ ከከረመ፣ ከዛሬ ነገ ይሻለዋል ብዬ ችየዋለሁ።

(ጀበና ትተው የወሬ ርዕስ ቀየሩ፣ ወ/ሮ ዘ)

እኔ የምለው? ምሥር ደግሞ “ኢትዮጵያን እወራለሁ፣ አባይ ይነካና ዋ!” ብላ ትፎክራለች አሉ። እኔ እንኳን ጭምጭምታ ነው የሰማሁት። እሳት ላይ ተወርቷል አሉ። “ይቼ ጥሬ፣ ይቺ ምሥር፣ ካደረች አትቆረጠምም” አሉ አበው።

ዠ    ዛሬ ደግሞ ከበደ ሚካኤልን መሆን አማረሽ እንዴ?ምነው ተረትና ምሳሌ አበዛሽ?። ግብጽ በማለት ፈንታ ምሥር የምትይውና የምትተርቺው?ደግሞ የእሳት ወሬ አታምጭብኝ። እሳት ማለቴ “ኢሳት ይፋጃል” ሲባል አልሰማሽም?ሲፈጃቸው እኔ ዠ የእሳቱ ማብረጃ፣ ማጥፊያ መሆን አልፈልግም። “ግብጽ ብትመጣ እንዘምታለና!ግብጽ ምናባቷ እንዳትሆን ነው?እስኪ ትምጣና እናያለና!” ነው የሚባለው።

ዘ     ፉከራ!መፈከር ብቻ!

ዠ    መፈከር ሥራዬ እንደነበር አጣሽው እንዴ?

ዘ     ዘመቻ?ዘመቻ?የምንበላው የሌለን ሰዎች በባዶ ሆዳችን ነው የምንዘምተው?አሃ!

(አሉ ወ/ሮ ዘ ወደሰማይ አንጋጠው፣ መንግስተ ሰማያት ተከፍቶ የሆነ ነገር የነገራቸው መስለው ተናገሩ።)

አሃ! ስኳር! ስኳር ፋብሪካ ይስፋፋ የተባለው ለዚህ ነው ለካ!ስኳር እየበላን እንዘምታለና። ኢሃዴግ ስኳር እየቃመ ተዋግቶ አይደለም እንዴ ነጻ ያወጣን?ከተመክሮ የተገኘ መላ ነው። የስኳር ፋብሪካ ይስፋፋ!

(አቶ ዠ ለመናገር አፋቸውን ከፈቱ። ልክ ያኔ…)

ዠ   ደግሞ ይህንን ግንፍል፣ ግንፍል ባይ፣ ገሚሱን ቡናዬን ደፊ ጀበና ከዛሬ ጀምሮ አልፈልግም ብለው ጀበናውን ወለሉ ላይ ከሰከሱት።

አቶ ዠ ይህንን “ጨዋታ” ጻፉና ወረቀቱን ኪሳቸው ውስጥ ከተው ወደ ኢሃዴግ ፍቅር ቴአትር ቤት አቀኑ። በመንገዳቸው ላይ የአቡነ ጴጥሮስ ሃውልት ቆሞበት የነበረው ቦታ ላይ አንድ ሰውዬ ቆመው አዩ። ሰውዬ የአቡኑን ሃውልት የሚፈልግ ይመስላሉ። አቶ ዠ አልፈዋቸው ሊሄዱ ሲል ሰውዬው ጮክ ብለው ተናገሩ። የተናገሩት መንገደኛው፣ አላፊ አግዳሚው እንዲሰማቸው አልነበረም። አቶ ማሞ፣ ወፍጮ ቤታቸውና መኖሪያ ቤታቸው ለባቡር መሄጃ ተብሎ የፈረሰባቸው፣ አቶ ማሞ ለራሳቸው ተናገሩ።

“እኔና የአቡነ ጴጥሮስ ሃውልት የትም ወድቀን መቅረታችን ነው?”

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Literature, Opinions Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Comments

  1. Gilentufagonji says

    January 30, 2016 12:15 am at 12:15 am

    Please speak freely, you are born free.So,why you go all around?

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የአየለ ጫሚሶ ቅንጅት ፈረሰ January 18, 2021 02:31 pm
  • ህወሓት ተሠረዘ!!! January 18, 2021 01:32 pm
  • ዓሲምባ፣ ሣልሳዊ ወያኔና ባይቶና ከመፍረሳቸው በፊት ማብራሪያ እንዲሰጡ ተነገራቸው January 18, 2021 01:00 pm
  • ቤተሰቦች አስከሬን መውሰድ እንደሚችሉ ተነገረ January 14, 2021 06:48 pm
  • ስብሃት፤ “ከሞትን ቆይተናል፤ … አሁን የቀብር ሥነ-ስርዓታችን” እየተፈጸመ ነው January 14, 2021 01:37 pm
  • “ተመልሰን እንነሳለን” ያሉት ህወሓቶች ተመልሰው ወደማይነሱበት ተሸኙ January 13, 2021 01:12 pm
  • አፋር ነፃ አውጪ (ኡጉጉሙን) ለመጠቀም የታቀደው የህወሃት ሤራ ከሽፏል January 13, 2021 01:10 pm
  • ህወሃትን ወደ ጅቡቲ ለማሻገር ሲሰሩ የነበሩ የአፋር ታጣቂዎች በሰላም ወደ ክልሉ ገቡ January 13, 2021 06:47 am
  • በታህሳስ ወር ብቻ ከ344 ሚሊየን ብር በላይ የኮንትሮባንድ ዕቃ ተያዘ January 13, 2021 06:10 am
  • የብልፅግና ፓርቲ ቀጣይ ፈተና ምን ሊሆን ይችላል? January 13, 2021 04:10 am
  • ለትምህርት እንዲሆነን January 11, 2021 01:20 pm
  • “ከተቀበሩበት የጃርት ጉድጓድ ነው ያወጣናቸው” መቶ አለቃ ስዩም ቱርቦ January 11, 2021 12:11 pm
  • የተደመሰሱና በቁጥጥር ሥር የዋሉ የወንበዴው አባላት ይፋ ሆነ January 7, 2021 01:16 pm
  • ዐቢይና መኮንኖቹ በመቀሌ፤ “ድሉ የመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ነው” December 13, 2020 02:36 pm
  • ወንበዴው ህወሓት ከ1.4 ትሪሊዮን ብር በላይ ዘርፎ በውጭ አገራት ባንኮች አስቀምጧል December 8, 2020 01:05 am
  • ማይካድራ – የትህነግ የዘር ማጥፋት ጥግ ቋሚ ምስክር December 8, 2020 12:57 am
  • የወልቃይት ጠገዴ እናቶች ሰቆቃ ሲታወስ December 8, 2020 12:50 am
  • የደብረጽዮን ዋሻ December 7, 2020 11:30 pm
  • ባለ ከዘራው ኮሎኔል December 7, 2020 05:15 pm
  • ሰላማዊ ሕይወት በማይጨው December 7, 2020 04:12 pm
  • ተጠርጣሪ የፌዴራልና የአዲስ አበባ ፖሊሶች የመያዣ ትዕዛዝ ወጣባቸው December 7, 2020 11:46 am
  • ከ3 ሺህ በላይ ተተኳሽ ጥይቶች በወልዲያ ጉምሩክ ሊያሳልፉ የሞከሩ 4 ግለሰቦች ተያዙ! December 7, 2020 11:18 am
  • ወንበዴዎቹ ይጠቀሙባቸው የነበሩ ተሽከርካሪዎችና የግል ሰነዶቻቸው ተያዙ December 7, 2020 10:50 am
  • ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ በሶማሌ ክልል ተመሠረተ December 7, 2020 10:31 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2021 · Goolgule