• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“የናፈቀ ሰዉ በር በሩን የታከተ ሰዉ መስኮቱን ይመለከታል” በዕዉቀቱ ስዩም

January 12, 2016 09:27 pm by Editor 2 Comments

ከዓመታት የንባብ ብህትዉና በኃላ በቀጣይ ሳምንት በመጽሃፍ መልኩ ብቅ የሚለዉ በዕዉቀቱ ስዩም፣ በርከት ያሉ ሞጋች ሃሳቦችን በሥነ-ጽሁፋዊ ለዛ እያዋዛ ወደ አደባባይ እንደሚያወጣ ጥርጥር የለዉም፡፡ “ከአሜን ባሻገር” ምን አለ? . . . የመራቂዉን ማንነት መፈተሸ …? ጥልቅ መጠይቅ …? ወይስ ለየት ያለ ፍንገጣ? … ብቻ ብዙ ነገር ይጠበቃል፡፡ በተለይ ጽዮን ተኮር ኃይማኖታዊ ባህልና መስመር ያለፈ ጥብቅ ብሄርተኝነት ስላጎበጣት ኢትዮጵያ “ከአሜን ባሻገር” ብዙ የምትለን ይመስለኛል፡፡

ታሪክን ከፖለቲካዊ ወገንተኝነት እና ከኃይማኖታዊ ጥብቅና በጸዳ መልኩ ለማየት የሚጥረዉ በዕዉቀቱ፣ ንባብ የፈጠረለት አቅሙን ተጠቅሞ በግሉ ከደረሰበት የታሪክ ምልከታ አኳያ የሚያካፍለን ብዙ ነገር እንደሚኖር እጠብቃለሁ፡፡ ባለመርማሪ ልቦናዉ በዕዉቀቱ፣ የጊዜችን ቋሚ ሽፍቶችን በተመለከተ ሽሙጥን በተሻገረ መልኩ መረር ያለ ሂስ እንደሚሰነዝር እሙን ነዉ፡፡ በተለየም የነጻዉ ፕሬስን ቅርቃር በነገስታቱ ዘመን ለአዝማሪዋች ይሰጥ ከነበረዉ ነጻነት አኳያ እያነጻጸረ ትዝብቱን እነደሚያካፍለን ግምቴ ነዉ፡፡ የሃገሪቱን ዳቦ አልባ ልማት፣ እንደ ግዙፍ ፋብሪካ አንድ አይነት ምርት እያመረቱ ስላሉት ዩኒቨርስቲዎቻችን፣ የንፉቅቅ ሚሄደዉን “ዴሞክራሲ” ያችንን በቸልታ የሚያልፋቸዉ አይመስልም፡፡ ማህበራዊ ሞገድ የሚንጠዉን የከተሜ ነዋሪ በሥነ-ጽሁፋዊ ለዛ እያዋዛ በብዕሩ ለስላሳ ኩርኩም የሚያሳርፈዉ በዕዉቀቱ፣ በዚህ ሥራዉም የእሽባይነት (አሜን ባይነት) ዝማሜውን በተመለከተ የሚያነሳችዉ ጭብጦች የመጽኃፉ አንኳር ሃሳብ እንደ ሚሆን ይጠበቃል፡፡

በሎንደን ኦሎምፒክ ከራሞቱ፣ በሰሜን አሜሪካ የሾዉ ጉዞና በብራዉን ዩኒቨርስቲ የፌሎዉሺፕ ምርምር ከፊል ቆይታዉ ከዳያስፖራዉ ማህበረሰብ የታዘባቸዉን ማህበረ-ፖለቲካዊ ጉዳዮችን ከምዕራባዊያኑ ነባራዊ ክስተቶች ጋር እያዛመደ የሚያወጋን ጉዳይ መኖሩ አይቀርም፡፡

amenየበዕዉቀቱ የፍንገጣ ጽሁፍ ለጽዮን ብሄርተኞች የሚመች አይደለም፡፡ አሰላሳዩ ልጅ ብዕሩን ማንሳት ሲጀመር በድብድብ የጽድቅ በር የሚከፈት ይመስል የኃይማኖት “አርበኛች” ራሳቸዉን ለዱላ ያዘጋጃሉ፡፡ የነገር ጂራፋቸዉ የተፈተለ ነዉና ዘለፋና ስድብ ከአንደበታቸዉ አይጠፋም፡፡ ሃሳብን በሃሳብ መመከት የከሸፈዉ በገዢዎቻችን በኩል ብቻ ሳይሆን በዘመኑ ጎረምሳ “ኃይማኖተኛች” ጭምር ነዉ፡፡ ንግድና ክህነትን አጣምረዉ የሚጓዙ ምግባረ-ክብሪት የሆኑ ዲያቆናት የዚህ መሰል ድረጊት አራጋቢዎች ናቸዉ፡፡ ነገር በማቀጣጥሉ ረገድ የቤንዚልን ሚና ያስንቃሉ፡፡ ለአንዳንዶቹማ ከክህነት ትምህርቱ ጋር አብሮ የተሰጣቸዉ እስኪመስል ድረስ የነገር አራጋቢነት “ችሎታ”ቸዉ ከፍ ያለ ነዉ፡፡

ለሁሉም፤ ድብርት ተጫጭኖት ለከረመዉ የኢትዮጲያ ሥነ-ጽሁፍ ገበያ ጥሩ መነቃቃትን የሚፈጥር መጽሃፍ ገበያዉን ለመቀላቀል እያኮበኮበ ያለበት ሁኔታ ነዉ ያለዉ፡፡ እናም የመታከት ወራት እያለፉ ነዉና አይናችንን ከመስኮቱ ወደ በሩ እናማትር፤ ልትናፈቅ የሚገባት ድርሳን ቀርባለችና፡፡ የቀኑ ሰዉ ይበለን፡፡ “አሜን” እያልን “ከአሜን ባሻገር”ን እንጠብቅ፡፡

ሙሉአለም ገ.መድህን

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Literature Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Comments

  1. Firew Ayenachew says

    January 18, 2016 05:48 pm at 5:48 pm

    I hop will read it.

    Reply
  2. Yikir says

    January 19, 2016 07:01 pm at 7:01 pm

    Nuro tefnegona asro adirgognal ye ferenj doro.

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule