• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“የናፈቀ ሰዉ በር በሩን የታከተ ሰዉ መስኮቱን ይመለከታል” በዕዉቀቱ ስዩም

January 12, 2016 09:27 pm by Editor 2 Comments

ከዓመታት የንባብ ብህትዉና በኃላ በቀጣይ ሳምንት በመጽሃፍ መልኩ ብቅ የሚለዉ በዕዉቀቱ ስዩም፣ በርከት ያሉ ሞጋች ሃሳቦችን በሥነ-ጽሁፋዊ ለዛ እያዋዛ ወደ አደባባይ እንደሚያወጣ ጥርጥር የለዉም፡፡ “ከአሜን ባሻገር” ምን አለ? . . . የመራቂዉን ማንነት መፈተሸ …? ጥልቅ መጠይቅ …? ወይስ ለየት ያለ ፍንገጣ? … ብቻ ብዙ ነገር ይጠበቃል፡፡ በተለይ ጽዮን ተኮር ኃይማኖታዊ ባህልና መስመር ያለፈ ጥብቅ ብሄርተኝነት ስላጎበጣት ኢትዮጵያ “ከአሜን ባሻገር” ብዙ የምትለን ይመስለኛል፡፡

ታሪክን ከፖለቲካዊ ወገንተኝነት እና ከኃይማኖታዊ ጥብቅና በጸዳ መልኩ ለማየት የሚጥረዉ በዕዉቀቱ፣ ንባብ የፈጠረለት አቅሙን ተጠቅሞ በግሉ ከደረሰበት የታሪክ ምልከታ አኳያ የሚያካፍለን ብዙ ነገር እንደሚኖር እጠብቃለሁ፡፡ ባለመርማሪ ልቦናዉ በዕዉቀቱ፣ የጊዜችን ቋሚ ሽፍቶችን በተመለከተ ሽሙጥን በተሻገረ መልኩ መረር ያለ ሂስ እንደሚሰነዝር እሙን ነዉ፡፡ በተለየም የነጻዉ ፕሬስን ቅርቃር በነገስታቱ ዘመን ለአዝማሪዋች ይሰጥ ከነበረዉ ነጻነት አኳያ እያነጻጸረ ትዝብቱን እነደሚያካፍለን ግምቴ ነዉ፡፡ የሃገሪቱን ዳቦ አልባ ልማት፣ እንደ ግዙፍ ፋብሪካ አንድ አይነት ምርት እያመረቱ ስላሉት ዩኒቨርስቲዎቻችን፣ የንፉቅቅ ሚሄደዉን “ዴሞክራሲ” ያችንን በቸልታ የሚያልፋቸዉ አይመስልም፡፡ ማህበራዊ ሞገድ የሚንጠዉን የከተሜ ነዋሪ በሥነ-ጽሁፋዊ ለዛ እያዋዛ በብዕሩ ለስላሳ ኩርኩም የሚያሳርፈዉ በዕዉቀቱ፣ በዚህ ሥራዉም የእሽባይነት (አሜን ባይነት) ዝማሜውን በተመለከተ የሚያነሳችዉ ጭብጦች የመጽኃፉ አንኳር ሃሳብ እንደ ሚሆን ይጠበቃል፡፡

በሎንደን ኦሎምፒክ ከራሞቱ፣ በሰሜን አሜሪካ የሾዉ ጉዞና በብራዉን ዩኒቨርስቲ የፌሎዉሺፕ ምርምር ከፊል ቆይታዉ ከዳያስፖራዉ ማህበረሰብ የታዘባቸዉን ማህበረ-ፖለቲካዊ ጉዳዮችን ከምዕራባዊያኑ ነባራዊ ክስተቶች ጋር እያዛመደ የሚያወጋን ጉዳይ መኖሩ አይቀርም፡፡

amenየበዕዉቀቱ የፍንገጣ ጽሁፍ ለጽዮን ብሄርተኞች የሚመች አይደለም፡፡ አሰላሳዩ ልጅ ብዕሩን ማንሳት ሲጀመር በድብድብ የጽድቅ በር የሚከፈት ይመስል የኃይማኖት “አርበኛች” ራሳቸዉን ለዱላ ያዘጋጃሉ፡፡ የነገር ጂራፋቸዉ የተፈተለ ነዉና ዘለፋና ስድብ ከአንደበታቸዉ አይጠፋም፡፡ ሃሳብን በሃሳብ መመከት የከሸፈዉ በገዢዎቻችን በኩል ብቻ ሳይሆን በዘመኑ ጎረምሳ “ኃይማኖተኛች” ጭምር ነዉ፡፡ ንግድና ክህነትን አጣምረዉ የሚጓዙ ምግባረ-ክብሪት የሆኑ ዲያቆናት የዚህ መሰል ድረጊት አራጋቢዎች ናቸዉ፡፡ ነገር በማቀጣጥሉ ረገድ የቤንዚልን ሚና ያስንቃሉ፡፡ ለአንዳንዶቹማ ከክህነት ትምህርቱ ጋር አብሮ የተሰጣቸዉ እስኪመስል ድረስ የነገር አራጋቢነት “ችሎታ”ቸዉ ከፍ ያለ ነዉ፡፡

ለሁሉም፤ ድብርት ተጫጭኖት ለከረመዉ የኢትዮጲያ ሥነ-ጽሁፍ ገበያ ጥሩ መነቃቃትን የሚፈጥር መጽሃፍ ገበያዉን ለመቀላቀል እያኮበኮበ ያለበት ሁኔታ ነዉ ያለዉ፡፡ እናም የመታከት ወራት እያለፉ ነዉና አይናችንን ከመስኮቱ ወደ በሩ እናማትር፤ ልትናፈቅ የሚገባት ድርሳን ቀርባለችና፡፡ የቀኑ ሰዉ ይበለን፡፡ “አሜን” እያልን “ከአሜን ባሻገር”ን እንጠብቅ፡፡

ሙሉአለም ገ.መድህን

Filed Under: Literature Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Comments

  1. Firew Ayenachew says

    January 18, 2016 05:48 pm at 5:48 pm

    I hop will read it.

    Reply
  2. Yikir says

    January 19, 2016 07:01 pm at 7:01 pm

    Nuro tefnegona asro adirgognal ye ferenj doro.

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

Recent Posts

  • ሕገወጡ ትህነግ ወጣቶችን ለዳግም ዕልቂት እያሰናዳ ለፈረንጆች “ኢትዮጵያን አውግዙልኝ” እያለ ነው June 11, 2026 12:57 am
  • በሐዘንና ግልፅ ደብዳቤ ስም የተሸፈነ የድህረ ምርጫ ሀገር የማተራመስ ስትራቴጂ June 10, 2026 12:19 am
  • የጽምዶ ልክፍት June 9, 2026 12:49 am
  • ገዳዩ ማነው? አስገዳዩስ ማነው? June 5, 2026 02:37 pm
  • ጽንፈኝነት ግን በኢትዮጵያ ምድር ፈጽሞ ቦታ የለውም! June 5, 2026 01:47 pm
  • የትብብሩ “ብናሸንፍም ፓርላማ አንገባም” መግለጫ “ወንበር ስታጡ ነው” የሚል ከፍተኛ ተቃውሞ አስነሳ June 4, 2026 12:04 am
  • አዲሱ የትራምፕ የምርጫ መመሪያ፡ የአሜሪካ ዲፕሎማቶችን አፍ ያስዘጋ፤ ተቃዋሚዎች ተስፋ ያስቆረጠ June 3, 2026 08:50 pm
  • “ኢህአፓ ከምርጫው በኋላ ይሰነጠቃል” May 29, 2026 07:07 pm
  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
Copyright © 2026 · Goolgule