• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“የናፈቀ ሰዉ በር በሩን የታከተ ሰዉ መስኮቱን ይመለከታል” በዕዉቀቱ ስዩም

January 12, 2016 09:27 pm by Editor 2 Comments

ከዓመታት የንባብ ብህትዉና በኃላ በቀጣይ ሳምንት በመጽሃፍ መልኩ ብቅ የሚለዉ በዕዉቀቱ ስዩም፣ በርከት ያሉ ሞጋች ሃሳቦችን በሥነ-ጽሁፋዊ ለዛ እያዋዛ ወደ አደባባይ እንደሚያወጣ ጥርጥር የለዉም፡፡ “ከአሜን ባሻገር” ምን አለ? . . . የመራቂዉን ማንነት መፈተሸ …? ጥልቅ መጠይቅ …? ወይስ ለየት ያለ ፍንገጣ? … ብቻ ብዙ ነገር ይጠበቃል፡፡ በተለይ ጽዮን ተኮር ኃይማኖታዊ ባህልና መስመር ያለፈ ጥብቅ ብሄርተኝነት ስላጎበጣት ኢትዮጵያ “ከአሜን ባሻገር” ብዙ የምትለን ይመስለኛል፡፡

ታሪክን ከፖለቲካዊ ወገንተኝነት እና ከኃይማኖታዊ ጥብቅና በጸዳ መልኩ ለማየት የሚጥረዉ በዕዉቀቱ፣ ንባብ የፈጠረለት አቅሙን ተጠቅሞ በግሉ ከደረሰበት የታሪክ ምልከታ አኳያ የሚያካፍለን ብዙ ነገር እንደሚኖር እጠብቃለሁ፡፡ ባለመርማሪ ልቦናዉ በዕዉቀቱ፣ የጊዜችን ቋሚ ሽፍቶችን በተመለከተ ሽሙጥን በተሻገረ መልኩ መረር ያለ ሂስ እንደሚሰነዝር እሙን ነዉ፡፡ በተለየም የነጻዉ ፕሬስን ቅርቃር በነገስታቱ ዘመን ለአዝማሪዋች ይሰጥ ከነበረዉ ነጻነት አኳያ እያነጻጸረ ትዝብቱን እነደሚያካፍለን ግምቴ ነዉ፡፡ የሃገሪቱን ዳቦ አልባ ልማት፣ እንደ ግዙፍ ፋብሪካ አንድ አይነት ምርት እያመረቱ ስላሉት ዩኒቨርስቲዎቻችን፣ የንፉቅቅ ሚሄደዉን “ዴሞክራሲ” ያችንን በቸልታ የሚያልፋቸዉ አይመስልም፡፡ ማህበራዊ ሞገድ የሚንጠዉን የከተሜ ነዋሪ በሥነ-ጽሁፋዊ ለዛ እያዋዛ በብዕሩ ለስላሳ ኩርኩም የሚያሳርፈዉ በዕዉቀቱ፣ በዚህ ሥራዉም የእሽባይነት (አሜን ባይነት) ዝማሜውን በተመለከተ የሚያነሳችዉ ጭብጦች የመጽኃፉ አንኳር ሃሳብ እንደ ሚሆን ይጠበቃል፡፡

በሎንደን ኦሎምፒክ ከራሞቱ፣ በሰሜን አሜሪካ የሾዉ ጉዞና በብራዉን ዩኒቨርስቲ የፌሎዉሺፕ ምርምር ከፊል ቆይታዉ ከዳያስፖራዉ ማህበረሰብ የታዘባቸዉን ማህበረ-ፖለቲካዊ ጉዳዮችን ከምዕራባዊያኑ ነባራዊ ክስተቶች ጋር እያዛመደ የሚያወጋን ጉዳይ መኖሩ አይቀርም፡፡

amenየበዕዉቀቱ የፍንገጣ ጽሁፍ ለጽዮን ብሄርተኞች የሚመች አይደለም፡፡ አሰላሳዩ ልጅ ብዕሩን ማንሳት ሲጀመር በድብድብ የጽድቅ በር የሚከፈት ይመስል የኃይማኖት “አርበኛች” ራሳቸዉን ለዱላ ያዘጋጃሉ፡፡ የነገር ጂራፋቸዉ የተፈተለ ነዉና ዘለፋና ስድብ ከአንደበታቸዉ አይጠፋም፡፡ ሃሳብን በሃሳብ መመከት የከሸፈዉ በገዢዎቻችን በኩል ብቻ ሳይሆን በዘመኑ ጎረምሳ “ኃይማኖተኛች” ጭምር ነዉ፡፡ ንግድና ክህነትን አጣምረዉ የሚጓዙ ምግባረ-ክብሪት የሆኑ ዲያቆናት የዚህ መሰል ድረጊት አራጋቢዎች ናቸዉ፡፡ ነገር በማቀጣጥሉ ረገድ የቤንዚልን ሚና ያስንቃሉ፡፡ ለአንዳንዶቹማ ከክህነት ትምህርቱ ጋር አብሮ የተሰጣቸዉ እስኪመስል ድረስ የነገር አራጋቢነት “ችሎታ”ቸዉ ከፍ ያለ ነዉ፡፡

ለሁሉም፤ ድብርት ተጫጭኖት ለከረመዉ የኢትዮጲያ ሥነ-ጽሁፍ ገበያ ጥሩ መነቃቃትን የሚፈጥር መጽሃፍ ገበያዉን ለመቀላቀል እያኮበኮበ ያለበት ሁኔታ ነዉ ያለዉ፡፡ እናም የመታከት ወራት እያለፉ ነዉና አይናችንን ከመስኮቱ ወደ በሩ እናማትር፤ ልትናፈቅ የሚገባት ድርሳን ቀርባለችና፡፡ የቀኑ ሰዉ ይበለን፡፡ “አሜን” እያልን “ከአሜን ባሻገር”ን እንጠብቅ፡፡

ሙሉአለም ገ.መድህን

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Literature Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Comments

  1. Firew Ayenachew says

    January 18, 2016 05:48 pm at 5:48 pm

    I hop will read it.

    Reply
  2. Yikir says

    January 19, 2016 07:01 pm at 7:01 pm

    Nuro tefnegona asro adirgognal ye ferenj doro.

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የአየለ ጫሚሶ ቅንጅት ፈረሰ January 18, 2021 02:31 pm
  • ህወሓት ተሠረዘ!!! January 18, 2021 01:32 pm
  • ዓሲምባ፣ ሣልሳዊ ወያኔና ባይቶና ከመፍረሳቸው በፊት ማብራሪያ እንዲሰጡ ተነገራቸው January 18, 2021 01:00 pm
  • ቤተሰቦች አስከሬን መውሰድ እንደሚችሉ ተነገረ January 14, 2021 06:48 pm
  • ስብሃት፤ “ከሞትን ቆይተናል፤ … አሁን የቀብር ሥነ-ስርዓታችን” እየተፈጸመ ነው January 14, 2021 01:37 pm
  • “ተመልሰን እንነሳለን” ያሉት ህወሓቶች ተመልሰው ወደማይነሱበት ተሸኙ January 13, 2021 01:12 pm
  • አፋር ነፃ አውጪ (ኡጉጉሙን) ለመጠቀም የታቀደው የህወሃት ሤራ ከሽፏል January 13, 2021 01:10 pm
  • ህወሃትን ወደ ጅቡቲ ለማሻገር ሲሰሩ የነበሩ የአፋር ታጣቂዎች በሰላም ወደ ክልሉ ገቡ January 13, 2021 06:47 am
  • በታህሳስ ወር ብቻ ከ344 ሚሊየን ብር በላይ የኮንትሮባንድ ዕቃ ተያዘ January 13, 2021 06:10 am
  • የብልፅግና ፓርቲ ቀጣይ ፈተና ምን ሊሆን ይችላል? January 13, 2021 04:10 am
  • ለትምህርት እንዲሆነን January 11, 2021 01:20 pm
  • “ከተቀበሩበት የጃርት ጉድጓድ ነው ያወጣናቸው” መቶ አለቃ ስዩም ቱርቦ January 11, 2021 12:11 pm
  • የተደመሰሱና በቁጥጥር ሥር የዋሉ የወንበዴው አባላት ይፋ ሆነ January 7, 2021 01:16 pm
  • ዐቢይና መኮንኖቹ በመቀሌ፤ “ድሉ የመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ነው” December 13, 2020 02:36 pm
  • ወንበዴው ህወሓት ከ1.4 ትሪሊዮን ብር በላይ ዘርፎ በውጭ አገራት ባንኮች አስቀምጧል December 8, 2020 01:05 am
  • ማይካድራ – የትህነግ የዘር ማጥፋት ጥግ ቋሚ ምስክር December 8, 2020 12:57 am
  • የወልቃይት ጠገዴ እናቶች ሰቆቃ ሲታወስ December 8, 2020 12:50 am
  • የደብረጽዮን ዋሻ December 7, 2020 11:30 pm
  • ባለ ከዘራው ኮሎኔል December 7, 2020 05:15 pm
  • ሰላማዊ ሕይወት በማይጨው December 7, 2020 04:12 pm
  • ተጠርጣሪ የፌዴራልና የአዲስ አበባ ፖሊሶች የመያዣ ትዕዛዝ ወጣባቸው December 7, 2020 11:46 am
  • ከ3 ሺህ በላይ ተተኳሽ ጥይቶች በወልዲያ ጉምሩክ ሊያሳልፉ የሞከሩ 4 ግለሰቦች ተያዙ! December 7, 2020 11:18 am
  • ወንበዴዎቹ ይጠቀሙባቸው የነበሩ ተሽከርካሪዎችና የግል ሰነዶቻቸው ተያዙ December 7, 2020 10:50 am
  • ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ በሶማሌ ክልል ተመሠረተ December 7, 2020 10:31 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2021 · Goolgule