ለጠቅላይ ሚኒስትሩና ለጓደኞቻቸው በሙሉ፤ ሰላምታዬን አቀርብላችኋለሁ፡፡ ኢትዮጵያ የእግዚአብሔር አገር ነች፤ የኢትዮጵያ ሕዝብ የእግዚአብሔር ሕዝብ ነው፤ ክርስቲያኑም፣ እስላሙም፣ አረመኔውም የእግዚአብሔር ነው፤ እንደየእምነቱ በእግዚአብሔር ፈቃድ የሚኖር ነው፡፡ የእግዚአብሔር ጊዜ የተለየ ነው፤ ትእግስቱን ስለሚያረዝመው የተረሳ ያስመስለዋል፤ እግዚአብሔር ግፍን አይረሳም፤ እግዚአብሔር ሁሌም ለአቅመ-ቢሶች ጉልበት የሚሆንበት መንገድ አለው፤ ግፍ በእግዚአብሔር በር ላይ እንደተጣለ ግም ቆሻሻ ነው፤ እግዚአብሔር ሲፈቅድ ይጠርገዋል፤ ወይም ያስጠርገዋል፡፡ እግዚአብሔር መንገዱ ብዙ ነው፤ ግፍን የሚያስከፍለው በተለያየ መንገድ ነው፤ በግፈኛው ቤተሰብ ላይ ሁሉ የግፈኛነት ጠባሳን ያሳርፍበታል፤ ሰዎች ለሥልጣናቸው ባላቸው ቅናት የእግዚአብሔርን ሥልጣን ይጋፋሉ፤ የእግዚአብሔርን ሥልጣን መጋፋት … [Read more...] about ደብዳቤ
Socio-Political
ማኅበራዊ-ሽከታ
ጳጳሶችና ስደት
እንዲያውም ርእሱን ካህናትና ስደት ብለው ይሻላል፤ ካህናት የሁሉንም ሃይማኖቶች መሪዎችን ይመለከታል፤ ዓላማዬም ሁሉም የሃይማኖት መሪዎችን የሚነካ ነው፤ ነገር ግን የእኔ እውቀት በክርስትናው ላይ ጎላ ያለ በመሆኑ የክርስቲያኖቹ መሪዎች ላይ ያተኮርኩ ቢመስልም ሁሉንም ይመለከታል፤ በተለይ መነኩሴዎች ላይ የማነጣጥርበትም የተለየ ምክንያት አለኝ፡፡ በመጀመሪያ አንድ መሠረታዊ ነገር ላብራራ፤ እንደማንኛውም ሰው ስለፍርሃትና ስለጥቃት አውቃለሁ፤ በተለያዩ መንገዶች በመርማሪዎች የተሰቃዩ ሰዎች ሲናገሩ ሰምቻለሁ፤ የጻፉትንም አንብቤአለሁ፤ ከሁሉም በላይ ፍርሃት የግል መሆኑን አውቃለሁ፤ በዚህም ምክንያት ሰውን ለምን ፈራህ ብሎ መውቀስም አስቸጋሪ መሆኑ ይገባኛል፤ ስለዚህም ይህንን የምጽፍበት ምክንያት የተሰደዱትን ለመውቀስና እነሱን ዝቅ አድርጌ ራሴን ከፍ ለማድረግ አይደለም፤ ከቃሌ በቀር ይህንን … [Read more...] about ጳጳሶችና ስደት
“በሴትነቴ የደረሰብኝ በደል ቁስሉ ከኅሊናዬ ባይጠፋም ታሪኬ ተቀይሯል”
* “... እህታችን ታሪኳን ስትነግረኝ፣ ለፍትህ እንደምትመጥን አመንኩ” ኦባንግ “... የተረሳሁ ነበርኩ፡፡ የደረሰብኝ ግፍ ጠባሳ የሚያልፍ መስሎ አይታየኝም ነበር። ግን ብርሃን ሆነልኝ። በየትኛውም ወቅት ልረሳው የማልችለው ኦባንግ ሜቶ ችግሬን ዝቅ ብሎ አደመጠኝ። ና ባልኩት ቦታ ሁሉ ፈጥኖ እየደረሰ ፍትህ ደጅ እንድቆም ረዳኝ። ስለ እሱ ለመናገር ቃላቶች የሉኝም። ከሁለት ዓመት በፊት ያለመድሃኒት አልተኛም ነበር። ዛሬ መድሃኒት ከመቃም ተገላግያለሁ። በሴትነቴ የደረሰብኝ በደል ቁስሉ ከህሊናዬ ባይጠፋም ታሪኬ ተቀይሯል። … በየቦታው ፍትህ የተዛባባችሁ ወገኖቼ ዝም አትበሉ። ፍትህ በደጃችሁ ነው። ግን ተናገሩ። ሆን ብላችሁ ያላጠፋችሁት ጥፋት አያሳፍራችሁምና ራሳችሁን ከዝምታ ድባብ አላቅቁ...” ይህ ስሟ እንዳይነገር ከጠቀችው እህት አንደበት ነው። “... እኔ የሰራሁት ሥራዬን ነው። … [Read more...] about “በሴትነቴ የደረሰብኝ በደል ቁስሉ ከኅሊናዬ ባይጠፋም ታሪኬ ተቀይሯል”
ችጋር – የሶስት ዓመት የዞረ ድምርና የህወሃት የፖሊሲ ክሽፈት
የፖለቲካ አለመረጋጋት፣ የባለስልጣናት ሌብነትና ድርጅታዊ ዝርፊያ፣ የማንነት ጥያቄ፣ ድህነት፣ ስራ አጥነት፣ አድሏዊ አመለካከት፣ የሰብአዊ መብት አለመከበር፣ የማሰብ፣ የመቃወም፣ የመናገርና የመጻፍ ተፈጥሮአዊ መብቶች መጣስ፣ የዲሞክራሲ መብቶች አለመከበር የፈጠረው ስሜት ተጠራቅሞ እየገነፈለ ባለበት በአሁኑ ወቅት፣ ኢትዮጵያ የተነከረችበት ከፍተኛ እዳና የተከሰተው ችጋር አገሪቱን ወደ ከፋ ቀውስ እንዳያመራት ስጋት አይሏል። ባለፉት ስድስት ወራቶች ሰላማዊ ጥያቄ ያነሱ ዜጎች በጥይት ተደብድበው ሞተዋል። በዚሁ ሳቢያ ኦሮሚያ በእምባ ነፍራለች። ህጻናትና እናቶች በህወሃት ልዩ ታማኝ ኃይሎች ተገድለዋል። የታሰሩ ዜጎች ቁጥር በሺህ የሚቆጠር ነው። የት እንደ ደረሱ የማይታወቁ ወገኖች ስለመበራከታቸው ቤተሰቦች ስምና አድራሻ ሳይደብቁ እየተናገሩ ነው። አማራ ክልል “በግድ ትግሬ መሆን በቃን” … [Read more...] about ችጋር – የሶስት ዓመት የዞረ ድምርና የህወሃት የፖሊሲ ክሽፈት
“የልጄን ነገር አደራ…” እናት ሎሚ
የእናትን መሪር ሐዘን ሰምቸ ሆዴ ተላውሷል፣ የእናትን ጥልቅ ጭንቀቷ፣ ያለ አባት በአሳር በመከራ ያሳደገቻት የእናትን ሎሜ መሪር ሐዘን ተረድቸ ህመም መታመሜ እውነት ሳለ በዝምታ እየቆሰልኩ ማስረጃ መረጃ ፍለጋ መዋተቴ ህመሜን አክብዶታል፡፡ ከጉያዋ ወሽቃ፣ በትንፋሿ አሙቃ፣ ስታገኝ በደስታ፣ ስታጣ ተከፍታ ድሃ አደግ ቤቷን አሟሙቃ ነገን ልጆቿን ለወግ ለማዕረግ የማድረስ ምኞት ተስፋን ሰንቃ ተስፋዋን የተነጠቀች እናት እንባ ውስጤን አድምቶ አቃጥሎታል። እናት ዛሬ ማለዳ በላኩልኝ መልዕክት እንዲህ ይላል “የልጀን ነገር አደራ እባክህ ነፍሴን አሳርፋት" … ሰው ሆዬ ሲጨንቀው እኔ መረጃን ከምንጩ ከማሰራጨት ባለፈ ሁሉን ማድረግ የሚቻለኝ አድርጎ ይስለኛል፤ እኔ ግን አቅሙ የለኝም! መረጃዎችን ለወገናቸው ጥቅም ቅድሚያ ከሚሰጡ የመንግስትና የድርጅት አባላት በሚስጥር፤ ከቀሩት ወገኖች … [Read more...] about “የልጄን ነገር አደራ…” እናት ሎሚ
የጥቁር ሕዝብ ኩራት!
መጪውን የአድዋ ቀን ስናስብ “እምዬ ምኒልክ ምን ዓይነት ውርስ ትተውልን ሄዱ?” ብለን እንድንጠይቅ የሚያደርገን ነው፡፡ በመሆኑም ወደ ጦርነት ለመግባት ሳይፈልጉ “በግድ” ወደሄዱበት የጣሊያን ጦርነት መለስ ብለን የሆነውን እንድናስብ ወደድን፡፡ ክተት፡- “እግዚአብሔር በቸርነቱ እስካሁን ጠላትን አጥፍቶ አገር አስፍቶ አኖረኝ፡፡ እኔም እስካሁን በእግዚአብሔር ቸርነት ገዛሁ፡፡ እንግዲህ ብሞትም ሞት ለሁሉ ነውና ስለ እኔ ሞት አላዝንም፤ ደግሞ እግዚአብሔር አሳፍሮኝ አያውቅም፤ እንግዲህም ያሳፍረኛል ብዬ አልጠራጠርም፡፡ አሁንም አገር የሚያጠፋ፣ ሃይማኖት የሚለውጥ ጠላት እግዚአብሔር የወሰነልንን የባሕር በር አልፎ መጥቷልና እኔም ያገሬ ከብት ማለቁንና የሰዉን መድከም አይቼ እስካሁን ዝም ብለው ደግሞ እያለፈ እንደ ፍልፈል መሬት ይቆፍር ጀመር፡፡ አሁን ግን በእግዚአብሔር ረዳትነት … [Read more...] about የጥቁር ሕዝብ ኩራት!
አቅም የተፈጠረላቸው ፈላሾች – ህወሃቶች
ከ1997 ምርጫ በኋላ ወደ አዲስ አበባ ከፈለሱት የክልል ነዋሪዎች መካከል ከ87 በመቶ በላይ የትግራይ ተወላጆች እንደሆኑ አንድ የስታትስቲክስ ባለስልጣን ባለሙያ ጠቆሙ። ቁጥሩ የሚያሳየው ባግባቡ ከሃብትና ንብረት፣ ወይም ከመተዳደሪያ ጋር የተመዘገቡትን ብቻ እንደሚያካትት ባለሙያው አመልክተዋል። ከዘጠና በመቶ በላይ ከሌሎች ክልሎች ወደ አዲስ አበባ የሚፈልሱት የእለት ጉርስ ፍለጋ ነው። በኢንቨስትመንት ስም በሚፈናቀሉ ዜጎች ኮቴ፣ በኮንደሚኒየም ቤቶች ዝውውር፣ መከላከያ፣ ደህንነትና ሁሉንም ዓይነት የፖሊስ ተቋማት ጨምሮ በመንግሥት መስሪያ ቤቶች ቅጥርና በመሳሰሉት ሰፊ ቁጥር ያላቸው የትግራይ ተወላጆች ወደ አዲስ አበባ ተምመዋል፤ እየተመሙም ናቸው። እንደባለሙያው የሌሎች ክልል ተወላጆች በስፋት ወደ አዲስ አበባ ቢፈልሱም፣ የትግራይ ተወላጆችን ልዩ የሚያደርገው “አቅም እየተፈጠረላቸው … [Read more...] about አቅም የተፈጠረላቸው ፈላሾች – ህወሃቶች
የመለስ “ሌጋሲ” – የድርብ አኻዝ ዕድገት ውጤት
ሥልጣን የያዙ ሰሞን ሞት የቀደማቸው መለስ ሲጠየቁ የኢትዮጵያን ሕዝብ በቀን ሦስት ጊዜ እመግባለሁ ወይም ሲመገብ አያለሁ የሚል የውሸት ተስፋ ሰጥተው ነበር፡፡ “የቀማኛ ኢኮኖሚ አቀንቃኝ” የነበሩት መለስ ለሥልጣናቸው ማራዘሚያ ጥቂቶችን በሃብት እንዲወጠሩ ሲያደርጉ የተቀረውን ኢትዮጵያዊ በቀን ሶስቴ ቀርቶ በሶስት ቀን አንዴ የማይመገብ አድርገውት ተሰናብተዋል፡፡ “ሌጋሲያቸውን እንጠብቃለን፤ እናስጠብቃለን” የሚሉት ያሁኖቹ ዘራፊዎችና ተላላኪዎች አገር በሁለት አኃዝ አድጋለች፤ ኢኮኖሚው ዓለምን እያስደነቀ ነው፤ ህዳሴ ነው፤ ውዳሴ ነው፤ … በማለት በቁማቸው ይዋሻሉ፤ የጥቅም ተካፋዮቻቸውም ይህንኑ ይዘው በየቀኑ ሲያናፉ ይውላሉ፡፡ ህወሃት ስለዘረጋው የዘራፊ፤ የቀማኛ፤ የሌባ፤ ኢኮኖሚ ብዙ ሊባልበት ይቻላል፡፡ ሌብነቱን ደግሞ መለስ ራሳቸው መስክረው ነው የሞቱት፡፡ “ያስቸገረን የመንግሥት … [Read more...] about የመለስ “ሌጋሲ” – የድርብ አኻዝ ዕድገት ውጤት
የኛ የነዳጅ ዋጋ የሚቀንሰው መቼ ነው?
ከጊዜ ወደ ጊዜ እያሽቆለቆለ የመጣው የዓለም የነዳጅ ዋጋ አሁን ደግሞ ሊብስበት ነው፡፡ በኢራን ላይ የተጣለው የኢኮኖሚ ማዕቀብ ትናንት በመነሳቱ በዓለም ገበያ ለአንድ በርሜል ድፍድፍ ዘይት የሚከፈለው ዋጋ ከ31 ዶላር ወደ 28 ዶላር ገብቷል፡፡ ይህ በአንድ ቀን የታየ የዋጋ ልዩነት ለወደፊቱ እየባሰ ሊሄድ እንደሚችል የዓለም የኢኮኖሚ ጠበብት በመናገር ላይ ይገኛሉ፡፡ በኢኮኖሚክስ Principle መሰረት ዋጋ ሲቀንስ የፍላጎት መጠን ይጨምራል፡፡ የገንዘብ የመግዛት አቅምም ይጨምራል፡፡ ዋጋውን ተከትሎ በአቅርቦት ላይ የሚደረግ ቅናሽ ካልታየ በዚያው ዋጋ ብዙ ምርትና አገልግሎት መግዛት ይቻላል፡፡ አቅራቢው ምርቱን የሚጨምር ከሆነ ደግሞ (በኢራን ላይ የተጣለው ማዕቀብ በመነሳቱ የነዳጅ አቅርቦቱ መጨመሩን ልብ ይሏል) ገዥው የሚገዛው ምርትና አገልግሎት እየጨመረ ይሄዳል፡፡ ስለዚህ እጥረት … [Read more...] about የኛ የነዳጅ ዋጋ የሚቀንሰው መቼ ነው?
ጥምቀትና ጎንደር Vs የትዝብት ወግ
“ጥምቀትን በጎንደር መታደም መባረክ ነው” ይህ የብዙሃኑ የእምነቱ ተከታዮች የምስክርነት ቃል ነው፡፡ ጥምቀትና ጎንደር የገጠሙ እለት እንኳንስ ለጎብኝዎች ለነዋሪዎችም ታይተው አይጠገቡም፡፡ የጎንደር ጥምቀት በዓል ከመላ ኢትዮጵያ አከባበር የሚለይባቸው በሁለት ተያያዥ ምክንያቶች ይመስለኛል፡፡ ከቀድመው የመሳፍንት እና የአፄዉ ስርዓት ጋር በተያያዘ ከተማዋ ለረዥም ዓመታት መናገሻ ከተማ ሆና መቆየቷ፣ በጊዜው የነበረው ኃይማኖታዊ መንግስት በመሆኑ አብዛኛው ነዋሪ ጥብቅ የኦርቶዶክስ ክርስትና ኃይማኖት ተከታይ ከመሆኑ ጋር በተያያዘ ከሌላው አካባቢ (ከተማ) በተለየ መልኩ “የአርባ አራቱ ታቦታት” መገኛ መሆኗ የመጀመሪያው ምክንያት ሲሆን፤ ሁለተኛው ምክንያት ደግሞ በአስራ ሰባተኛው መቶ ክፍለ ዘመን አጋማሽ ከአፄ ፋሲል ቤተመንግሥት ምስረታ በኋላ ከቤተ መንግሥቱ በስተ ምዕራብ በኩል አራት … [Read more...] about ጥምቀትና ጎንደር Vs የትዝብት ወግ










